Kestedemena pre-primary, primary and middle school
Open in Telegram
Show more
888
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
Repost from Yeka Education
✅በአዲስ አበባ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የ2016 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና‼️
✍️" ፈተናው በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል " - የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ
✍️በአዲስ አበባ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል፡፡
✍️ከተማ አቀፍ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት በዚህ ዓመት በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
👉በዚህም በአዲስ አበባ ለ6ኛ ክፍል 86,691 ተማሪዎች እንዲሁም ለ8ኛ ክፍል 88,028 ተማሪዎች በከተማ አቀፍ ፈተናው ይቀመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አሳውቋል።
Vua 👉#ኢዜአ
✅ቻናላችን ይህ ነው
❤❤❤❤❤❤
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/dam76
በቀን 16/06/2016ዓ.ም የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርት በዚህ መልኩ እየተሠጠ ይገኛል።
ቀስተ-ደመና ቅድመ-አንደኛ: አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
ዕለተ-ሰኞ*** 11/06/2016ዓ.ም
በስፖርት ክበብ ተጠሪና አባላት አማካኝነት የማለዳ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በተሳካ ሁኔታ ተጀመረ። በዕለቱ የተለያዩ ስፖርታዊ ሁነቶች ተከናውነዋል።
SCHOOL SPORTING FOR THE NEW GENERATION
በ06/06/2016ዓ.ም የንባብ ክበብ እና የአገራችንን እንወቅ ክበብ አባላት ተማሪዎች በሚኒሚዲያ ክበብ አስተባባሪነት ተሰጥቷቸውን አቅርበዋል።
ለተሳተፋችሁ የክበቡ ተጠሪዎች እናመሰግናለን።👌👌👌
እንደዚሁም ከትምህርት በኃላ የትውውቅ መድረክ በማዘጋጀት በትምህርት ቤቱ ማህበራዊ ክበብ አማካኝነት : መራቂ እናቶችንና አባቶችን በመጋበዝ የቀጣይ ስራችን የተባረከ እንዲሆን በመመኘት : በተሳካ ሁኔታ ጀምረን አሳክተናል።
ለተሣተፋችሁ በሙሉ ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።
04/06/2016
ለሁሉም መምህራን
የሁለተኛው መንፈቀ-ዓመት ትምህርት የሚጀምረው በ04/06/2016 ዓ.ም በመሆኑ:
ሀ ...በመማር ማስተማር ወቅት የሚያስፈልጉ የትምህርት ቁሣቁሦችን በማሟላት እና የነበረውን የክፍለጊዜ መርኻግብር መሠረት በማድረግ በስራ ገበታችሁ እንድትገኙ
ለ ... ክፍል ኃላፊ መምህራን የተማሪዎችን ውጤት(ሮስተር) እና ደረጃ በማሣወቅ ድርብ ስራችሁን (ኃላፊነተችሁን) እንድትወጡ
ሐ... የክበባት ተጠሪዎች በተለይ ሚኒሚዲያ የተሣካ ተግባቦት እንዲፈጠር በጠዋት በመገኘት ኃላፊነታችሁን እንደምትወጡ በመተማመን ይህን የስራ መልዕክት በስርዓት እንዲተገበር ለመጀመሪያ ጊዜ ሳስተላልፍ በታላቅ ትህትና ነው።
መምህር መሠረት አስፈሪ
የስራ ባልደረባችሁ።
02 06 2016ዓ.ም
