en
Feedback
Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Open in Telegram
888
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
❓❓እንዴት እናጥና🤔❓❓❓
በእነዚህ ምክሮች መሠረት የማስታወስ ችሎታችሁንና የትኩረት አቅማችሁን ታዳብራላችሁ።
📌 1. á‰áˆ­áˆľáŠ“ ጠቃሚ ምግቦች
ሰውነታችን በአግባቡ ሥራውን እንዲሰራ ኃይል ያስፈልገዋል፤ አንጎላችን ደግሞ ትኩረት እንዲኖረውና የማስተዋል አቅማችን እንዲጨምር በቂ የሆነና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት ይፈልጋል። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ቁርሳቸውን ተመግበው ወደፈተና የሚገቡ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ። የተመጣጠነ ምግብ ተመግበው ለፈተና የሚቀርቡት ደግሞ የበለጠ የማስታወስና የማስተዋል አቅም ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሁሌም ቢሆን ፈተና ያለባቸው ተማሪዎች እንደ የገብስ ገንፎ፣ ዳቦ፣ ሩዝና ድንች ያሉ በካርቦሃይድሬት የበለጸጉ ምግቦችን በቁርስ ሰዓት ተመግበው ቢወጡ ይመከራል። እርጎ፣ እንቁላል፣ አሳ፣ ጎመን፣ ቲማቲምና አቮካዶ ዓይነት ምግቦችም እጅጉን ጠቃሚ ናቸው።
📌 2. á‰ áŒ á‹‹á‰ľ ወደ áŒĽáŠ“á‰ľ መግባት
ሁሌም ቢሆን ነገሮችን አስቀድሞ መጀመርን የመሰለ ነገር የለም። ለፈተናም ቢሆን ጥናት በጠዋት ተነስቶ መጀመር በፈተና ወቅት የተረጋጋ መንፈስ እንዲኖረን ይረዳል። ጠዋት ላይ ጭንቅላታችን እረፍት አድርጎ በአዲስ መንፈስ ሁሉንም ነገር ስለሚጀምር፤ በዚህ ሰዓት ማጥናት ውጤታማ ያደርጋል። በተለይ ደግሞ የክለሳ ጥናቶችን ለከሰዓት ማሸጋገር ተገቢ አይደለም። ጠዋት ጥናት የምንጀምርበትና የምናበቃበት ሰዓት ከፈተናው በፊት ባሉት ሁለት ወይም ሦስት ሳምንታት ውስጥ ተመሳሳይ ለማድረግ መሞከርም ውጤታማ ያደርጋል።
📌 3. áˆáŠ• ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ ወስኑ
በመጀመሪያ ፈተናው የጽሁፍ ነው ወይስ የተግባር? ወይስ ቃለመጠይቅ ነው የሚለውን መለየት ወሳኝ ነው። ሁሉም ዓይነት ፈተናዎች የራሳቸው የሆነ የተለያየ አይነት አቀራረብ አላቸው። በምሳሌ አስደግፎ ማብራሪያ መስጠት የሚጠይቅ ዓይነት ፈተና ከሆነ ከዚህ በፊት የተሠሩ ፈተናዎችን እያመሳከሩ ጥቂት ቦታዎች ላይ በትኩረት መዘጋጀት። ምናልባት ፈተናው ምርጫ አልያም አጭር መልስ የሚፈልግ ዓይነት ከሆነ ቀለል ያለና አጠቃላይ መረጃዎችን ለመያዝ መሞከር።
📌 4. áŠĽá‰…á‹ľ ማዘጋጀት
ምናልባት ነገሮችን ቦታ ቦታ ለማስያዝና እቅድ ለማውጣት የምናጠፋው ጊዜ የባከነ መስሎ ሊሰማን ይችላል። ነገር ግን እውነታው በተቃራኒው ነው። ምክንያቱም ምን ማጥናት እንዳለባችሁና መቼ ማጥናት እንዳለባችሁ እቅዳችሁ ይነግራችኋል። ከዚህ በተጨማሪም ምን ያክል እንደተጓዛችሁ ለመመዝገብና ለመከታተል ይረዳል። የትኞቹን ማስታወሻ ደብተሮች መቼ መመልከት እንዳለባችሁ፣ የትኞቹን መጻህፍት ለተጨማሪ ማብራሪያ እንደምትጠቀሙ እንዲሁም የፈተና ጥያቄዎችን መቼ መለማመድ እንዳለባችሁ በእቅድ ውስጥ ማስገባት ውጤታማ ያደርጋል። እዚህ ጋር መርሳት የሌለብን ለእረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴም ቦታ መስጠት እንዳለብን ነው።
📌 5. áŠ¨á‹ááˆŽ ማጥናት
የክለሳ ጥናትን ከፋፍሎ ማካሄድን የመሰለ ነገር የለም። አንድ የትምህርት ዓይነት ላይ 10 ሰዓት ሙሉ ከማሳለፍ በየቀኑ አንድ ሰዓት በማጥናት በ10 ቀን መጨረስ ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋል። ያጠናነውን ነገር ለማስታወስና በቀላሉ ለመሸምደድ ጭንቅላታችን ጊዜ ይፈልጋል። ከፋፍሎ ማጥናት ደግሞ ለዚህ ፍቱን መድሃኒት ነው። ከፋፍሎ ማጥናት እጅግ ውጤታማው መንገድ እንደሆነም በመላው ዓለም የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች ያለመክታሉ።
📌 6. ራሳችሁን ቶሎ ቶሎ ፈትኑ
የሥነ አዕምሮ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚሉት የማስታወስ ችሎታን ለማዳበርና በራስ መተማመናችንን ለመጨመር ራስን መፈተን ውጤታማ ያደርጋል። ከዚህ በተጨማሪ እየተዘጋጀንበት ያለነውን ጉዳይ በደንብ እንድናውቀው ከማድረጉ በተጨማሪ የረሳናቸው  የረሳናቸው አልያም የዘለልናቸው ርዕሶችን ለመለየት ይረዳናል።
📌 7. áˆ˜áˆáˆ…ር መሆን
ከባዱን የክለሳና ራሳችሁን የመፈተን ሥራውን ካከናወናችሁ በኋላ ጓደኞቻችሁን ሰብሰብ አድርጋችሁ በጭንቅላታችሁ የሚመጣውን ነገር በሙሉ ንገሯቸው። ራሳችሁን በመምህር ቦታ አድርጋችሁ እውቀታችሁን ለማካፈል ሞክሩ። ምን ያህል እንደምታስታውሱ ለማወቅ ከመርዳቱ በተጨማሪ ጓደኞቻችሁንም ትጠቅሟቸዋላችሁ።
📌 8. áŠ¨á‰°áŠ•á‰€áˆłá‰ƒáˆ˝ ስልካችሁ ራቅ በሉ
ስልኮች በጣም ብዙ ጥቅም አላቸው። ነገር ግን በጥናት ወቅት ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ነው የሚያመዝነው። በተለይ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምትጠቀሙ ከሆነ። ብዙ ጥናቶች እንዳረጋገጡት ብዙ ጊዜያቸውን ስልካቸው ላይ የሚያሳልፉ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው ሁሌም ቢሆን ዝቅ ያለ ነው። ብትችሉ ስልካችሁን አጠገባችሁ እንኳን አታድርጉት።
📌 9. áˆ™á‹šá‰ƒ መቀነስና በጸጥታ ማንበብ
በጸጥታ ውስጥ ሆነው ጥናታቸውን የሚያከናወኑ ተማሪዎች ሙዚቃ እየሰሙ ከሚያጠኑት ጋር ሲወዳደሩ በእጅጉ የተሻለ የማስታወስና የትኩረት አቅም እንዳለቸው ማረጋገጥ ተችሏል።
📌 10. á‰‹áˆš እረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴ
ውጤታማ የክለሳ ጥናት ማለት እረፍት አልባ ጥናት ማለት አይደለም። በጥናታችን መሀል መሀል ላይ ጥሩ አየር ለማግኘትና ሰውነታችንን ለማፍታታት ወጣ ብሎ እንቅስቃሴ ማድረግ የማስታወስ ችሎታችንን በደንብ ከፍ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሰውነታችን እና ጭንቅላታችን በእጅጉ የተሳሰሩ በመሆናቸው እንቅስቃሴ ስናደርግ የደም ዝውውራችን ይስተካከላል፤ ይህ ደግሞ በቂ ኦክስጅን ወደ ጭንቅላታችን እንዲሄድ ይረዳል። አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ጭንቀትን መከላከልና በራስ መተማመንን መጨመር ከነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
📌   11. áŠĽáŠ•á‰…áˆá
ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው። ✅በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዲሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታድርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ። 👍እስካሁን የተዘረዘሩትን ነገሮች ሁሉ ተግባራዊ ካደረጋችሁ ምንም የሚያሳስባችሁ ነገር ሊኖር አይገባም። መልካም ፈተና!

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ  አስተዳዳር ት/ጽ/ቤት ስር ባሉ ት/ቤቶች ውስጥ በመስራት ላይ ለምትገኙ የት/ት ማህበረሰቦች በሙሉ፦ በ2016ዓ.ም የት/ት ዘመን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ትምህርት ቢሮ በደብዳቤ በአሳወቀን መሰረት ጤግሮስ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር  በት/ቢሮው ስር ለሚገኙ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት ሰራተኞች የመኪና ተጠቃሚ ለማድረግ ከፍኖተ የገንዘብና ብድር ኃ/የተ/የግ/ማህበር  ጋር በጋራ በመስራት 40% ብድር በማመቻቸት ወደ ስራ ለመግባት ይዞ የቀረበው ዝርዝር ሁኔታዎች እንደሚከተለው ተቀምጧል፡፡ 1.  ለምዝገባ የሚከፈል ብር ፤- ለአገልግሎት 1,000 ብር  የግለሰቡ  የራሱ ቁጠባ  3,500 ብር አጠቃላይ  4,500 ብር ነው፡፡ 2.  ቁጠባ በተመለከተ ፤- ለተከታታይ ለ 6 ወራት  4000 ብር  ወርሃዊ ቁጠባ ይሆነና አንድ ሰው እጣ ከደረሰው በኋላ  በየወሩ  8000 ብር ክፍያ  ሆኖ ይቀጥላል :: 3.  የመኪናዎቹ አይነት ፤- በኤሌክትሪክ  የሚሰሩ ሲሆኑ ዲዛይናቸው ብዙ አይነት እና ዋጋቸው የተለያየ  ስለሆነ ግለሰቡ የሚፈልገውን መምረጥ ይችላል፡፡ 4.  እዳው ሙሉ በሙሉ ተከፍሎ የሚያልቀው   በ10 ዓመት ውስጥ ነው፡፡ 5.  ለኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ  የተሰጠ ኮታ ፤- 500 መኪናዎች ( 500 ተመዝጋቢዎች ይኖራሉ ተብሎ   ስለሚጠበቅ)፡፡ 6.  እጣው በየሁለት ወሩ የሚወጣ ሲሆን ለሁሉም ( ለ500 ሰዎች ) ተመዝጋዎች ተደራሽ  የሚሆነው   ፤- በአንድ ዓመት   ከአራት  ወር  ውስጥ ነው፡፡ 7.የግዥ አማራጮች  ፤-   ለተከታታይ 6 ወር 4000 ብር የቆጠበ እጣ ውስጥ ገብቶ እጣ ከደረሰው በኋላ  8000 በወር ይከፍላል፡፡   የሙሉ ዋጋውን 25% ቀድሞ የከፈለ ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡   25% መክፈል ፍላጎት ኖሮት መክፈል ያቃተው ሰው 10% በራሱ ቁጠባ  15% ከፍኖት የብድር ተቋም ተበድሮ አጠቃላይ 25% የቆጠበ ( ከፍሎ ) ቅድሚያ ማግኘት ይቻላል፡፡    አስተማማኝነቱ 1ኛ.ዋስትና ፤- በብሄራዊ ባንክ በኩል እውቅና ባለው(ከፍኖት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህ/ስ/ማህበር ) ተቋም መቆጠቡ እና እጋዊ መሆኑ፡፡     2ኛ. የመኪናው ሙሉ ኢንሹራንስ ይኖረዋል፡፡     4ኛ.የመኪናው ባትሪ የ10 ዓመት ዋስትና አለው፡፡

#የምዝገባ ቀን ጥር 15 እና 16
#የምዝገባ ቀን ጥር 15 እና 16

የትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ አሳልፏል። (ቀን ጥር 11/2016 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12
የትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ አሳልፏል። (ቀን ጥር 11/2016 ዓ.ም)  የትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን በዚህም በሁለቱም የትምህርት መስኮች እያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች ፈተናው እንዲሰጥ ተወስኗል፡፡ሲሆን የተፈጥሮ ሣይንስ፦ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት የማኅበራዊ ሣይንስ፦ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የተፃፈው ሰርኩላር፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝግጅትንም ያብራራል። በዚህም የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ከ12ኛ ክፍል ብቻ ፈተናው የሚዘጋጅ ሲሆን ሌሎች የትምህርት አይነቶች ከ9-11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንደሚሆን ያትታል። ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ወደፊት ጥናት ተጠንቶ እስከሚለይ ድረስ በነበረው አሠራር መሠረት ውጤት ተደምሮ የሚገለጽ መሆኑንም ገልጿል። የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያውቁት እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አሳስባል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728 TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

ለክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ በሙሉ! እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ጥምቀት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ከልብ እን
ለክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ በሙሉ! እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ጥምቀት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን!                                  

ከተራ ምንድን ነው? ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥ
ከተራ ምንድን ነው? ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡ በተጨማሪ  በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት  አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ። በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡ መልካም የከተራ በዓል

ቀን 08/05/2016 ዓ.ም ማስታወቂያ አርብ ማለትም 10/05/2016 ዓ.ም የከተራ እለት መንገዶች ሥለሚዘጋጉና ተማሪዎችና ሠራተኞች ላይ እንግልት ሥለሚፈጥር  ትምህርት አይኖርም።

answer sheet MORAL.pdf4.43 KB

+9
answer sheet amharic gr6.pdf4.40 KB

ቀን 02/05/2016 ዓ.ም ማስታወቂያ ለርዕሰ መምህር እና ም/ር/መምህር ተወዳድራችሁ 47 እና በላይ ዉጤት ያመጣችሁ ጥር 3/2016 ዓ.ም የቃል ጥያቄ ስላለ  7:30 ቀስተደመና ት/ቤት እንድትገኙ እናሳዉቃለን።