Kestedemena pre-primary, primary and middle school
Open in Telegram
Show more
888
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
በቀን 01/05/16 ዓ/ም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የተዘጋጀውን ሞዴል ፈተና በዚህ መልኩ እየተሰጠ ነው።
#Update
የሰራተኞች ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የተሰጠው ፈተና #ውጤት ይፋ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ፈተናን በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል።
በዚህ መግለጫም ፤ ፈተናውን የወሰዱት የከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ለአመራሮች፣ ለባለሙያዎችና ሰራተኞች ቁጥር 15 ሺህ 151 መሆኑ ተገልጿል።
ከዚህ ውስጥ የአመራሩ ቁጥር 4 ሺህ 213 ሲሆን የፈተውን ማለፊያ ውጤት ያመጡት 1 ሺህ 422 ናቸው። ይህም 34 በመቶው አመራሮች አልፈዋል። አመራሩ ለማለፍ ከ60 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።
ፈተናውን የወሰዱ የሠራተኞች ቁጥር 10 ሺህ 257 ሲሆኑ ያለፉት 5 ሺህ 95 ናቸው ተብሏል። ይህም 50 በመቶ ነው። ሰራተኞች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት አለባቸው።
ለፈተና ከተቀመጡት አጠቃላይ ቁጥር 681 የሚሆኑት በተለያየ የስነ ምግባር ጥሰት ከፈተና ውጪ መሆናቸውን እና 441 የሚሆኑት ደግሞ በፈተና ስፍራ ያልተገኙ መሆናቸው ተገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከኢፕድ እና ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ልማት ቢሮ ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia
https://principal.aa.ministry.et/ ሠላም በዚ ሊንክ ተፈታኝ አመራሮች እና መምህራን ኮዳችሁን እያስገባቹ ውጤታችሁን ማየት ትችላላቹ።
አስቸኳይ
የርዕሰ መምህራን ውድድር የፈተና ውጤት ለማየት ሊንኩ አለመስራቱን የተለያዩ አካላት በስልክና በጽሑፍ አሳውቀውናል።በዚሁ መሰረት ከትምህርት ቢሮ ችግሩ መኖሩን አምኖ በአጭር ጊዜ እንደሚያስተካክል ቃል ገብተዋ።
#የርዕሰ መምህራን ውድድር ውጤት ለማየት"
የ1ኛ እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የዋና እና የምክትል ርዕሰ መምህራን ውድድር የፅሁፍ ፈተና ውጤት ተገመገመ።
(ቀን ታህሳስ 29/2016 ዓ.ም) የ1ኛ እና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የዋና እና የምክትል ርዕሰ መምህራን ውድድር የፅሁፍ ፈተና ውጤት አብይ ኮሚቴ በመሰብሰብ የገመገመ ሲሆን ኮሚቴው በቀጣይ መሰራት በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ የፈተና ውጤቱ ከዛሬ ጀምሮ ይፋ እንዲሆን ውሳኔ አሳርፋል፡፡
የፈተና ውጤቱን ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫንና የፈተና ኮድ በማስገባት መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማስፈንጠሪያው፡- http://aaceb.gov.et/Result/
ፈተና ከጀመርን በኋላ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤
👉1. ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎችና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት።
👉2. አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ።
👉3. ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።
👉 4. በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ። ከዚህ በመቀጠል የማረጋጊያ ቃላትን ለራስዎ መንገር::
👉5. ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤
👉6. በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።
👉7. ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ።
👉8. በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ።
👉መጭው ጊዜ የፈተና ወቅት ነውና ለተፈታኞች #ሸር በማድረግ ግንዛቤ እንፍጠር
መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ ይሁንላቹ!
በፈተና ጊዜ የሚፈጠርን ጭንቀት ወይም ቴንሽንን ልንቆጣጠር የምንችልባቸው ዘዴዎች!
>> ፈተና የመፈተኛ ጊዜ ሲቃረብ ሁላችንም በመጠኑ መጨነቅ እና ከወትሮው ከፍ ባለ መጠን ውጥረት ውስጥ መግባታችን የተለመደ ነገር ነው::ይህን አይነቱን ከፍተኛ ውጥረት መቆጣጠር የምንችለበት መንገድ:-
ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን
1. ፈተና ሲመጣ መጠነኛ ውጥረትና ጭንቀት ተፈጥሮአዊና ሁሉም ተፈታኝ ተማሪ እንደሚያጋጥመው መረዳት።
2. ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊና በጎ ሀሳቦችን ብቻ ማሰብ፡፡
3. ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውንና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ እንጂ የኛ የህይወት ምዕራፍ ማብቂያ ወይም አጠቃላይ ችሎታችንን የሚያመላክት አለመሆኑን መረዳት።
4. መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅና ራስን ለማሻሻል ዝግጁ መሆን ።
5. አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን።
6.ከጓደኞች ጋር ያጠኑትን ነገር በጋራ ሆኖ መጠያየቅና እርስ በርስ ያወቁትን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃትን እንደሚጨምርና የተጠያየቁትን ነገር እንዳይረሳ ያረጋል ። ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳቱትን ነገር ድጋሚ እንድከለሱና እርማት እንድናደርግ ያግዘናል።
7.የፈተና ቀን ሲቃረብ በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።
ይቀጥላል. . .
መልካም በዓል ለትምህርት ቤቱ ሶሻል ኮሚቴ እናመሰግናለን፡፡👏👏👏👏👌👌👌👌
