234
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from Addis Ababa Education Bureau
አዲስ መዋቅር እየተጠና እንደሚገኝ እና በዋናነትም የተማሪዎችና የመምህራንን የዲሲፒሊን ችግሮች የሚቀርፍ መመሪያ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ ጠቁመው በቅርቡ የተጀመረው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ እንዲችል አመራሩ ሚናውን በአግባቡ ሊወጣ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ዶክተር ዘላለም አክለውም በ2016ዓ.ም የመማር ማስተማር ስርአቱ ውጤታማ እንዲሆን የትምህርት ቁሳቁሶችንም ሆነ የመማሪያ መጽሀፎችን ለማቅረብ የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው በትምህርት ተቋማት አከባቢ የሚገኙ አዋኪ ጉዳዮችን ማስወገድ እንዲቻል ችግሮቹን በመለየት እንዲወገዱ ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Repost from Addis Ababa Education Bureau
በትላንትናው እለት የተጀመረው የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች ግምገማዊ ስልጠና ተጠናቀቀ።
አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 5 ፣ 2015 ዓ.ም (ትምህርት ቢሮ) ግምገማዊ ስልጠናው የትምህርት ሴክተሩን የ2015ዓ.ም አፈጻጸምና የ2016ዓ.ም እቅድን መሰረት አድርጎ የተካሄደ ሲሆን የመርሀ ግብሩ ተሳታፊዎች በቀረበው ሰነድ ዙሪያ ባካሄዱት የቡድን ውይይቶች ያነሱዋቸውን የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎች በጽሁፍና በክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ኃላፊዎች አማካይነት አቅርበው በቢሮ አመራሮች ምላሽ ተሰቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ኡመር በመርሀ ግብሩ እንዳስታወቁት በዘንድሮው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በቀን ተማሪዎች አበረታች ውጤት የተመዘገበ ቢሆንም የማታ ተማሪዎችን ከማብቃት አኳያ የታዩ ችግሮች ባስቸኩዋይ ሊስተካከሉ እንደሚገባ ገልጸው ትምህርት ቤቶች የ2016ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ መርሀ ግብርን በሁሉም የትምህርት እርከኖች ቢሮው በሚልከው ፎርም መሰረት ማካሄድ እንደሚገባቸው አስረድተዋል።
አዲሱን ስርአተ ትምህርት መሰረት አድርጎ በተጀመሩ አዳዲስ የትምህርት አይነቶች ለሚያስተምሩ መምህራን የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አሊ ከማል ጠቅሰው የተማሪዎችን ውጤትና ስነምግባር ለማሻሻል የትምህርት አመራሩ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ አመራሩ ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በግምገማዊ ስልጠናው ባስተላለፉት መልዕክት ዘንድሮ የተካሄደው የትምህርት አመራሩ ግምገማዊ ስልጠና ቀድሞ ከነበረው አንጻር በጥብቅ ዲስፕሊን የተካሄደ መሆኑን በመግለጽ የትምህርት ስርአቱ ውጤታማ እንዲሆን
ለሁሉም ት/ቤቶች
👉ጉዳዩ፡- የተጓዳኝ ትምህርት(ክበባት) አደረጃጀትና አተገባበር ማንዋልን ይመለከታል
👉በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የሥርዓተ-ትምህርት ማበልጸጊያ አዲሱን የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ እና የአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ-ትምህርት ማዕቀፍ መነሻ በማድረግ ተማሪዎች በመማሪያ ክፍል በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን እንደየ ዝንባሌያቸው ከክፍል ውጪ በተግባር እንዲለማመዱና ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳ የተጓዳኝ ትምህርት አደረጃጀትና አተገባበር ማንዋል አዘጋጅቷል፡፡
👉በመሆኑም ከ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ እንደየ ክፍል ደረጃዎቹ እና እንደየትምህርት ቤቶቹ ተጨባጭ ሁኔታ በማቀድ ወደተግባር እንዲገባ የአዲስ አበባ ከተማ ት/ቢሮ በደብዳቤ ያሳወቀን በመሆኑ ሰነዱን መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር እንዲገባ እናሳስባለን::
የየካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት
በየካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ስር ለምትገኙ
👉1ኛ እና 2ኛ ደረጃ የመንግስት ት/ቤቶች በሙሉ
ጉዳዩ ፡- የ2016 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባን ይመለከታል
☝️ ከላይ በርእሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው የ2016 ዓ.ም የተማሪ ምዝገባ በከተማ ደረጃ የሚመዘገብበት ጊዜአዊ ከላንደር በት/ቢሮ በኩል መላኩ ይታወቃል ፡፡
👉ይሁን እንጅ አንዳንድ ት/ቤቶች የተማሪ ምዝገባ ከተቀመጠው ጊዜ ውጭ ምዝገባ እያካሄዳችሁ መሆኑን መረጃ የደረሠን በመሆኑ ከተቀመጠው ጊዜ ውጭ ሲመዘግብ የተገኘ ት/ቤት ተጠያቂ የሚደረግ መሆኑን በጥብቅ እናሰስባለን ፡፡
የየካ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የሀይማኖት ተቋማት ተወካዮችን ጨምሮ የአካል ጉዳተኞች ማህበር አመራሮችና የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር አባላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Repost from Addis Ababa Education Bureau
በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተግባራዊ የሚደረገውን የግብረገብ ትምህርት መጽሀፍ ብቃት የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
(ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም) የግብረገብ ትምህርት አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች የሚሰጥ ሲሆን ትምህርቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአማርኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች የሚሰጥ ይሆናል፡፡
በኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር በእንግሊዘኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ የተላከውን የግብረገብ ትምህርት ወደ አማርኛ ቋንቋ የመተርጎምና ከከተማው አውድ ጋር የማስማማት ስራ መሰራቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የስርአተ ትምህርት ማበልጸግና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ታለማ ገልጸው በቀጣይ በብቃት ማረጋገጥ መርሀግብሩ ከተሳተፉ አካላት የሚሰጡ ሀሳቦችን በማካተት መጽሀፉን ወደማሳተም ሂደት እንደሚገባ አስታውቀዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአፋን ኦሮሞ ስርዓተ ትምህርት ማበልጸግና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሮቢ ዋሚ በበኩላቸው በትምህርት ሚኒስቴር በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተዘጋጀው የግብረገብ ትምህርት(barnootaa safuu) ወደ አፋን ኦሮሞ ቋንቋ ተተርጉሞ በአሁኑ ሰአት በባለድርሻ አካላት ብቃቱን የማረጋገጥ ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው ከገምጋሚዎቹ የሚገኙ ተጨማሪ ሀሳቦችን በማካተት በ2016ዓ.ም ትምህርቱን ተግባራዊ ለማድረግ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል፡፡
ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀን በሚካሄደው የመጽሀፉን ብቃት የማረጋገጥ መርሀ ግብር የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት መምህራን ፤የመምህራን ማህበርና የወላጅ ማህበር ተወካዮች፤የትምህርት ባለሙያዎች፤ የሀይማኖት ተቋማት ተወካዮችን
Repost from Addis Ababa Education Bureau
#ማስታወቂያ ለትምህርት ዕድል ፈላጊዎች
(አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 28 2015 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2015 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ተፈትናችሁ
በእቴጌ መነን የሴቶች 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት
በገላን የወንዶች 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት
በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ቀዳማዊ ምኒሊክ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ
መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
የወጣቶች ገነት ቅ/አንደኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የ2015 ዓ.ም በ6ኛ ክፍል 44 ተማሪዎችን በማስፈተን 35ቱ ከ50% በላይ 9ኙ ከ50% በታች በማስመዝገብ 79.54% ማሳለፍ ችሏል።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ከ2016ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሀገሪቱን ስርአተ ትምህርት ተግባራዊ የማያደርጉ አለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች(international school) የሚማሩ ተማሪዎች የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል መልቀቂያን ጨምሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና መፈተን እንደማይችሉ ኃላፊው በመግለጫቸው ጠቁመው ወላጆች ከወዲሁ ይህንኑ ታሳቢ ያደረገ ውሳኔ በመወሰን ልጆቻቸውን ማስመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡
ተማሪዎች ውጤታችሁን ሊንኮቹን በመጫን መመልከት ተችላላችሁ
https://aa6.ministry.et/#/result
Telegram bot: @G6MinistryResultQMTBot
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ሰበር ዜና!
የ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ፡፡
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2015 (ትምህርት ቢሮ) ከ28 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብቻ የተሰጠው ከተማ አቀፉ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በዛሬው እለት ይፋ ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች መግለጫ ሰተዋል፡፡
ኃላፊው በመግለጫቸው ዘንድሮ ፈተናውን 73,667 ተማሪዎች መውሰዳቸውን ጠቁመው 50% እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡ መደበኛ ተማሪዎች ወደ 7ኛ ክፍል እንዲዘዋወሩ መወሰኑን በመጥቀስ የተለያየ የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች የማለፊያ ነጥቡ 45% መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘንድሮ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 80.2% ያህሉ 50 ፐርሰንት እና ከዛ በላይ በማምጣት ማለፋቸውን ዶክተር ዘላለም ገልጸው 67,939 ከሚሆኑ የቀን ተማሪዎች መካከል 56,842 የሚሆኑት ማለትም 83.6 % ያህሉ የማለፊያ ውጤቱን በማስመዝገብ ወደቀጣዩ የትምህርት እርከን መዘዋወራቸውን አስረድተዋል፡፡
ቢሮው የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የ6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ዶክተር ዘላለም ገልጸው በዋናነትም አዲሱን ስርአተ ትምህርት መሰረት ያደረገ የማጠናከሪያ ትምህርት እና የሞዴል ፈተናን በመስጠት ፤የተሻለ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት፤ እንዲሁም መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ተማሪዎችን ብቁ የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መደረጉ ተማሪዎቹ አበረታች ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማስቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ሰበር ዜና!
በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተሰጠው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ነገ ይፋ ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2015 (ትምህርት ቢሮ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጀነራል ካውንስል በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰጠው በ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ማለፊያ ነጥብ ላይ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን በሙሉ ድምጽ ወስናል፡፡
ውጤቱንም በማስመልከት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ለሚዲያ አካላት ነገ 4 ሰሃት ላይ ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ይፋ ይሆናል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 28-30/10/2015 ዓ.ም ድረስ በ182 የፈተና ጣቢያዎች ለ75,090 ተማሪዎች ፣ 1,900 ፈታኞችን፣ 700 ሱፐር ቫይዘሮችንና 182 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችን በማሳተፍ መሰጠቱ ይታወሳል።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ሰበር ዜና!
የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ይፋ ሆነ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በዛሬው እለት የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ማለፊያ ውጤትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡ ሲሆን በመግለጫቸውም በዘንድሮው ማለፊያ ውጤት 50% እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡ መደበኛ ተማሪዎች ወደ ዘጠነኛ ክፍል እንደሚዘዋወሩ ጠቁመው የተለያየ የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች የማለፊያ ነጥቡ 45% መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘንድሮ 73,385 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደው 70.6% ያህሉ 50 ፐርሰንትና ከዛ በላይ በማምጣት ማለፋቸውን ዶክተር ዘላለም ገልጸው 61,840 ከሚሆኑ የቀን ተማሪዎች መካከል 50,812 የሚሆኑት ማለትም 82.16 % ያህሉ የማለፊያ ውጤቱን በማስመዝገብ ወደቀጣዩ የትምህርት እርከን መዘዋወራቸውን አስረድተዋል፡፡
የዘንድሮው ውጤት ባለፉት አመታት ጋር ሲነጻጸር መሻሻል ማሳየቱን ኃላፊው ጠቁመው ለዚህም የሞዴል ፈተናዎችና የማጠናከሪያ ትምህርቶች መሰጠታቸው ፤የተሻለ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ስርዓት መዘርጋቱ፤አዲሱን ስርአተ ትምህርት መሰረት ያደረገ ፈተና መዘጋጀቱ እንዲሁም መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣታቸው እንዲሁም በትምህርት ቤቶች የተጀመረው የምገባ ስርዓትና ለተማሪዎች እየቀረቡ የሚገኙ ዩኒፎርምን ጨምሮ የተለያዩ የመማሪያ ቁሳቁሶች ለውጤቱ መሻሻል አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አስገንዝበዋል፡፡
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ቀን 21/11/2015 ዓ.ም
ሰበር ዜና!
የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰአታት በኋላ ይፋ ይሆናል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጀነራል ካውንስል በ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ማለፊያ ነጥብ ላይ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ከውይይቱ በሃላ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ውጤቱን አስመልክተው ለሚዲያ አካላት 4 ሰሃት ላይ ማብራሪያ የሚሰጡ ይሆናል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 26-27/10/2015 ዓ.ም ድረስ በ182 የፈተና ጣቢያዎች ለ75100 ተማሪዎች ፣ 1,900 ፈታኞችን፣ 700 ሱፐር ቫይዘሮችንና 182 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችን በማሳተፍ መሰጠቱ ይታወሳል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
👉*ጊዜያዊ የ2016 ዓ.ም የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ
👉በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም የትምህርት ጊዜ ሰሌዳ
👉በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህር ቢሮ ባሉ የመንግስት የግልና በሌሎች ቅድመ አንደኛ፤ አንደኛ ደረጃ መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ወጥ የሆነ የትምህርት አተገባበር የጊዜ ሰሌዳ በማስፈለጉ ይህ ጊዜያዊ የትምህርት የጊዜ ሰሌዳ Calendar ተዘጋጅቷል።
የዚህ ግሩፕ አባል የሆናችሁ በሙሉ
በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 በተለምዶዉ ሾላ ገበያ/ባዶ እግር አካባቢ የሚገኘዉን ወጣቶች ገነት ትምህርት ቤት ስም የተከፈተ በመሆኑ
አላማዉ በ25/10/2015 እንደ አገሪቱ በትምህርት ሚኒስተርና በጠቅላይ ሚኒስተሩ በኩል ትምህርት ለትዉልድ በሚል መሪ ቃል ትምህርት ቤቶችን ያለባቸዉን የመሰረተ ልማት ችግር በጋራ በመወያየት በገንዘብ፤ በጉልበት፤ በእዉቀት፤ በአይነት በማሰባሰብ ችግሩን በመቅረፍ ለነገ ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት ስለሆነ
ወደዚህ ግሩፕ መቀላቀል ያለባቸዉ፡-
ከግለሰቦች፣
የቀድሞ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች
የአካባቢ ማህበረሰብ፣
በት/ት ቤቱ ተምረው የወጡ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ የቀድሞ ተማሪዎች
ባለሀብቶችን፣ ታዋቂ ግለሰቦችን፣ ማህበራትን፣ የግልና የመንግሥት ተቋማትን፣ የልማት አጋሮችን፣ ወዘተ. በማሳተፍ በተለያየ የኮሚኒኬሽን ስልቶች በማሰባሰብ የበኩላቸዉን ድርሻ እንዲወጡ በማድረግ ነዉ፡፡ በመሆኑም ሁላችንም ከላይ የተጠቀሱ አካላትን አባል በማድረግ የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ
የዚህ ግሩኘ አባል የሆናችሁ ሁሉ የተሰባሰበው ለተቀደሰ አላማ ነውና ያልተቀላወቀሉትን አባል እያደረጋችሁ እያልኩ አባል እያመጣችሁ ያላችሁ በርቱ በዚሁ ግፉበት ሌሎቻችሁም ተንቀሳቀሱ
የት/ቤታችን ር/መምህር አቶ መሃመድ ኢሳ
https://t.me/WotatochGenet
#ETHIOPIA
ማህበራዊ ሚዲያዎች ያለ VPN መስራት ጀመሩ።
ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቹ ለማረጋገጥ ችሏል።
#ቴሌግራም ፣ ዩትዩብ ፣ ፌስቡክ ፣ ቲክቶክ መሰል የማህበራዊ ሚዲያዎች ከወራት በፊት (የካቲት ወር 2015 ዓ/ም) በተጣለባቸው ገደብ ያለ VPN መስራት እንዳቆሙ ይታወቃል።
ዛሬ ሰኞ ከሰዓታት በፊት ግን እነዚህ የማህበራዊ ሚዲያዎች #ያለ_VPN_እየሰሩ እንደሚገኙ እና ገደቡም መነሳቱን #ማረጋገጥ ችለናል።
