en
Feedback
ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️

ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️

Open in Telegram

መጽሐፍትን በጥሩ ዋጋ እንገዛለን እንሸጣለን! ገፁን ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን ያስፉት 📚📚 አድራሻችን አዲስአበባ 0991001450

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️

Channel ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️ (@bookworlds1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 10 532 subscribers, ranking 3 627 in the Books category and 3 156 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 532 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -102 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 17.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 816 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 21.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
መጽሐፍትን በጥሩ ዋጋ እንገዛለን እንሸጣለን! ገፁን ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን ያስፉት 📚📚 አድራሻችን አዲስአበባ 0991001450

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Books category.

10 532
Subscribers
-524 hours
-207 days
-10230 days
Posts Archive
እንጃ ምን እንደሆንኩ ፣ አላውቅም ዘንድሮ፣ ዶሮ ዶሮ አይሸትም ፣ የእማምዬ ጓሮ፣ ጠጅ ጠጅ አይሸትም ፣ ያባብዬ ደጅ፣ እንደሀገር ሰክሬ ፣ ተንገዳገድኩ እንጅ። መቆምና መውደቅ ፣ መሔድ እስኪያቅተኝ
እንጃ ምን እንደሆንኩ ፣ አላውቅም ዘንድሮ፣ ዶሮ ዶሮ አይሸትም ፣ የእማምዬ ጓሮ፣ ጠጅ ጠጅ አይሸትም ፣ ያባብዬ ደጅ፣ እንደሀገር ሰክሬ ፣ ተንገዳገድኩ እንጅ። መቆምና መውደቅ ፣ መሔድ እስኪያቅተኝ ከእማምዬ ጓሮም ካባብዬ ደጅም ፣ ባሩድ ነው ሚሸተኝ ። እንጃ ምን እንደሆንኩ ፣ ምንድነው ችግሩ፣ ባሩድ ባሩድ ብቻ ፣ ሚሸተኝ ምድሩ፣ አፍንጫዬ ታሟል ፣ ወይ ታሟል ሀገሩ። ይህ በእንዲህ እንዳለ... ላዲስ ዓመት ብስራት ፣ መድፍ ለመተኮስ፣ ሮኬት ለማፈንዳት ፣ ርችት ለመለኮስ፣ "እንዳትደነግጡ" የሚል ሀሳብ ያለው ፣ መግለጫ ይወጣል። የለመዱት ነገር ፣ ምን ያስደነግጣል? በላይ በቀለ ወያ✍️

"ትልቅ አደራ ተሸክሜ መጥቻለሁ!" እኔ ወንድማችሁ ከ ደብረ ታቦር ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ጉባኤ ቤት ይሄንን ታላቅ ሀላፊነት ተጥሎብኛልና እናንት ውድ ወዳጆቼ ለእኔ ስትሉ ሳይሆን ለጉባኤ ቤቱ ስትሉ መ
"ትልቅ አደራ ተሸክሜ መጥቻለሁ!" እኔ ወንድማችሁ ከ ደብረ ታቦር ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ጉባኤ ቤት ይሄንን ታላቅ ሀላፊነት ተጥሎብኛልና እናንት ውድ ወዳጆቼ ለእኔ ስትሉ ሳይሆን ለጉባኤ ቤቱ ስትሉ መጽሐፍትን በመለገስ እንድትተባበሩ በትህትና እጠይቃለሁ። ማንኛውም ዓለማዊም ሆነ መንፈሳው መጽሐፍትን መለገስ ይቻላል! በእኔ በኩል 25 መጽሐፍትን በመለገስ የምጀምር ሲሆን የለገስኳቸውን መጽሐፍት በቀጣይ እስከምለጥፋቸው ቀድሞ የሚለግስ እጁን ያውጣልኝ! አንብባችሁ ያስቀመጣችኋቸውን ማንኛውም መጽሐፍቶች መለገስ ትችላላችሁ! የንባብ ባህልን በማበረታታት አስተዋይ ትውልድ እንፍጠር! 0991001450 ደውሉ ወይም ከታች ያለውን user name ተጠቀሙ።

የኢትዮጵያ የመካከለኛው ዘመን ታሪክ ብዙ ነገር የታየበትና የተከናወነበት ዘመን ነው። የዛጉዌ ስርዎ መንግስት አክትሞ አፄ ይኩኖአምላክ የሰሎሞንን ስርዎ መንግስት እንደገና ሲያስነሳው ብዙ የታሪክ ሁነ
የኢትዮጵያ የመካከለኛው ዘመን ታሪክ ብዙ ነገር የታየበትና የተከናወነበት ዘመን ነው። የዛጉዌ ስርዎ መንግስት አክትሞ አፄ ይኩኖአምላክ የሰሎሞንን ስርዎ መንግስት እንደገና ሲያስነሳው ብዙ የታሪክ ሁነቶች ተከስተዋል። ይህ ዘመን አምደ ፂዮን የገነነበት፣ አፄ ዘረያዕቆብ ጠንካራ መንግስት የመሰረተበት የግራኝ አህመድ እንቅስቃሴ የተጀመረበት እና የሀገራችን ዋነኛው የታሪክ ምዕራፍ ነው። ታሪኩም በዚህ መጽሐፍ ተሰንዷል። መጽሐፉ የኢትዮጵያን መካከለኛ ዘመን ታሪክ ታላቅነትና ውጣ ውረድ በጥልቀት የሚመረምር ድንቅ የታሪክ ሰነድ ሲሆን፣ በተለይም ከአፄ ይኩኖ አምላክ የሰሎሞናዊው ሥርወ-መንግሥት መነሳት ጀምሮ እስከ አፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥት ድረስ ያለውንና በሀገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ሃይማኖታዊ እንዲሁም ባህላዊ መስተጋብሮች ላይ ከፍተኛ አሻራ ያሳረፈውን ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ በዝርዝር የሚተርክ ስራ ነው። መጽሐፉ በእነዚህ ታላላቅ ነገሥታት ዘመን የተከናወኑትን የሀገር አንድነት ግንባታ ጥረቶች፣ የውስጥ ለውስጥ የሥልጣን ሽኩቻዎችን፣ ከውጭ ኃይሎችና ጎረቤት መንግሥታት ጋር የነበሩትን ዲፕሎማሲያዊና ወታደራዊ ግንኙነቶች፣ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ዘመናዊ መልክ መፈጠር መሠረት የሆኑትን ታሪካዊ ክስተቶች ትውልድ ሊገነዘባቸው በሚችል መልኩ አቀናጅቶ ይዟል። ባጠቃላይ፣ መጽሐፉ የኢትዮጵያን የጥንት ሥልጣኔ ማማ፣ የሉዓላዊነትና የጽናት ጉዞን እንዲሁም የአባቶቻችንን ጥበብና ጀግንነት በውብ የአማርኛ ሥነ-ጽሑፍ ስልት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይና ለማንኛውም የታሪክ አሳሽ የማይተካ የእውቀት ምንጭ ነው። @a9OaG @a9OaG

በሀገራችን ወርቃማ የስነጽሑፍ ዘመን የሚባለው የደርግ ዘመን ነው። ምክነያቱም አብዛኞች የስነ ጽሑፍ ስራዎች የታተሙትና የተፃፉት በዚያ ዘመን ነበርና። በአንፃሩ የአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን የተለያዩ የታሪ
በሀገራችን ወርቃማ የስነጽሑፍ ዘመን የሚባለው የደርግ ዘመን ነው። ምክነያቱም አብዛኞች የስነ ጽሑፍ ስራዎች የታተሙትና የተፃፉት በዚያ ዘመን ነበርና። በአንፃሩ የአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት የተፃፉበትና ጥቂት የልቦለድ ስራዎችም ብቅ ብቅ ያሉበት ዘመን ነው። በዚህ ዘመን በጣም ገነው ከወጡ መጽሐፎች መካከል ደግሞ አንዱ ይህ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ በፊውዳሉ ዘመን በነበረው የባላባት መደብ እና የድህነት ግንብ መካከል የተቀሰቀሰውን፣ በሀብታሟ እመቤት በሰበለወንጌል እና በምስኪኑ ቄስ-ተማሪ በበዛብህ መካከል የበቀለውን ፍጹም፣ ንጹሕ እና መሥዋዕትነት የተሞላበትን የፍቅር ነበልባል ይተርካል። ፍቅር ከሞቀ ከደመቀ ቤት አስወጥቶ በበረሃ የሚያስመንን አደገኛ ኃይል እንደሆነ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ያች አበባ የመሰለች ሰብለወንጌል ከበዛብህ ጋር ያጣበቃት ፍቅር ከባድ ነውና አለምን አስትቶ አስመንኗታል። ምናኔዋ ግን ከዓለም ርቆ ወደ አለሟ የሚወስድ ምኞት እንጅ ጽድቅን ፍለጋ አልነበረም። መጽሐፉ ፍቅርን በንዑስ ጭብጥነት ያነሳል እንጅ ዋና ሀሳቡ የዘመኑን የፊውዳል ስርአትና የማህበረሰቡን ወግና ባህል እንዲሁም ሐይማኖት ማስተማር ነው። ይህ መጽሐፍ በአብዛኛው ኢትዮጵያን ዘንድ የሚታወቅ በብዙዙዎች የተነበበ ከመነበብም በዘለለ ወጋየሁ ንጋቱ በሚያምር ድምጹ የተረከልን ፤ ቴዎድሮስ ካሳሁንም በሙዚቃ መልክ ያስደመጠን ምርጥ መጽሐፍ ነው። እስኪ ስለ መጽሐፉ የተሰማችሁን የሆነ ነገር ፃፉ!

ግጥም ማለት ቤት መምታት ማለት ነው ብሎ የሚያስብ ሰው ይህችን መጽሐፍ እንዲያነባት አልመክርም። ግና "ግጥም ማለት የሰው ልጅ የውስጥ ማንነትና የትዝታ ጉዞ በጥልቀት የሚፈተሽበት፣ የቋንቋ ውበትና የ
ግጥም ማለት ቤት መምታት ማለት ነው ብሎ የሚያስብ ሰው ይህችን መጽሐፍ እንዲያነባት አልመክርም። ግና "ግጥም ማለት የሰው ልጅ የውስጥ ማንነትና የትዝታ ጉዞ በጥልቀት የሚፈተሽበት፣ የቋንቋ ውበትና የፍልስፍና ምስጢር የተዋሃዱበት ድንቅ የጥበብ ነው።" ብላችሁ ለምታምኑ ታነቧት ዘንድ ጋበዝኳችሁ! ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር! 0991001450

እንደምንም ሌሊቱ በጭንቀት ነጋለት...በጧት ተነስቶ በተራዋ ብቅ ያለችውን ፀሀይ እያየ ተደመመና በሚገርም ሁኔታ አሳምሮ ሳላት። ሽማግሌውን የማያገኝበት መንገድ ሲያሰላስል ስዕሎችን ወደ ገበያ ይዞ መሄድ እንዳለበት ተገነዘበ ። በጧት ተነስቶ የሳላቸውን ስዕሎች ይዞ ወደ ገበያ ሄደ። አንድ በእድሜ ገፋ ያለች ሴትዮ አንገቷ ላይ የሚያምር ወርቅ አድርጋ ወደ ልጁ ቀረበችና ስዕሉን ልግዛህ? አለችው። ሴትዮዋን ሲመለከታት ውስጡን አንዳች ነገር ተሰማው ። እንደውም ከዚህ በፊት የሚያውቃት መሰለው። ስዕሉን አባቴን ልፈልግበት ነው ይዤው የመጣው ላንች አልሸጥም አላት። አባትህ ማነው ስትል ጠየቀችው? ወላጅ አባቴ ንጉስ ነው ። ነገር ግን ህይወቴን የታደገልኝ ሌላኛውን አባቴን እየፈለኩ ነው አላት። ንግግሩ ስላልገባት በደንብ እንዲያስረዳት ጠየቀችው። አንድ ቀን መንገድ ላይ እናቱ አቅፋው ተቀምጣ ሳለ አንድ ንጉስ ላሳድገው ብሎ እንደወሰደው እና  እናቱ ለንጉስ እንደሰጠችውና ከዚያም ከንጉሱ ልጅ ጋር ለአደን ፉክክር እንደወጡ   ከዚያም ተጠፋፍተው  በሽፍቶች ተይዞ  አሁን እስካለው ሁሉንም በዝርዝር ነገራት። ሴትዮዋ ይህንን ስትሰማ እያለቀሰች ነበር። ቀና ብሎ ጉንጯ ላይ የወረዱትን እንባዎች እያየ ምን ሆነሽ ነው ሲል ጠየቃት። ከብዙ አመታት በፊት ከአንድ ከማላውቀው ሰው የወለድኩት ልጅ ነበረኝ። የምበላውና የምጠጣው የሌለኝ ደሃ ነበርኩኝ። መንገድ ላይ ልጁን ይዤ ስለምን አንድ ንጉስ ወደ እኔ መጣ። ልጅሽን ላሳድገው አለኝ። እሺ አልኩት። ብዙ ብርና ወርቅ ሰጥቶኝ ልጄን ወሰደ። ልጄን ሸጥኩት ቢጨንቀኝ ቢጠበኝ የማደርገው ባጣ ልጄን ሸጥኩት። እንባዋን መቆጣጠር አቃታት። አሁን አንተ የነገርከኝን ታሪክ ስሰማ የሸጥኩትን ልጄን እንዳገኜሁት አወኩ።  ብላ እንባዋን ዘረገፈችው። ልጁም የሚሰማውን ማመን ተስኖት በድንጋጤ ተውጦ እያዳመጣት ነው።

እርስዎ አልሳሉትም እባክዎት ይሄንን ስዕል የሳለውን ሰው ይንገሩኝ...እያለች ብትለምናቸውም ልጁ የሰጣቸው ማስጠንቀቂያ ነበርና ሊነግሯት አልፈለጉም። መለመኑ ሲሰለቻት አንድ ሃሳብ መጣላትና ያንን ሀሳብ  መጠቀም ፈለገች። አባቷን ቀለምና ቡርሽ እንዲያስመጣላት ጠየቀችው። አባቷም የምትፈልገውን አይነት ቀለምና ቡርሽ እንዲሁም ለስዕል የሚያገለግል ነገር ሁሉ አስመጣላት። አሁን አለች ልዕልቷ...አሁን እርስዎ ከሆኑ ስዕሉን የሳሉት አለች ወደ ሽማግሌው ዞራ ፣ ፈረሱም ይሄው ሜዳውም ይሄው ...እኔን ይሳሉኝ። እውነትም እኔን በደንብ አድርገው ከሳሉኝ የእስከዛሬዎቹን ስዕሎች እርስዎ እንደሳሏቸው አምናለሁ አለቻቸው። ሽማግሌ ፍርሃት ውስጣቸውን ሲወራቸው ተሰማቸው። በንጉሱ ፊት የዋሹት ታላቅ ውሸት አስደነገጣቸው። ቡርሽና ቀለም ተሰጣቸውና ልዕልቷን እንዲስሉ ታዘዙ። ወትሮውንም አሳ ማስገር እንጂ ስዕል መሳል ሞክረውት የማያውቁት እኒያ መልካም ሽማግሌ ውስጣቸው በፍርሃት ራደ። ለመልካም ብለው ልጁን ማዳናቸው ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስጥልባቸው ተገነዘቡ። በልባቸውም ልጁን ረገሙት። እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስዕሉን ለመሳል ቢሞክሩም አልሆን አላቸው። ንጉሱ በዝምታ ሲመለከታቸው ከቆዬ በኋላ አንድ ትዕዛዝ አስተላለፈ። እጅኛ እግራቸው በሰንሰለት እንዲታሰር አሽከሮቹን አዘዘ። ባላወቁትና ባልጠበቁት መንገድ በሰንሰለት ለመታሰር በቁ። ትክክለኛውን የስዕሉን ባለቤት እንዲናገሩ በአሽከሮች ብዙ ጅራፍ ተገረፉ እሳቸው ግን እውነቱን ለመናገር አልቻሉም። የልጁን ቃል አክብረው ከንጉሱ አሽከሮች ዱላ እና ከንጉሱ ፍርድ የሚመጣውን የመጨረሻውን ውሳኔ መጠባበቅ ጀመሩ። ቀኑ መሽቶ ፀሀይ የምዕራቡን አድማስ ሀምራዊ ቀለም አልብሳ ወደቤቷ ስታሸልብ ጨረቃ በተራዋ ብቅ አለች። የድሃይቱ ልጅ የሽማግሌው ወጥቶ መቅረት አሳስቦታል። ቀኑን ሙሉ ጠብቋቸው ስላልመጡ ውስጡ በፍርሃት እና በጭንቀት ተውጧል። ከሽማግሌው ጎጆ ወጠጥቶ ውጭ ላይ ተቀመጠና በጨረቃዋ ውበት ተመሰጠ። በምስራቅ በኩል ብቅ ያለችው ጨረቃ ልዕልቷን መስላ ታየችው። ቡዝዝ ብሎ ተመለከታት። ከልዕልቷ ጋር ያሳለፈው ጊዜ አንድ በአንድ መጣበት ...ጨረቃዋ ለመሙላት ትንሽ ይጎድላታል። ታራራዎችን ተንተርሳ የወጣችው ጨረቃ ልቡን ወስዳዋለች። ወደ ጎጆዋ ተመልሶ ቡርሽና ቀለም ይዞ ተመለሰ ። ጠረቃዋን ተራራ ተንተርሳ ሳላት። እጅግ ውብ አድርጎ ሳላት። ስዕሉን ይዞ ወደ ጎጆዋ ተመለሰና ጋደም አለ።

ታሪኩን ለማስታወስ ያህል ትረካው የቆመበትን ሁኔታ ላስታውሳችሁ.....ልጁ እየሳለ ለአሳ አጥማጁ ወይም ለሽማግሌው የሚሰጠው ስዕል ልዕልቲቱጋ ደርሶ ነበር። ከዚያም አባቷን ይሄንን ስዕል የሳለውን ሰው አስመጣልኝ ብላው ሰዓሊው ወይም ልዕልቲቱን ከሽፍታዎች አድኖ የወሰዳት ወጣት ሽልማቱን ከባህር ያዳኑት ሽማግሌ እንዲያገኙ ስለፈለገ ወደ ንጉሱ ጥሩ ልብስ አልብሶ ልኳቸው ነበር። ልዕልቷ ደግሞ ሽማግሌውን ስታያቸው ተናዳ እርስዎ አይደሉም የሳሉት የሳለውን ሰው ይንገሩኝ እያለች እየተማፀነቻቸው ነበር ታሪኩ ልባችንን አንጠልጥሎ የቀረው። እኔ በራሴ መንገድ ደፍሬ ቀጥዬበታለሁና ከዚህ በመቀጠል አቀርብላችኋለሁ!

"ሰበዝ" የተሰኜው የአለማየሁ ዋሴ መጽሐፍ ላይ "አልጨረስክልኝም" የተሰኜ ልብ አንጠልጥል የሚያስቀር አንድ ንዑስ ርዕስ አለ! እስኪ ያነበባችሁት የ ❤ ምልክት አሳዩና በራሴ መንገድ የጨረስኩትን ላጋራችሁ!

አባ ታጠቅ ካሳ የቋራው አንበሳ ይህ መጽሐፍ ከሁሉም ስለ አፄ ቴዎድሮስ ከተጻፉ የታሪክ ድርሳናት ሁሉ ልዩ የሚያደርገው፣ የንጉሡን ታሪክ በደረቅ የታሪክ መረጃዎች ብቻ ሳይሆን የነበራቸውን ሕዝባዊ መሠ
አባ ታጠቅ ካሳ የቋራው አንበሳ ይህ መጽሐፍ ከሁሉም ስለ አፄ ቴዎድሮስ ከተጻፉ የታሪክ ድርሳናት ሁሉ ልዩ የሚያደርገው፣ የንጉሡን ታሪክ በደረቅ የታሪክ መረጃዎች ብቻ ሳይሆን የነበራቸውን ሕዝባዊ መሠረት፣ ስሜት እና የነፍስ ትግል በጥልቀት በሚያሳይ ልዩ የአጻጻፍ ስልት የተከተለ መሆኑ ነው። ሌሎች መጻሕፍት ብዙውን ጊዜ ትኩረታቸውን በጦርነቶቻቸው እና በፖለቲካዊ ውሳኔዎቻቸው ላይ ብቻ ሲያደርጉ፣ ይህ መጽሐፍ ግን የአፄ ቴዎድሮስን የኢትዮጵያዊነት ጽኑ ፍቅር፣ መላ ሕይወታቸውን የገዛውን የአንድነት ራዕይ እና ከሕዝባቸው ጋር የነበራቸውን ጥልቅ ትስስር በስሜት ቀስቃሽ ቋንቋ ይተነትናል። በተጨማሪም፣ በመቅደላ ምሽግ ላይ የፈጸሙትን የጀግንነት መስዋዕትነት የኢትዮጵያዊነት ክብር ማኅተም አድርጎ በመሳል፣ አንባቢው የንጉሡን የታሪክ ጉዞ በቅርበት እንዲረዳና የእውነት ስሜቱ እንዲቀሰቀስ የሚያደርግ በመሆኑ ከማንኛውም ስለ ቴዎድሮስ ከተጻፈ መጽሐፍ በላይ በእውነተኛ ታሪካዊና ስነ-ጽሑፋዊ ዋጋው ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። 0991001450 @a9OaG

ይህ መጽሐፍ በታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት የተጻፈ ሲሆን በኢትዮጵያ የመካከለኛው ዘመን ታሪክ ውስጥ በሃይማኖት (በቤተ ክርስቲያን) እና በፖለቲካዊው ሥልጣን (በመንግሥት) መካከል የ
ይህ መጽሐፍ በታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት የተጻፈ ሲሆን በኢትዮጵያ የመካከለኛው ዘመን ታሪክ ውስጥ በሃይማኖት (በቤተ ክርስቲያን) እና በፖለቲካዊው ሥልጣን (በመንግሥት) መካከል የነበረውን ጥልቅና ውስብስብ ግንኙነት የሚመረምር እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ የምርምር ሥራ ነው። መጽሐፉ ትኩረት የሚያደርገው የአክሱም ሥርወ-መንግሥት ካበቃ በኋላ የሰለሞናውያን ሥርወ-መንግሥት በዓፄ ይኩኖ አምላክ አማካኝነት በ1270 ዓ.ም. ዳግም ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ፣ በግራኝ አህመድ ወረራ ምክንያት አጠቃላይ የአገሪቱ መዋቅር እስከ ተናወጠበት 1527 ዓ.ም. ባለው ወርቃማና ፈታኝ ዘመን ላይ ነው። በዚህ ዘመን የነበሩት ነገሥታት (በተለይም እንደ ዓፄ ዓምደ ጽዮን እና ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ያሉ ጠንካራ መሪዎች) ግዛታቸውን ወደ ደቡብና ምስራቅ ለማስፋፋት፣ ሕዝቡን አንድ ለማድረግና ማዕከላዊ ሥልጣናቸውን ለማጠናከር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ዋና የመንፈሳዊ፣ የባህልና የፖለቲካ መሣሪያ እንደተጠቀሙባት መጽሐፉ በስፋት ይተነትናል። በተያያዥም ቤተ ክርስቲያን በአገሪቱ የትምህርት፣ የሥነ-ጽሑፍና የስምሪት ማዕከል በመሆን ያበረከተችውን አስተዋጽኦ፣ ከመንግሥት የምታገኘውን የርስት (የጉልት) መሬትና የሀብት ጥገኝነት፣ እንዲሁም አልፎ አልፎ በመንፈሳዊ መሪዎች (እንደ ደብረ ሊባኖስ ገዳማውያን) እና በነገሥታቱ መካከል በሃይማኖታዊ ሥርዓቶችና በሥነ-ምግባር ጉዳዮች ላይ ይፈጠሩ የነበሩትን መካረሮችና የሥልጣን ሽኩቻዎች በብራና ምንጮችና በነገሥታት ገድላት ተደግፎ በዝርዝር ያሳያል። በአጠቃላይ መጽሐፉ ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት እርስ በእርስ እየተደጋገፉና እየተሻኮቱ እንዴት የአሁኗን የኢትዮጵያን ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ማንነት እንደቀረጹ የሚያስረዳ ዋቢ የታሪክ መጽሐፍ ነው።

ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881)" የተሰኘውና በደጃዝማች አበበ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያን የታሪክ አቅጣጫ በቁርጠኝነት በለወጡት ታላቁ ወታደራዊ ስትራ
ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881)" የተሰኘውና በደጃዝማች አበበ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያን የታሪክ አቅጣጫ በቁርጠኝነት በለወጡት ታላቁ ወታደራዊ ስትራቴጂስትና ፖለቲከኛ ራስ ጎበና ዳጨ ላይ የተሰናዳ ድንቅ የታሪክ ሰነድ ነው። መጽሐፉ የጀግናውን የልጅነት ዘመን፣ የአመራር ብቃት፣ የጦር ሜዳ ውሎዎች እንዲሁም ከዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ጋር በመሆን የዘመናዊቷን ኢትዮጵያ አንድነትና መልክዓ-ምድር በመቅረጽ ረገድ የተጫወቱትን ታላቅ ሚና በጥልቀትና በምርምር ይተነትናል።   መጽሐፉ፣ ተደብቀውና ተረስተው የቆዩ በርካታ የታሪክ እውነታዎችን በይፋ የሚያወጣና ለአንባቢ አዲስ እይታን የሚለግስ ውድ የሥነ-ጽሑፍ ሀብት ነው ። በተለይም የሀገራቸውን ጥንታዊ የወታደራዊ ጥበብ፣ የዲፕሎማሲ ጥልቀትና የአንድነት ጉዞ በጥሩ ቃላትና ሚዛናዊ በሆነ የታሪክ ትረካ ማወቅ ለሚሹ ሁሉ ይህ ሥራ የማይተካ የምርምርና የንባብ ማጣቀሻ ነው። 0991001450

"ድንግል ነኝ አትበይኝ" እኔ አውሬ አይደለሁ ፣ ደም አፍስሼ አልረካ፣ በሴት የዋይታ እምባ ፣ ቀኔን የማፈካ፣ የአንችነት ክብርሽን ፣ በደም ዋጋ አልካም፣ ድግል ልብሽ እንጅ ፣ አካልሽ አይደለም። ላ
"ድንግል ነኝ አትበይኝ" እኔ አውሬ አይደለሁ ፣ ደም አፍስሼ አልረካ፣ በሴት የዋይታ እምባ ፣ ቀኔን የማፈካ፣ የአንችነት ክብርሽን ፣ በደም ዋጋ አልካም፣ ድግል ልብሽ እንጅ ፣ አካልሽ አይደለም። ላንች እንደው ደም ማለት........ ሰርክ የምታፈሽው ፣ 1 ወር እየጠበቅሽ፣ ከሄዋን በለስ ጋር ፣ የመጣ ርግማንሽ። እናንልሽ አለሜ.......... ለመድማት ከሆነ ፣ ድሚ ግድ የለኝም፣ አንች ያልደማሽ እንደው፣ ትውልድ አይተካም፣ ፅንስ አይፈጠርም ፣ ህይወት አይቀጥልም፣ በደም ግብር ምክነያት ፣ ከፍ ያለው ይህ ስምሽ፣ በአለም አደባባይ ሁሉም እንዲጠራሽ፣ ደምሽ ንፁህ ይሁን ፣ ቆሻሻ እጅ አይንካው፣ በንፁሀን ደም ነው ፣ ትንሳኤሽ ሚበስረው። እናልሽ አለሜ......! ስለንፅህናሽ .... ፍፁም አታስቢ፣ተይው ግድ የለሽም፣ ክብርሽ ልብሽ ላይ ነው ገላሽ ላይ አይደለም። ይድረስ ለውዷ ድንግል ሀገር፣ የት እንዳለች ለጠፋችብን የኖህ መርከብ ኢትዮጵያ!!!! ገጣሚ ጊዜአለው ✍️

An Introduction to the Economic History of Ethiopia የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ታሪክ መግቢያ የተሰኘው መጽሐፍ፣ ከጥንት ጀምሮ እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ድረስ የነበረ
An Introduction to the Economic History of Ethiopia የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ታሪክ መግቢያ የተሰኘው መጽሐፍ፣ ከጥንት ጀምሮ እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ድረስ የነበረውን የኢትዮጵያን ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ጉዞ በጥልቀት የሚመረምር እጅግ ጠቃሚ የታሪክ ማጣቀሻ ነው። መጽሐፉ የአገሪቱን የግብርና ሥርዓት፣ የየብስና የባሕር የንግድ መስመሮችን፣ የገንዘብና የግብይት ዓይነቶችን፣ የከተሞች አገነባብን እንዲሁም የዕደ-ጥበብና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በሰፊው የሚያትት ሲሆን፣ የሕዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮና የባርነት ታሪክን ጨምሮ ሰፊ ማኅበራዊ ገጽታዎችን በታሪካዊ ሰነዶችና ማስረጃዎች አስደግፎ ያቀርባል። ከዚህም በተጨማሪ የባህላዊ ሕይወት ሥዕል አገሪቱ የነበራትን ጥንታዊ የሥራ ባህልና የማኅበረሰብ አወቃቀር የሚያንጸባርቅ ሲሆን፣ መጽሐፉ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ታሪክ በኢኮኖሚው መዋቅር ላይ የነበረውን ተጽዕኖ ለመረዳት ለሚፈልጉ ተመራማሪዎችና አንባቢዎች እንደ ዋነኛ መነሻ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል። መጽሐፉን በመደብራችን ያገኙታል!

ይህ የታሪክ ሰነድ በምሥራቅ አፍሪካ ምድር ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድና የሰዎች ዕጣ ፈንታ የተሰናሰሉበትን ያንን ታላቅ ዘመን በጽኑ የጽሑፍ ምስክርነት ያዘክራል። መጽሐፉ ልክ እንደ ቅዱሳን የጉዞ ታሪኮ
ይህ የታሪክ ሰነድ በምሥራቅ አፍሪካ ምድር ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድና የሰዎች ዕጣ ፈንታ የተሰናሰሉበትን ያንን ታላቅ ዘመን በጽኑ የጽሑፍ ምስክርነት ያዘክራል። መጽሐፉ ልክ እንደ ቅዱሳን የጉዞ ታሪኮች ሁሉ፣ ሰላምን ለመፈለግና ሥርዓትን ለመመሥረት ከፍ ካለውና በተባረከው የኢትዮጵያ ደጋማ ምድር ተነስተው፣ እግራቸው እሳት ወደሚመስለውና ፈታኝ ወደሆነው የሶማሊላንድ በረሃ የተጓዙትን የእንግሊዝ መኮንኖችና የአፄ ምኒልክን ጨዋ አርበኞች የተቀደሰ የትብብር ጉዞ በስሱ ይተርካል። ታዋቂው የታሪክ ሊቅ ሪቻርድ ፓንክረስትና ፍሬድሪክ ሻርፍ እንደ ታማኝ የቤተ-መቅደስ ጠባቂዎች ይህንን የተረሳ የዘመን ታሪክ አድሰውና ጠብቀው ያቆዩት ሲሆን፣ መጽሐፉ በምድር ላይ ስላለው የነገሥታት ዲፕሎማሲ፣ ስለ ሰብአዊ ፍጡራን መከራ፣ ጽናትና ሕብረት በጥልቀት የሚሰብክ፣ የሰው ልጅ በፈጣሪ መሬት ላይ ያሳለፈውን ፈታኝ የሕይወት ጎዳና የሚያሳይ ሕያው ምስክር ነው። ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር!

እነዚህ ሦስት ድንቅ መጽሐፍት በአገራችን የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ የኢትዮጵያን አብዮት ማዕበል በጥልቅ የከሸኑ እውነተኛ የጥበብ ማማዎች ናቸው። ታላቁ ደራሲ ብርሃኑ ዘሪሁን በዚሁ ታዋቂ የረጅም ልብ-
እነዚህ ሦስት ድንቅ መጽሐፍት በአገራችን የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ የኢትዮጵያን አብዮት ማዕበል በጥልቅ የከሸኑ እውነተኛ የጥበብ ማማዎች ናቸው። ታላቁ ደራሲ ብርሃኑ ዘሪሁን በዚሁ ታዋቂ የረጅም ልብ-ወለድ ጥራዝ፣ የአንድን ትውልድ የለውጥ ናፍቆት፣ የትግል ወላፈን እና የሕዝብን ማኅበራዊ ስብራት በደማቅ ቀለማት ይሥላል። ታሪኩ በለውጥ ዋዜማ ካለው ማኅበራዊ መናወጥ ተነስቶ፣ አሮጌው ሥርዓት ሲናድና አዲሱ አብዮት በደም አበራሽ ጎዳና ላይ ሲወለድ የነበረውን እውነተኛ ገጽታ በገጸ-ባህሪያቱ ሕይወት ውስጥ በሕያውነት ይተርካል። ደራሲው የሰው ልጅን የሥልጣን ጥም፣ የነፃነት ፍለጋ፣ የክህደት ምሬት እና የጋራ ሰብአዊ መከራን በብዕሩ በመቅረጽ፣ አንባቢን በታሪክ ማኅደር ውስጥ እንዲጓዝ የሚያደርግና የዘመኑን ማኅበራዊ ውቅያኖስ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የማይደበዝዝ የሥነ-ጽሑፍ ሐውልት ነው። መጽሐፎችን በመደብራችን ታገኟቸዋላችሁ!

ይህ መጽሐፍ ቅዱስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጥንታዊና ታሪካዊ የቅዱሳት መጻሕፍት ሀብት በዕንግሊዝኛ ቋንቋ አጠቃሎ የያዘ ታላቅ መንፈሳዊ መዝገብ ነው። መጽሐፉ «The Complet
ይህ መጽሐፍ ቅዱስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጥንታዊና ታሪካዊ የቅዱሳት መጻሕፍት ሀብት በዕንግሊዝኛ ቋንቋ አጠቃሎ የያዘ ታላቅ መንፈሳዊ መዝገብ ነው። መጽሐፉ «The Complete Orthodox Ethiopian Bible in English» በሚል ርዕስ በኮቨናንት ሴክሬድ ፕሬስ (Covenant Sacred Press) የታተመ ሲሆን፣ በውስጡም ከቀኖና መጻሕፍት በተጨማሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ የማይገኙ ነገር ግን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቀኖና ውስጥ በቅዱስነትና በስልጣን የተጠበቁትን እንደ መጽሐፈ ሄኖክ፣ መጽሐፈ ኢዮቤልዩ፣ የዕዝራ ሱቱኤል እና መጽሐፈ ጥበብ ያሉ እጅግ ውድ የሆኑ ጥንታውያንና አዋልድ መጻሕፍትን አካትቶ የያዘ የጥበብ ምንጭ ነው። በሽፋኑ ላይ በግልጽ እንደሚታየው፣ በውስጡ 88 የታተሙ መጻሕፍትን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ዲጂታል መጻሕፍት ማጣቀሻዎችን (3500 Books) የያዘ በመሆኑ፣ ለአንባቢያንና ለተመራማሪዎች ሰፊ መንፈሳዊና ታሪካዊ ዕውቀትን የሚያድል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ክርስቲያናዊ ቅርስና ሥነ-ጽሑፋዊ ትውፊት ለዓለም የሚያስተዋውቅ ድንቅ የሃይማኖት ሰነድ ነው። ኦርጅናል የሆኑ ሁለት ፍሬ መጽሐፎችን አስገብተናል። እዘዙን ያሉበት ቦታ እናደርሳለን!

"የሰው ፊት" አንዳንድ ህመም አለ ይማርህ የማይሉት፣ ወደ ውስጥ ዘልቆ የሚገባ ካ'ንጀት። በቃላት ሰንሰለት ሊገለጥ የማይችል፣ የጭንቅላት ህመም ክፉ የልብ ቁስል። በዚህ ምስል መሀል.... ይታየኛል
"የሰው ፊት" አንዳንድ ህመም አለ ይማርህ የማይሉት፣ ወደ ውስጥ ዘልቆ የሚገባ ካ'ንጀት። በቃላት ሰንሰለት ሊገለጥ የማይችል፣ የጭንቅላት ህመም ክፉ የልብ ቁስል። በዚህ ምስል መሀል.... ይታየኛል ህመም ይታየኛል ስቃይ፣ ይነበባል በደል ተጽፏል ፊቱ ላይ። ኑ እስኪለን ድረስ.... ማግኜትና ማጣት መቼገር ቢኖርም፣ እንደ ሰው ፊት ማየት የሚያም ነገር የለም። ገጣሚ ጊዜአለው✍️

የሰሞኑ የአዲስአበባ ኢግዚቢሽን የመጽሐፍት አውደ ርዕይ ያልተካፈላችሁ አንባቢዎች ክፉኛ ተጎድታችኋል። አሁንም አልረፈደም ኢግዚቢሽኑ ነገ እና እሁድም የሚቀጥል ሲሆን በተለይ እሁድ ይህ የአዳም ረታ መ
የሰሞኑ የአዲስአበባ ኢግዚቢሽን የመጽሐፍት አውደ ርዕይ ያልተካፈላችሁ አንባቢዎች ክፉኛ ተጎድታችኋል። አሁንም አልረፈደም ኢግዚቢሽኑ ነገ እና እሁድም የሚቀጥል ሲሆን በተለይ እሁድ ይህ የአዳም ረታ መጽሐፍ በይፋ ለንባብ ይቀርባልና አንዳትቀሩ። ከተወዳጅ ደራሲዎች ጋር የማይረሳ ጊዜም አሳልፉ!

የተነበቡ (ያገለገሉ) አሮጌ መጽሐፍትን እንገዛለን! በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የተፃፉ፦ 👉 የታሪክ 👉 የሐይማኖት 👉የፍልስፍና 👉የሳይኮሎጂ እና ልቦለድ መጽሐፍትን እንገዛለን! ከዚህም በተጨማሪ
የተነበቡ (ያገለገሉ) አሮጌ መጽሐፍትን እንገዛለን! በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የተፃፉ፦ 👉 የታሪክ 👉 የሐይማኖት 👉የፍልስፍና 👉የሳይኮሎጂ እና ልቦለድ መጽሐፍትን እንገዛለን! ከዚህም በተጨማሪ 👉ጋዜጣ 👉ወረቀት 👉የክር ካሴቶችን እንገዛለን! ስልክ ፦0991001450 ወይም ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ ገብታችሁ አናግሩኝ! 👇👇👇👇👇 @a9OaG @a9OaG @a9OaG