en
Feedback
Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Open in Telegram
888
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
ቀን፦17/5/2016 ………ለት/ቤቱ መምህራን!!!……… የቤት መደራጀት 30% ቅድመ ክፍያ ለመክፈል የተመዘገባችሁ፤ የመመዝገቢያው ቅፅ ከላይ ባለው ስለተቀየረ፤በዚህ መሰረት መረጃውን አሟልታችሁ ሰኞ በ
ቀን፦17/5/2016 ………ለት/ቤቱ መምህራን!!!……… የቤት መደራጀት 30% ቅድመ ክፍያ ለመክፈል የተመዘገባችሁ፤ የመመዝገቢያው ቅፅ  ከላይ ባለው ስለተቀየረ፤በዚህ መሰረት መረጃውን አሟልታችሁ ሰኞ በ20/5/2016 ጠዋት መ/ራን ማህበር ቢሮ በአካል በመቅረብ መመዝገብ ትችላላችሁ።               የት/ቤቱ መ/ራን ማህበር

ለግል ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ኦን ላይን ምዝገባን አስመልክቶ ገለጻ ተሰጠ። (ቀን ጥር 17/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትም
+1
ለግል ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ኦን ላይን ምዝገባን አስመልክቶ ገለጻ ተሰጠ። (ቀን ጥር 17/2016 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ፈተና ምዘናና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት የ2016 ዓ/ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ኦላይን ምዝገባን አስመልክቶ ለግል ትምህርት ቤት ርዕስ መምህራን ገለጻ ሰጠ። የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር  ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ፈተና ምዘናና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዲናኦል ጫላ በምዝገባው ሂደት ዙሪያ እና ለምዝገባው በሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች ላይ የማስፈፀሚያ ሰነድ አቅርበው ወይይት የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች ላነሷቸው ጥያቄዎችና ለሰጧቸው አሰተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ምዝገባው ከ21/5/2016 ዓ.ም እስከ 06/6/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚከናወን ያገኘነው መረጃ ያሳያል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728 TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/ Website: - aaceb.gov.et Email;- aacaebc@gmail.com Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/

የአንደኛ ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል።

የምዝገባውን ቀን መረጃ ሳንሰማ አለፈብን፣ ቀኑ ያራዘምልን የሚሉ ጥያቄዎችን የሚያነሱ መምህራን ቁጥር እየተበራከተ ስለሆነ ለዛሬ ብቻ ሃና ማርያም ቅርንጫፍ ቢሮ ሔዳችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

❓❓እንዴት እናጥና🤔❓❓❓
በእነዚህ ምክሮች መሠረት የማስታወስ ችሎታችሁንና የትኩረት አቅማችሁን ታዳብራላችሁ።
📌 1. ቁርስና ጠቃሚ ምግቦች
ሰውነታችን በአግባቡ ሥራውን እንዲሰራ ኃይል ያስፈልገዋል፤ አንጎላችን ደግሞ ትኩረት እንዲኖረውና የማስተዋል አቅማችን እንዲጨምር በቂ የሆነና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት ይፈልጋል። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ቁርሳቸውን ተመግበው ወደፈተና የሚገቡ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ። የተመጣጠነ ምግብ ተመግበው ለፈተና የሚቀርቡት ደግሞ የበለጠ የማስታወስና የማስተዋል አቅም ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሁሌም ቢሆን ፈተና ያለባቸው ተማሪዎች እንደ የገብስ ገንፎ፣ ዳቦ፣ ሩዝና ድንች ያሉ በካርቦሃይድሬት የበለጸጉ ምግቦችን በቁርስ ሰዓት ተመግበው ቢወጡ ይመከራል። እርጎ፣ እንቁላል፣ አሳ፣ ጎመን፣ ቲማቲምና አቮካዶ ዓይነት ምግቦችም እጅጉን ጠቃሚ ናቸው።
📌 2. በጠዋት ወደ ጥናት መግባት
ሁሌም ቢሆን ነገሮችን አስቀድሞ መጀመርን የመሰለ ነገር የለም። ለፈተናም ቢሆን ጥናት በጠዋት ተነስቶ መጀመር በፈተና ወቅት የተረጋጋ መንፈስ እንዲኖረን ይረዳል። ጠዋት ላይ ጭንቅላታችን እረፍት አድርጎ በአዲስ መንፈስ ሁሉንም ነገር ስለሚጀምር፤ በዚህ ሰዓት ማጥናት ውጤታማ ያደርጋል። በተለይ ደግሞ የክለሳ ጥናቶችን ለከሰዓት ማሸጋገር ተገቢ አይደለም። ጠዋት ጥናት የምንጀምርበትና የምናበቃበት ሰዓት ከፈተናው በፊት ባሉት ሁለት ወይም ሦስት ሳምንታት ውስጥ ተመሳሳይ ለማድረግ መሞከርም ውጤታማ ያደርጋል።
📌 3. ምን ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ ወስኑ
በመጀመሪያ ፈተናው የጽሁፍ ነው ወይስ የተግባር? ወይስ ቃለመጠይቅ ነው የሚለውን መለየት ወሳኝ ነው። ሁሉም ዓይነት ፈተናዎች የራሳቸው የሆነ የተለያየ አይነት አቀራረብ አላቸው። በምሳሌ አስደግፎ ማብራሪያ መስጠት የሚጠይቅ ዓይነት ፈተና ከሆነ ከዚህ በፊት የተሠሩ ፈተናዎችን እያመሳከሩ ጥቂት ቦታዎች ላይ በትኩረት መዘጋጀት። ምናልባት ፈተናው ምርጫ አልያም አጭር መልስ የሚፈልግ ዓይነት ከሆነ ቀለል ያለና አጠቃላይ መረጃዎችን ለመያዝ መሞከር።
📌 4. እቅድ ማዘጋጀት
ምናልባት ነገሮችን ቦታ ቦታ ለማስያዝና እቅድ ለማውጣት የምናጠፋው ጊዜ የባከነ መስሎ ሊሰማን ይችላል። ነገር ግን እውነታው በተቃራኒው ነው። ምክንያቱም ምን ማጥናት እንዳለባችሁና መቼ ማጥናት እንዳለባችሁ እቅዳችሁ ይነግራችኋል። ከዚህ በተጨማሪም ምን ያክል እንደተጓዛችሁ ለመመዝገብና ለመከታተል ይረዳል። የትኞቹን ማስታወሻ ደብተሮች መቼ መመልከት እንዳለባችሁ፣ የትኞቹን መጻህፍት ለተጨማሪ ማብራሪያ እንደምትጠቀሙ እንዲሁም የፈተና ጥያቄዎችን መቼ መለማመድ እንዳለባችሁ በእቅድ ውስጥ ማስገባት ውጤታማ ያደርጋል። እዚህ ጋር መርሳት የሌለብን ለእረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴም ቦታ መስጠት እንዳለብን ነው።
📌 5. ከፋፍሎ ማጥናት
የክለሳ ጥናትን ከፋፍሎ ማካሄድን የመሰለ ነገር የለም። አንድ የትምህርት ዓይነት ላይ 10 ሰዓት ሙሉ ከማሳለፍ በየቀኑ አንድ ሰዓት በማጥናት በ10 ቀን መጨረስ ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋል። ያጠናነውን ነገር ለማስታወስና በቀላሉ ለመሸምደድ ጭንቅላታችን ጊዜ ይፈልጋል። ከፋፍሎ ማጥናት ደግሞ ለዚህ ፍቱን መድሃኒት ነው። ከፋፍሎ ማጥናት እጅግ ውጤታማው መንገድ እንደሆነም በመላው ዓለም የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች ያለመክታሉ።
📌 6. ራሳችሁን ቶሎ ቶሎ ፈትኑ
የሥነ አዕምሮ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚሉት የማስታወስ ችሎታን ለማዳበርና በራስ መተማመናችንን ለመጨመር ራስን መፈተን ውጤታማ ያደርጋል። ከዚህ በተጨማሪ እየተዘጋጀንበት ያለነውን ጉዳይ በደንብ እንድናውቀው ከማድረጉ በተጨማሪ የረሳናቸው  የረሳናቸው አልያም የዘለልናቸው ርዕሶችን ለመለየት ይረዳናል።
📌 7. መምህር መሆን
ከባዱን የክለሳና ራሳችሁን የመፈተን ሥራውን ካከናወናችሁ በኋላ ጓደኞቻችሁን ሰብሰብ አድርጋችሁ በጭንቅላታችሁ የሚመጣውን ነገር በሙሉ ንገሯቸው። ራሳችሁን በመምህር ቦታ አድርጋችሁ እውቀታችሁን ለማካፈል ሞክሩ። ምን ያህል እንደምታስታውሱ ለማወቅ ከመርዳቱ በተጨማሪ ጓደኞቻችሁንም ትጠቅሟቸዋላችሁ።
📌 8. ከተንቀሳቃሽ ስልካችሁ ራቅ በሉ
ስልኮች በጣም ብዙ ጥቅም አላቸው። ነገር ግን በጥናት ወቅት ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ነው የሚያመዝነው። በተለይ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምትጠቀሙ ከሆነ። ብዙ ጥናቶች እንዳረጋገጡት ብዙ ጊዜያቸውን ስልካቸው ላይ የሚያሳልፉ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው ሁሌም ቢሆን ዝቅ ያለ ነው። ብትችሉ ስልካችሁን አጠገባችሁ እንኳን አታድርጉት።
📌 9. ሙዚቃ መቀነስና በጸጥታ ማንበብ
በጸጥታ ውስጥ ሆነው ጥናታቸውን የሚያከናወኑ ተማሪዎች ሙዚቃ እየሰሙ ከሚያጠኑት ጋር ሲወዳደሩ በእጅጉ የተሻለ የማስታወስና የትኩረት አቅም እንዳለቸው ማረጋገጥ ተችሏል።
📌 10. ቋሚ እረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴ
ውጤታማ የክለሳ ጥናት ማለት እረፍት አልባ ጥናት ማለት አይደለም። በጥናታችን መሀል መሀል ላይ ጥሩ አየር ለማግኘትና ሰውነታችንን ለማፍታታት ወጣ ብሎ እንቅስቃሴ ማድረግ የማስታወስ ችሎታችንን በደንብ ከፍ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሰውነታችን እና ጭንቅላታችን በእጅጉ የተሳሰሩ በመሆናቸው እንቅስቃሴ ስናደርግ የደም ዝውውራችን ይስተካከላል፤ ይህ ደግሞ በቂ ኦክስጅን ወደ ጭንቅላታችን እንዲሄድ ይረዳል። አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ጭንቀትን መከላከልና በራስ መተማመንን መጨመር ከነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
📌   11. እንቅልፍ
ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው። ✅በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዲሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታድርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ። 👍እስካሁን የተዘረዘሩትን ነገሮች ሁሉ ተግባራዊ ካደረጋችሁ ምንም የሚያሳስባችሁ ነገር ሊኖር አይገባም። መልካም ፈተና!

በቀን 16/05/16 ዓ/ም የአንደኛ ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና በዚህ መልኩ እየተሰጠ ነው ።

በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ለሚያስተምሩ መምህራን የጋራ መኖሪያ ህንጻ በህብረት ስራ በማደራጀት ግንባታ ለማስጀመር በተዘጋጀ ሰነድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ። (ቀን ጥር 16/2016 ዓ.ም)  በውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር አመራሮችን ጨምሮ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የህብረት ስራ ኮሚሽን አመራሮችና የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሊ ከማል ከተማ አስተዳደሩ የመምህራንን የቤት ጥያቄ ለመመለስ የተለያዩ አማራጮችን በመከተል ላይ መሆኑን በመግለጽ ከነዚህ አማራጮች መካከል አንዱ መምህራንን በህብረት ስራ ማህበራት በማደራጀት የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ማስቻል መሆኑን ጠቁመው የዛሬው ውይይት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ወደ ተግባር ለመግባት የሚያግዝ መሆኑንም አስገንዝበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ በበኩላቸው የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ሰኔ ስድስት 2015 ዓ.ም ባፀደቀው መመሪያ መሰረት መምህራን ተደራጅተው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ማህበሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸው በቀጣይ ዛሬ የቀረበውን የማስፈጸሚያ ሰነድ መሰረት በማድረግ በአስቸኩዋይ ወደተግባር የሚገባ መሆኑን አስታውቀዋል። መምህራኑ በቀረቡላቸው አማራጮች መሰረት የቁጠባ ባህላቸውን በማሳደግ በህብረት ስራ ማህበር ተደራጅተው  የባለ 1፣ባለ 2 እና  የባለ 3 መኝታ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቆ ወደ ተግባር ለመግባት በእንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን የህብረት ስራ ኮሚሽን እንዲሁም የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አመራሮች በውይይቱ ገልጸዋል።

በቀን 16/05/16 ዓ/ም የአንደኛ ወሰነ ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና በዚህ መልኩ እየተሰጠ ነው።

መምህራንን በህብረት ስራ ለማደራጀት እና መኖሪያ ቤት እንዲገነቡ በሚደረግ ሂደት ቅድመ ቁጠባ ማለትም 30% ማሟላት የሚችሉ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንዲደራጁ እና ቀሪዎቹ ደግሞ እየቆጠቡ እንዲደራጁ ለማድ
መምህራንን በህብረት ስራ ለማደራጀት እና መኖሪያ ቤት እንዲገነቡ በሚደረግ ሂደት ቅድመ ቁጠባ ማለትም 30% ማሟላት የሚችሉ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንዲደራጁ እና ቀሪዎቹ ደግሞ እየቆጠቡ እንዲደራጁ ለማድረግ የተግባር እንቅስቃሴ ላይ መግባት እንድንችል  ቀድሞ የተላከው መረጃ እንደተጠበቀ ሆኖ ቅድሚያ የሚቆጥቡትን በቤት አይነት በመለየት እስከ አርብ 17/5/2016  እንድታሳውቁ እናሳስባለን።