en
Feedback
Addis መረጃ™

Addis መረጃ™

Open in Telegram

@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹 . ⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬ ⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬ መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis መረጃ™

Channel Addis መረጃ™ (@addis_mereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 41 888 subscribers, ranking 6 308 in the News & Media category and 800 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 41 888 subscribers.

According to the latest data from 02 February, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -500 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹 . ⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬ ⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬ መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 February, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

Buy Ad
41 888
Subscribers
No data24 hours
-987 days
-50030 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
February '26
February '260
in 0 channels
January '260
in 0 channels
Get PRO
December '25
+3
in 0 channels
Get PRO
November '25
+1
in 0 channels
Get PRO
October '25
+2
in 0 channels
Get PRO
September '25
+13
in 0 channels
Get PRO
August '250
in 0 channels
Get PRO
July '250
in 0 channels
Get PRO
June '250
in 2 channels
Get PRO
May '25
+4
in 0 channels
Get PRO
April '25
+1
in 0 channels
Get PRO
March '25
+1
in 0 channels
Get PRO
February '250
in 0 channels
Get PRO
January '25
+1
in 1 channels
Get PRO
December '24
+16
in 1 channels
Get PRO
November '24
+14
in 1 channels
Get PRO
October '24
+10
in 0 channels
Get PRO
September '24
+19
in 0 channels
Get PRO
August '24
+18
in 0 channels
Get PRO
July '24
+60
in 0 channels
Get PRO
June '24
+1
in 1 channels
Get PRO
May '24
+118
in 0 channels
Get PRO
April '24
+206
in 0 channels
Get PRO
March '24
+150
in 3 channels
Get PRO
February '24
+41
in 1 channels
Get PRO
January '24
+51
in 2 channels
Get PRO
December '23
+56
in 2 channels
Get PRO
November '23
+14
in 4 channels
Get PRO
October '23
+131
in 5 channels
Get PRO
September '23
+44
in 0 channels
Get PRO
August '23
+165
in 0 channels
Get PRO
July '23
+106
in 0 channels
Get PRO
June '23
+51
in 0 channels
Get PRO
May '23
+153
in 0 channels
Get PRO
April '23
+338
in 0 channels
Get PRO
March '23
+123
in 0 channels
Get PRO
February '23
+461
in 0 channels
Get PRO
January '23
+384
in 0 channels
Get PRO
December '22
+174
in 0 channels
Get PRO
November '22
+227
in 0 channels
Get PRO
October '22
+303
in 0 channels
Get PRO
September '22
+765
in 0 channels
Get PRO
August '22
+905
in 0 channels
Get PRO
July '22
+405
in 0 channels
Get PRO
June '22
+190
in 0 channels
Get PRO
May '22
+293
in 0 channels
Get PRO
April '22
+142
in 0 channels
Get PRO
March '22
+251
in 0 channels
Get PRO
February '22
+145
in 0 channels
Get PRO
January '22
+163
in 0 channels
Get PRO
December '21
+117
in 0 channels
Get PRO
November '21
+377
in 0 channels
Get PRO
October '21
+563
in 0 channels
Get PRO
September '21
+360
in 0 channels
Get PRO
August '21
+929
in 0 channels
Get PRO
July '21
+1 114
in 0 channels
Get PRO
June '21
+650
in 0 channels
Get PRO
May '21
+281
in 0 channels
Get PRO
April '21
+344
in 0 channels
Get PRO
March '21
+272
in 0 channels
Get PRO
February '21
+261
in 0 channels
Get PRO
January '21
+778
in 0 channels
Get PRO
December '20
+114 755
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
01 February0
Channel Posts
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 7 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ገቢ አገኘሁ አለ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።የአየር
+1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 7 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ገቢ አገኘሁ አለ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው እንደገለጹት በዓመቱ 6 ዓለም አቀፍ ጣቢያዎች መክፈት የቻለው አየር መንገዱ 13 የተለያዩ አውሮፕላኖች ወደ ስራ አስገብቷል። በ2017 በጀት ዓመት 19 ሚሊየን መንገደኞችን አየር መንገዱ ማጓጓዝ ሲችል በጭነት አገልግሎት ደግሞ 785 ሺህ 323 ቶን በላይ ካርጎ እንዳጓጓዘም ጨምረው አስታውቀዋል። ከመንገደኞችና ዕቃ ጭነት አገልግሎትም 7 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱንም አስታውቀዋል።እንደ ኤፍ ኤም ሲ ዘገባ አሁን ላይ የአየር መንገዱ የሀገር ውስጥ በረራ መዳረሻዎች 21 መሆናቸውን እና በቅርቡ የሚጠናቀቁ የ5 መዳረሻዎች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን አቶ ጣሰው ገልጸዋል። @YeneTube @FikerAssefa

2
ኤርትራ 10 ኪ.ሜ ወደ ኢትዮጵያ ገብታለች በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የጀርመን ዜና ወኪል ከስፍራው አንድ ዘገባ አሰራጭቷል፡፡ በመቀሌ ነዋሪ የሆኑ አንዲት ለዜና አውታሩ ሲናገሩ ‹‹አሁን ላይ ሆነን ምንም ማቀድ አንችልም፡፡ አዲስ ጦርነት ነገ ሊጀመር ይችላል፡፡›› ያሉ ሲሆን ነዋሪው በዚህ የተነሳ ከፍተኛ ፍርሀት ውስጥ መውደቁን አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ኑሮ በጣም እየተወደደ ነው፡፡ እኛ ሰላማዊ መፍትሄ መጥቶ ወደስራችን መመለስና ህይወታችንን መልሰን መገንባት ነው የምንፈልገው›› ብለዋል፡፡ እንደዘገባው በህወሀት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል ተከትሎ የትግራይ መከላከያ ሀይል(ቲዲኤፍ) ዋና አዛዥ የነበሩት ታደሰ ወረደ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ሆነዋል፡፡፡ እሳቸው በህዝቡ ዘንድ ያለውን ስጋት በማጣጣል ‹‹ጦርነት አይኖርም፡፡ ከትግራይ በኩል ምንም አይነት ቀስቃሽ ሁኔታ የለም›› በማለት እየተናገሩ መሆናቸውንም አስረድቷል፡፡ ዘገባው ሲቀጥል በሌላ በኩል የህወሀት ሊቀመንበር የሆኑት ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ደግሞ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ለተፈጠረው ችግር ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲፈለግ እያሳሰቡ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ የፌዴራል መንግስቱና አጋሮቹ ለጦርነት እያደረጉ ካለው ዝግጅት እንዲቆጠብ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግበት ጥሪ ማቅረባቸውንም አስረድቷል፡፡ ይሁንና እነዚህ ሁሉ የመቀሌ ነዋሪዎችን ስጋት እንዳልቀረፉ ገልጿል፡፡ አንድ የከተማው ነዋሪ ሲናገሩ ‹‹ህዝቡ አሁን ከባንክ ገንዘብ እያወጣ ነው፡፡ እንደጤፍ የመሳሰሉ እህሎችም ከመጋዘን እያለቁ ነው›› ያሉ ሲሆን ለሁለቱም የህወሀት አንጃዎችም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በመልእክታቸውም ‹‹ሁለቱም የህወሀት አንጃዎች ወይ ስልጣን ይልቀቁ፣ አልያም ተፅእኗቸውን ተጠቅመው ከማእከላዊው መንግስት ጋር ይህንን ቀውስ ለማስወገድና ጦርነትን ለማስቀረት ይስሩ›› ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል፡፡ በሌላ በኩል በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ድጋሚ ጦርነት ይቀሰቀሳል የሚል ስጋት እንዳለ የጠቀሰውዘገባው በዚህ ጉዳይ የጀርመን አለም አቀፍና የደህንነት ጉዳዮች ኢኒስቲትዩት የአፍሪካ ጉዳዮች ኤክስፐርት የሆኑትን ጊርት ኩርዝ ማነጋገሩን አስታውቋል፡፡ ኩርዝ ለዜና አውታሩ በሰጡት ማብራሪያ ሁለቱ አገራት ሙሉ ጦርነት ውስጥ ይገባሉ የሚል እምነት እንደሌላቸው ጠቅሰው ይሁንና በውክልና የሚደረግ ግጭት እንደሚኖር አስረድተዋል፡፡ ዘገባው አያይዞም ኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት 10 ኪሎሜትር መግባቷንና ጦር እያሰለጠነች መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል። @Yenetube @Fikerassefa
22 681
3
አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል። የሱዳን ጦር የኢትዮ
አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል። የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር። በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡ በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡ የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡ @Yenetube @Fikerassefa
22 450
4
ኢሎን መስክ የፖለቲካ ፓርቲ አቋቋመ ኢሎን መስክ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ያለው የቅርብ ወዳጅነት በአለመግባባት ከተጠናቀቀ ከሳምንታት በኋላ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ አቋቁሜያለሁ አለ። ቢሊየነሩ የፖለቲካ ፓርቲን ማቋቋሙን ለሪፐብሊካን እና ዲሞክራቲክ የሁለት ፓርቲ ስርዓት ፈተና እንደሆነ በመግለጽ በማህበራዊ ሚዲያው ኤክስ ገጹ ላይ አስታውቋል። ሆኖም ፓርቲው በይፋ በአሜሪካ የምርጫ ባለሥልጣን መመዝገቡ ግልፅ አይደለም ከአሜሪካ ውጭ በመወለዱ ለአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ብቁ ያልሆነው መስክ ፓርቲውን ማን እንደሚመራው አልተናገረም። መጀመሪያ ከትራምፕ ጋር በነበረው አለመግባባት ወቅት ፓርቲ የመመስረት ሃሳብን አንስቶ የነበረው መስክ፣ አለመግባባቱ እየተካረረ መጥቶ በአስተዳደሩ ውስጥ የነበረውን ኃላፊነት ለቅቆ ከቀድሞ የቅርብ ወዳጁ ጋር የተካረረ አለመግባባት ውስጥ መግባቱ የአደባባይ ሚስጥር ነበር። መስክ ከፕሬዚደንት ትራምፕ ጋር የተካረረ አለመግባባት ውስጥ በነበረበት ወቅት የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን በአሜሪካ ውስጥ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ መኖር ይኖርበት እንደሆን የሚጠይቅ አስተያየት ለጥፏል። መስክ በቅዳሜው ልጥፍ ላይ ያንን የሕዝብ አስተያየት በመጥቀስ "2 ለ 1 በሆነ ውጤት፣ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ እንዲኖር ፍላጎታችሁን አሳይታችኋል! አገራችንን በቆሻሻና በሌብነት ወደ ኪሳራ ስለመውሰድ ስንነጋገር የምንኖረው በአንድ ፓርቲ ስርዓት እንጂ በዲሞክራሲ አይደለም።" ሲል ጽፏል። አክሎም "ዛሬ የአሜሪካ ፓርቲ የተመሰረተው ነፃነታችሁን ሊመልስላችሁ ነው" ብሏል። ከቅዳሜ ጀምሮ የፌዴራል ምርጫ ኮሚሽን ፓርቲው በይፋ መመዝገቡን የሚጠቁሙ ሠነዶችን ይፋ አላደረገም። በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ከተለምዷዊው የሁለት ፓርቲ ስርዓት ውጪ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችም ቢኖሩም፣ እውነተኛ ጫና ለመፍጠር በአገር አቀፍ ደረጃ ጠንካራ ተቀባይነት ማግኘት አዳጋች ነው። ባለፈው ዓመት በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንደ ሊብሪተያን ፓርቲ፣ ግሪን ፓርቲ እና ፒፕልስ ፓርቲ ያሉ እጩዎች ትራምፕን ወይም የዴሞክራቲክ ተቀናቃኛቸውን ካማላ ሃሪስን እንዳያሸንፉ ለማድረግ ያልተሳካ ሙከራ አድርገዋል ። መስክ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የትራምፕ ዋና ደጋፊ ነበር። ባለፈው ዓመት በተደረጉ የምርጫ ቅስቀሳዎች ወቅት ከፕሬዚደንቱ ጎን በአጋፋሪነት የነበረው መስክ ሥልጣን ከያዙ በኋላም የአራት ዓመት ልጁ ትራምፕን እንዲያገኝ ኦቫል ኦፊስ ድረስ ይዞት መጥቷል። መስክ የትራምፕን የምርጫ ቅስቀሳ በገንዘብ ከደገፉ ባለሀብቶች መካከል ዋነኛው ነው። ፕሬዚደንቱ ዳግም ሥልጣናቸውን እንዲይዙ 250 ሚሊዮን ዶላር አውጥቷል። ከምርጫው በኋላም በፌዴራል በጀት ውስጥ የሚታዩ ወጪዎች ላይ ቅነሳዎችን የመለየት ኃላፊነት የተሰጠውን የመንግስት ቅልጥፍና (ዶጅ) ተብሎ የሚጠራውን ተቋም እንዲመራ ተሾመ። ከትራምፕ ጋር የነበራቸው ውዝግብ የጀመረው በግንቦት ወር አስተዳደሩን ለቅቆ በወጣበት ጊዜ እና የትራምፕን ግብር እና የወጪ ዕቅዶችን በይፋ መተቸት ሲጀምር ነው። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ትልቅ ቆንጆ" ሲሉ በይፋ የሰየሙት ረቂቅ በጀታቸው በአገሪቱ በምክር ቤት ጸድቋል። ሕጉ ከፍተኛ ወጪን እና የግብር ቅነሳን ያካተተ ሲሆን በአሜሪካ በጀት ላይ በሚቀጥሉት አስርት ዓመታት ውስጥ ከሦስት ትሪሊየን ዶላር በላይ ጉድለት እንደሚያስከትል ተገምቷል። በኤሌክትሪክ የሚንቀሳቀሱ መኪኖችን የሚያመርተው ግዙፉ ቴስላ ባለቤት የሆነው መስክ የትራምፕ ሕግ በአረንጓዴ ሽግግር ላይ ወይም እንደ ቴስላ ላሉ ምርቶች ድጎማ ማድረግ ላይ አያተኩርም ሲል ይተቻል። ትራምፕ በዚህ ሳምንት በማኅበራዊ ድረ ገጻቸው ትሩዝ ሶሻል ላይ "ኤሎን በታሪክ ውስጥ ከየትኛውም የሰው ልጅ የበለጠ ድጎማ ሊያገኝ ይችላል" ሲሉ ጽፈዋል። "ያለ ድጎማ ኤለን ምናልባት ሱቁን ዘግቶ ወደ አገሩ ደቡብ አፍሪካ መመለስ ይኖርበታል።" ትራምፕ የቢሊየነሩን ሌሎች ንግዶችን በመጥቀስ ለመስክ ኩባንያዎች የሚደረጉ ድጎማዎችን እንዲመለከት የቅልጥፍና ቢሮውን እንደሚያዙ ዝተዋል። በተጨማሪም መስክ ለአሜሪካ መንግሥት ሮኬቶችን የሚያመጥቀውን ስፔስ ኤክስ እና ለአሜሪካ እና አውሮፓ የመከላከያ ኃይሎች የሳተላይት አገልግሎት የሚሰጠውን ስታርሊንክ ባለቤት ነው። Via:- BBC @Yenetube @Fikerassefa
17 206
5
ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የአንድ ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት ተፈራረሙ! ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የአንድ ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት ተፈራርመዋል።ስምምነቱ ሀገሪቱ እያካሄደች ላለው
ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የአንድ ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት ተፈራረሙ! ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የአንድ ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት ተፈራርመዋል።ስምምነቱ ሀገሪቱ እያካሄደች ላለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ሁሉን አቀፍ እድገትን ለመደገፍ የተደረገ ነው ተብሏል። ስምምነቱ የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።የድጋፍ ስምምነቱ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ስምምነቱ የፋይናንስ ሴክተሩ መረጋጋትን ለማረጋገጥ፣ የንግድ ተወዳዳሪነትን ለማጎልበት፣ የሀገር ውስጥ ሃብት ማሰባሰብን ለማጠናከር፣ ግልፅ እና ውጤታማ የመንግስት ሴክተር አስተዳደርን ለማስፈን እና የማህበራዊ አገልግሎቶችን ዘላቂነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተነግሯል። @YeneTube @FikerAssefa
10 225
6
እንጦጦ ላይ ያሉ ባህር ዛፎች ሙሉ በሙሉ ይነሳሉ ተባለ! በአዲስ አበባ ተራራማ ቦታ በእንጦጦ ላይ የሚገኙት ባህር ዛፎች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንደሚነሱ እና በሀገር በቀል ዛፎች እ
እንጦጦ ላይ ያሉ ባህር ዛፎች ሙሉ በሙሉ ይነሳሉ ተባለ! በአዲስ አበባ ተራራማ ቦታ በእንጦጦ ላይ የሚገኙት ባህር ዛፎች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ እንደሚነሱ እና በሀገር በቀል ዛፎች እንደሚተኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ገልጸዋል። ባህር ዛፍ ውሃ የመምጠጥ አቅሙ ከፍተኛ ስለሆነ እና መዲናዋ የከርሰ ምድርን ውሃ በአግባቡ ለመጠቀም እየሠራች በመሆኑ ዛፎቹን መተካት አንዱ መፍትሔ መሆኑን ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል። ባህር ዛፎቹ ሲነሱ ግን በእጥፍ በሀገር በቀል ዛፎች እና ስነ ምህዳሩን ለማስተካከል በሚችሉ ዛፎች እየተተኩ መሆኑንም መገረለጻቸውን ኤ ኤም ኤን ዘግቧል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከተጀመረ ወዲህ ከእንጦጦ ተነስተው ወደ መሀል ከተማ የሚፈሱት ወንዞች የውሃ መጠን መጨመሩንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡በእንጦጦ ፓርክ ከሚገኙ የዛፍ አይነትቶች ባህር ዛፍ አብዛሃኛው ቦታ ይሸፍናል። ይህ ደግሞ ለሥነ-ምህዳር ተስማሚ እንዳልሆነ በብዙ ሳይንሳዊ ጥናቶች የተረጋገጠ በመሆኑ፤ በአሁኑ ሰዓት በከተማዋ እየተካሄደ ካለው የወንዞች መልሶ ማቋቋም ፕሮጀክት ትግበራ ጋር ተሳስሮ ባህር ዛፍን በአገር በቀል ዝርያዎች ለመተካት እየተሰራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች አስተዳደር ኮርፖሬሽን አስታውቋል።በዚህም መሠረት በፖርኩ የሀበሻ ጽድ፣ ዝግባ፣ ወይራ የመሳሰሉት አገር በቀል ዛፎች ባህር ዛፍን እንዲተኩ እንደሚደረግ ተነግሯል። Via AMN @YeneTube @FikerAssefa
10 692
7
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ሀገራቸው ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር ያላትን ግንኙነት የሚያቋርጠውን ሕግ ፈረሙ * የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ኢራን ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀን+2
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ሀገራቸው ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር ያላትን ግንኙነት የሚያቋርጠውን ሕግ ፈረሙ * የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ኢራን ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማቋረጥ ያስችላታል የተባለውን ሕግ አጽድቀዋል። የኢራን ፓርላማ ከሳምንት በፊት ባደረገው ስብሰባ ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ በኢራን ላይ ጫና እያሳደረ ነው፤ ይህን ደግሞ ኢራን መታገስ የለባትም፤ ከዚህ ተቋም አባልነት ለመውጣት ጊዜው አሁን ነው በማለት ሕግ አጽድቆ ወደ ፕሬዚዳንቱ ልኮ ነበር። ፕሬዚዳንቱ በዛሬው ዕለት ከዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር ኢራን የምታደርገውን ትብብር እንደታቋርጥ ፓርላማው ያቀረበውን ሰነድ መፈረማቸውን አስታውቀዋል። ኢራን እዚህ እርምጃ ላይ የደረሰችው እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ ኤጀንሲው ባሳየው ቸልተኝነት እና ተገቢውን ሽፋን ባለመስጠቱ ነው ተብሏል። ኢራን የኒውክሌር የጦር መሳሪያ ባለቤት ልትሆን ነው፤ ይህን እውን ለማድረግ የሚያስችላትን ዩራኒየም እያበለፀገች ነው በሚል እስራኤል እና አሜሪካ የኢራንን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫዎችን አጥቅተዋል። ኢራን በበኩሏ የተለያዩ ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል እና በመካከለኛው ምስራቅ ወደሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች አስወንጭፋለች።   T.me/ethio_mereja         ኢትዮ-መረጃ
23 402
8
ኢትዮጵያ ወደ ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል መላክ ጀመረች! ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ወደ ታንዛኒያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል በሙከራ ደረጃ መላክ መጀመሯ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ
ኢትዮጵያ ወደ ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል መላክ ጀመረች! ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ወደ ታንዛኒያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል በሙከራ ደረጃ መላክ መጀመሯ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለፁት፤ የሁለቱ ሀገራት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ስምምነቱ ከተፈረመ የተወሰኑ ወራት ተቆጥረዋል። በዚህም መሰረት አሁን ላይ በኢትዮጵያ በኩል 200 ሺህ ሜጋ ዋት ድረስ የመሸከም አቅም ያለው የማስተላለፊያ መስመር ተሰርቷል ብለዋል።አሁን በመስመሩ እየተላለፈ ያለው 200 ሜጋ ዋት መሆኑን በመጥቅስ፤ መስመሩ ተጨማሪ ግንባታ ሳይከናወን ተጨማሪ ኃይል ማስተላለፍ እንደሚችል ተናግረዋል። ሙከራው በሂደት ላይ ያለ ነው ያሉት አቶ ሞገስ፤ በይፋ የኤሌክትሪክ ሽያጭ እንዳልተጀመረ ተናግረዋል።የኃይል ልማት ትስስሩ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት ለሌሎች ሀገራት ጭምር ሞዴል የሚሆን ሥራ እየሰራች መሆኑን የሚያመለክት መሆኑን አንስተዋል። ሀገሪቱ ያላትን ሀብት ለራሷ ብቻ ሳይሆን በዙሪያው ከሚገኙ ጎረቤቶቿ ጋር የጋራ ተጠቃሚነትን አረጋግጣ በጋራ የማልማት ፍላጎት ያላት ሀገር መሆኗን የሚያሳይ ነውም ብለዋል። የኬንያ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ኢንጂነር ጆን ማቲቮ ኤምቢኤስ በማህበራዊ ሚዲያ ገፃቸው እንዳስታወቁት፤ በሙከራው የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ኤሌክትሪክ የማስተላለፊያ መስመር በተሳካ ሁኔታ ኤሌክትሪክ ማስተላለፍ መቻሉን ተናግረዋል። Via Gazeta+ @YeneTube @FikerAssefa
13 245
9
ኢራን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስጠነቀቀች የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መሪዎች ላይ የሚያስተላልፉትን አሉታዊ መልዕክት እንዲያቆሙ ኢራን አስጠነቀቀች። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስት
ኢራን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስጠነቀቀች የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መሪዎች ላይ የሚያስተላልፉትን አሉታዊ መልዕክት እንዲያቆሙ ኢራን አስጠነቀቀች። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰይድ አባስ አራቅቺ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው የሚያሰፍሩት መልዕክት ክብረ-ነክ አገላለፅ የተሞላበት ነው ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ በተለይም የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ሆሚኒን በተመለከተ የሚያስተላልፉትን መልዕክት ጠብአጫሪ ነው ሲሉ ነው የገለፁት። የፕሬዚዳንት ትራምፕ የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ተገቢነት የጎደለው ነው ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ የቋንቋ አጠቃቀማቸውን ሊያሻሽሉ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ አያቶላህ አሊ ሆሚኒን በተመለከተ የሚያሰራጩትን መልዕክት የማያስተካክሉ ከሆነ እየተካሄደ ባለው ድርድር ስምምነት ላይ መድረስ አይቻልም ነው ያሉት።ጠንካራ ሀገረ መንግሥት እንዲሁም ሥራ ወዳድ እና የራሱ ባህል ያለው ህዝብ ባለቤት የሆነችው ኢራን ክብሯ ሊነካ አይችልም ሲሉም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰይድ አባስ አራቅቺ ስለመናገራቸው ዥንዋ ዘግቧል። @Addis_Mereja
12 406
10
Q
5 776
11
" የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል " - ሚኒስቴሩ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ። የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የ
" የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል " - ሚኒስቴሩ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ። የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል። ሚኒስቴሩ የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስቧል። @Addis_Mereja
14 054
12
ነዳጅ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017
ነዳጅ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጥብቅ ያሳስባል፡፡ Via:- አዩዘበሀሻ @Addis_Mereja
18 874
13
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል። መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል። ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል። ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል። ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል። ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል ሲል ካፒታል ዘግቧል ። @Addis_Mereja
17 074
14
በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙ በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸውን አ
በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙ በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸውን አናዶሉ እና የኢራን የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል። እስራኤል ከሰኔ 13 ጀምሮ የኢራን የጦር ጀኔራሎችን መግደሏን ያስታወቀች ሲሆን፤ ሦስቱ የኢራን የጦር መሪዎች በትናንትናው ዕለት ኢራን የድል በዓሏን ስታከብር ከህዝቡ ጋር በመገኘት አክብረዋል ብለዋል ምንጮቹ። ከዚህ ውስጥ አንዱ የሆኑት የእስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፕስ ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኢል ቃኣኒ በዓሉን ከሕብ ጋር ማክበራቸውን የኢራቅ የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል። በኢራን ታስኒም የዜና አገልግሎት የተለጠፈ ቪዲዮ ቃአኒ በዝግጅቱ ላይ ከተሰበሰቡት መካከል አሳይቷል። በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ቃአኒ በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት የኢራን ጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ዘግቦ እንደነበር የሚታወስ ነው። በተመሳሳይ የወቅቱ የመከላከያ ሚኒስትር እና የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩ ብርጋዴር ጄኔራል አዚዝ ናስርዛዴህ በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ በመከላከያ ሚኒስቴር ላይ በተፈፀመ የአየር ጥቃት ተገድለዋል ተብለው የነበረ ቢሆንም በሕይወት እንዳሉ እና አሁንም በስልጣን ላይ እንደሚገኙ ተስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል። የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የደህንነት ዋና አማካሪ አድሚራል አሊ ሻምካኒ እ.ኤ.አ ሰኔ 13 ቀን 2025 በእስራኤል የአየር ጥቃት መሞታቸው ከተነገሩት አንዱ የነበሩ ናቸው። አድሚራል አሊ ሻምካኒ በድል በዓሉ ላይ በመገኘት የድል በዓሉን አክብረዋል ሲሉ የኢራን የዜና ወኪሎች ዘግበዋል። @Addis_Mereja
16 170
15
በአማራ ክልል ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማት ከሥራ እየወጡ መሆኑ ተገለጸ! በአማራ ክልል በግንባታው ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ተቋማት አብዛኞቹ በክልሉ በሚስተዋልው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከሥራ እየወጡ መሆኑን የክልሉ ኮንስርታክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር ለአሐዱ ገልጿል፡፡በክልሉ ከ3 ሺሕ በላይ ተቋማት በግንባታው ዘርፍ ለመንቀሳቀስ ፈቃድ አውጥተው ይሰሩ እንደነበር የገለጸው ማህበሩ፤ በማህበሩ ሥር ደግሞ ከ765 በላይ ተቋማት እንደነበሩ አስታውቋል፡፡ "ነገር ግን ክልሉ ላይ በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ፤ አብዛኞቹ ጨረታዎች ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች የሚሰጡ በመሆናቸው ብዙዎቹ በአቅም ማነስ ምክንያት ከዘርፉ እየወጡ ነው" ሲሉ የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ሙሉቀን ቢተው ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡"ችግሩን ለማስተካከል ይመለከታቸዋል የተባሉ አካላትን ጠይቀናል ነገር ግን ምንም መፍትሄ ማግኘት አልተቻለም" ያሉት አቶ ሙሉቀን፤ በእዳ ምክንያት ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ንብረቶቻቸውን ያጡ እንዲሁም ከዘርፉ የወጡ እና ሌላ ዘረፍ የቀየሩም ባለሙያዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡ "አሁን ላይ በክልሉ ከሚሰሩት የግንባታ ሥራዎች ውስጥ በግብረ-ሰናይ ድርጅቶች የሚመጡ ግንባታዎች ብቻ በግሉ ዘርፍ እየተሰሩ ነው" ብለው፤ ነገር ግን ይህ ለሁሉም የሚዳረስ እና ሰፊ ባለመሆኑ ችግሩ ባለሙያዎቹ ሥራ እንዲያጡ ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል፡፡የማህበሩ ፕሬዝደንት "በግንባታው ዘርፍ ተሰማርተው የነበሩና በአሁኑ ወቅት ከሥራ የወጡ ተቋማት ምን ያህል ናቸው?" ሲል አሐዱ ላቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ከዘርፉ ለመውጣታቸው የጸጥታቸው ችግር እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያለ ጨረታ የሚወስዷቸው ፕሮጀክቶች መብዛት ዋና ምክንያቶች ናቸው ተብሏል፡፡ Via Ahadu @Addis_Mereja
13 651
16
ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ባሉ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የበልስቲክ ሚሳይል መተኮስ ጀምራለች። በዚህም በካታር እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ያሉ የጦር ሰፈሮች ኢላማ እንደተደረጉ ሲነገር የአሜሪ
ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ባሉ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ የበልስቲክ ሚሳይል መተኮስ ጀምራለች። በዚህም በካታር እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ያሉ የጦር ሰፈሮች ኢላማ እንደተደረጉ ሲነገር የአሜሪካ የሚሳይል መከላከያዎች መደረጋቸው ታውቋል። @Addis_Mereja
15 311
17
ኢትዮጵያ በኑሮ ውድነት ከአፍሪካ ቀዳሚ ደረጃ መያዟን ሪፖርት አመላከተ ኢትዮጵያ ለመኖር እጅግ ውድ ከሆኑ የአፍሪካ ሀገሮች መካከል ቀዳሚ ደረጃ ስትይዝ ከዓለም 53ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ሪፖርት አመ
ኢትዮጵያ በኑሮ ውድነት ከአፍሪካ ቀዳሚ ደረጃ መያዟን ሪፖርት አመላከተ ኢትዮጵያ ለመኖር እጅግ ውድ ከሆኑ የአፍሪካ ሀገሮች መካከል ቀዳሚ ደረጃ ስትይዝ ከዓለም 53ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ሪፖርት አመላከተ። የዓለማችን ትልቁ የኑሮ ውድነት የመረጃ ቋት ባወጣው አዲስ ሪፖርት እንዳስታወቀው፤ ኢትዮጵያውያን አሁን ላይ እንደ ምግብ እና ትራንስፖርት ባሉ መሰረታዊ ነገሮች ላይ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ዜጎች የበለጠ ገንዘባቸውን ያወጣሉ። በሪፖርቱ መሰረት፣ በኑሮ ውድነት ኢትዮጵያ ከዓለም 53ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው 46.5 የኑሮ ውድነት ጠቋሚ ነጥብ በመስመዝገብ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ ውስጥ ካሉ አገሮች ሁሉ ከፍተኛው ነው። በሀገሪቱ የሚታየው የሸቀጦች ዋጋ መወደድ በኑሮ ውድነት ደረጃ አንደኛ እንድትሆን ምክንያት መሆኑ ተገልጿል። ይህም በተለይ በቋሚ ወይም በዝቅተኛ ገቢ የሚኖሩ ሰዎች ሳምንታዊ ወጪያቸውን ለመሸፈን እየከበዳቸው መምጣቱን የሚያሳይ ነው መባሉን ኤፒኤ ኒውስ ዘግቧል።  @Addis_Mereja
22 490
18
ኢራን ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ ቅሬታ አቀረበች! ቢቢሲ እንደዘገበው፤ ኢራን፣ እስራኤል በኒውክሌር ማበልጸጊያዎቿ ላይ እየፈጸመችው ያለውን ጥቃት በተመለከተ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤነር
ኢራን ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ ቅሬታ አቀረበች! ቢቢሲ እንደዘገበው፤ ኢራን፣ እስራኤል በኒውክሌር ማበልጸጊያዎቿ ላይ እየፈጸመችው ያለውን ጥቃት በተመለከተ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ቅሬታ አቀረበች። እስራኤል “በኒውክሌር ማዕከላት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን የሚከለክሉ አለም አቀፍ ህጎችን በጣሰ መልኩ ጥቃቶችን መፈጸሟን ቀጥላለች” ስትል ኢራን ለኤጀንሲው ከስሳለች። በዛሬው ዕለት እስራኤል አገልግሎት በማይሰጠው በአራክ የኒውክሌር ማብላያ እንዲሁም የናታንዝ የኒውክሌር ማበልጸጊያ ተቋም ጥቃት መፈጸሟ ተገልጿል። ኤጀንሲው በአራክ የኒውክሌር ይዞታ ላይ በደረሰው ጥቃት በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለም ገልጿል። @Addis_Mereja
18 410
19
ትራምፕ ኢራን "ያለ ቅድመ ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ" ጠየቁ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኔይ የት እንደሚገኙ በትክክል እንደሚያውቁም ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ዩናይትድ ስቴ
ትራምፕ ኢራን "ያለ ቅድመ ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ" ጠየቁ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የኢራኑ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኔይ የት እንደሚገኙ በትክክል እንደሚያውቁም ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ዩናይትድ ስቴትስ እርሳቸውን "ለጊዜውም ቢሆን" ለማጥፋት ፍላጎት እንደሌላት ተናግረዋል። ትራምፕ የኢራን አየር ክልል ሙሉ በሙሉ በአሜሪካ ቁጥጥር ስር መዋሉንም አስታውቀዋል። ትራምፕ የኢራን መሪን ለአሁኑ 'የመግደል እቅድ' የለንም ብለዋል ። ዶናልድ ትራምፕ "እኛ" የኢራንን ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኔን አንገድልም - "ቢያንስ ለጊዜውም ቢሆን" ብለዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አያቶላህ የት እንዳሉ በትክክል እናውቃለን "ቀላል ኢላማ ነው " በማለት ገልጸዋል። ነገር ግን "ትዕግሥታችን በጣም ጠባብ ነው" ሲሉ አስጠንቅቀዋል ያለው ቢቢሲ ነው። እስራኤል ኢራንን ማጥቃት ከጀመረች ከአምስት ቀናት በኋላ ሁለቱም ወገኖች እርስ በርስ መታኮሳቸውን ቀጥለዋል ። ኢራን ማምሻውን በቴል አቪቭ እና ሃይፋ ያሉ ሰዎችን ለቀው እንዲወጡ አስጠንቅቃለች። ብዙ ኢራናውያን ቴህራንን ለመሸሽ እየሞከሩ መሆኑ ተዘግቧል። @Addis_Mereja
16 535
20
እየተወሳሰበ የመጣው የቀይ ባህር ጉዳይ ከደቂቃዎች በፊት የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን በአወጣው መረጃ ኢራን ኢትዮጵያን በቀጥታ አደጋ ውስጥ ሊከት የሚችለውን እርምጃ ወስዳለሁ ስትል ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች
እየተወሳሰበ የመጣው የቀይ ባህር ጉዳይ ከደቂቃዎች በፊት  የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን በአወጣው  መረጃ  ኢራን ኢትዮጵያን በቀጥታ አደጋ ውስጥ ሊከት የሚችለውን እርምጃ ወስዳለሁ ስትል ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች። በዚህም መሰረት ኢራን "እስራኤልን እንዳላጠቃ ለመከላከል የሚሞክሩትን   አሜሪካ ፣ዩኬ፣ የኢዩ ሀገራትን  ወታደራዊ ጣቢያዎችንና መርከቦቻቸውን  በቀጥታ ማጥቃት እጀምራለሁ"  ስትል  ይፋዊ  መግለጫ የሰጠች ሲሆን ፤እንደሚታወቀው  ሁሉም የተጠቀሱት ሀገራት የወታደራዊ ጣቢያና ባህር ሃይላቸው በአንድ ላይ ተከማችተው  የሚገኙት እና የሚተላለፉባት የበሬ ግንባር የምታክለውና የ120 ሚሊየን ኢትዮጵያዊያን  ህልውና የኪራይ ወደባችን  በሆነችው ጂቡቲ  ነው።  ኢራን እንዳለችውምበ ጅቡቲ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር ቤዝ  ለማጥቃት በቀጥታ የጦር ቀጠና ምታደርጋት ከሆነ  ያለ አንዳች ጥርጥር ሀገራችን  ከዚህ ቀድም ባህር በር በማጣታችን  ስንፈራው የነበረውን ከባድ አደጋ ይዞ ይመጣል። @Addis_Mereja
19 597