en
Feedback
Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Kestedemena pre-primary, primary and middle school

Open in Telegram
888
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+230 days
Posts Archive
በምንሠጠው አገልግሎት አገልግሎት ምን ያህል እረክተዋል?
Anonymous voting

የቀስተ ደመና መካከለኛ ፣ የመ/ደ/ት/ቤት የ2017 ዓ.ም የተማሪዎች የክፍል የተማሪዎች መተዳደሪያ ደንብ 1. አርፍዶ አለመምጣት 2. ዩኒፎርም በአግባቡ ለብሶ መምጣት 3. ከዴክስ ዴክስ አለመዝለል 4. የቤትና የክፍል ስራ በአግባቡ ሰርቶ መምጣት 5. በክፍል ውስጥ ምግብ አለመመገብ 6. አስተማሪ ሲያስተምር በአግባቡ መከታተል እና ተከትሎ አለመውጣት 7. በክፍል ውስጥ ማስቲካ አለማኘክ እና የክፍል ንፅህና መጠበቅ 8. አስተማሪ ሲያስተምር ጎን ለጎን አለማዉራት 9. በክፍል ውስጥ ኳስ አለመጫወትና_አለማርፈድ 10. የክፍል ንብረቶችን በአግባቡ መጠቀም 11. የትምህርት መማሪያ መሳሪያዎችን አሟልቶ መገኘት 12. በክፍል ውስጥ አለመረበሽ 13. የግልና የአካባቢ ንፅህናን መጠበቅ 14. ከት/ት መማሪያ መሳሪያዎች ውጪ ሌሎች ነገሮች ይዞ አለመምጣት 15. የምትቀመጡበትን ዴስክ አለመደብደብ 16. በክፍል ዉስጥ ቆሻሻ አለመጣል 17. አለመስረቅ፣ሲሰርቅ ያገኘዉን ማጋለጥ ካልሆነም ለሚመለከተዉ ማሳወቅ 18. ከክፍል ወደ ክፍል አለመሯሯጥ 19. እርስ በእርስ መዋደድና መከባበር 20. ማንኛዉም የት/ት ሂደቱን የሚረብሽና የመማር ማስተማሩን ሂደት የሚጎዱ ነገሮችን አለመፈፀም 21. ሴት ተማሪዎችን አለመተናኮል ከላይ የተጠቀሱትን ህጎች በሙሉ ያላከበረ ተማሪ መምህሩም ሆነ የት/ቤቱ አስተዳደር አስፈላጊዉን ህጋዊ ተመጣጣኝ እርምጃ የሚወስንበት መሆኑን ያስታዉቃል፡

''ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ሀሣብ የ2017ዓ.ም 17ኛ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በቀስተ ደመና ት/ቤት በተለያዩ መርኃ-ግብር ተከበረ። 04/02/2017 ''Alaabaan keenya waliin jireenya waloo keenyaan Itoophiyaa ol qabna! '' dhaadannoo jedhuun guyyaan ayyaana alaabaa bara 2017 A.L.I M/B Qasta Dammanaa Dursaa Idilee, sad 1ffaa fi G/Galeessaatti haala gaariin kabajameera.

Repost from Dr. Eyob Mamo
መወዳደር ወይስ መፎካከር?
መወዳደር ወይስ መፎካከር?

Repost from Dr. Eyob Mamo
መወዳደር ወይስ መፎካከር? ተወዳዳሪዎች የሌሎችን ስኬት በማየት ይነሳሳሉ፣ እነሱም ስኬታማ ለመሆን ይሰራሉ፡፡ ተፎካካሪዎች ግን የሌሎችን ስኬት ሲመለከቱ ይቀናሉ እነሱን በመጣል መነሳት የሚችሉ ይመስላቸዋል፡፡ ተወዳዳሪዎች የወቅቱን ሁኔታ እያዩ ከለውጥ ጋር አብረው ይራመዳሉ፣ ካለማቋረጥ ራሳቸውን በማዘመን ያሻሽላሉ፡፡ ተፎካካሪዎች ግን ስለሌላው ሰው ሲያወሩ ጊዜ ስለሚያልፍባቸው ወደ ኋላ ይቀራሉ፡፡ ተወዳዳሪዎች ራእያቸውንና ዓላማቸውን ያውቃሉ፣ ከዚያም አንጻ ስኬታማነታቸውን ይመዝናሉ፡፡ ተፎካካሪዎች ግን ማን ምን እንዳደረገ እና እንዳላደረገ ሲመለከቱ ውለው ያድራሉ፣ ስኬታማነታቸውንም የሚመዝኑት ከማን እንደበለጡ በማየት ነው፡፡ ተወዳዳሪ መሆን ማለት የእኛን ስኬታማነት ከራሳችን ዓላማ እና ግብ ጋር በማነጻጸር መኖርና ካለማቋረጥ ወደዚያ ማደግ ማለት ነው፡፡ ተፎካካሪነት አሉታዊ ኃይል ሲሆን፣ ተወዳዳሪነት አዎንታዊ ኃይል ነው፡፡ ተፎካካሪነት ለመታየት ከመፈለግ ሲነሳ፣ ተወዳዳሪነት በውስጠ-ህልና ራእይን ከማየት ነው የሚነሳው፡፡ ይህንን አስገራሚ ሕይወት በለማመድ ከተፎካካሪት ወደ ተወዳዳሪነት ለመሸጋገር ከፈለጋችሁ በቅርቡ የሚሰጠው ስልጠና ይጠቅማችኋልና በመመዝገብ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ተመዝጋቢዎች ሰልጣኞች ጋር ተቀላቀሉ፡፡ ስልጠናው የሚሰጠው ለአምስት ተከታታይ ኃሙስ ምሽቶች ይሆናል፡፡ የስልጠኛው ርእስ፡ “በራእይ የሚመራ ሕይወት” የስልጠናው ቀናት፡ ጥቅምት 14፣ 21፣ 28 እንዲሁም ሕዳር 5 እና 12 የስልጠናው ሰዓት፡ አምስቱም ኃሙሶች ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 (በኢትዮጲያ አቆጣጠር) የክፍያ መረጃ፡ ለአምስቱም ኃሙሶች ጠቅላላ ክፍያ 1ሺህ ብር ብቻ በዚህ ስልጠና ለመሳተፍ ፈቃደኛነታችሁን በ @DrEyobmamo ኢንቦክስ ለምትገልጹ ብቻ የምዝገባ ሂደቱን መመሪያ እና መረጃ እናደርሳለን፡፡ የክፍያ መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁ በኋላ ለዚሁ ስልጠና ወደሚዘጋጀው ቴሌግራም ግሩፕ ውስጥ እንጨምራችኋለን (add እናደርጋችኋለን)፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂደዋል ። (መስከረም 28/2017 ዓ.ም) በ3 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈባቸው
+2
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 4ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂደዋል ። (መስከረም 28/2017 ዓ.ም) በ3 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ፡- 1 ኛ. የኮሪደር ልማት የግዥ ጥያቄ ፣ የግንባታ በጀት እና የግዢ ሂደት አወሳሰን በተመለከተ በፋይናንስ ቢሮ በኩል ለቀረበልን ጥያቄም፤ ለልማቱ መሳለጥ እና የሀብት መባከን እንዳይፈጠር እንዲሁም የሥራ ቅልጥፍናን በሚጨምር መንገድ ለመስራት እንዲያስችል የሚያደርግ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተወያይተን አፅድቀዋል :: 2ኛ. በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት የሚተዳደሩ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን አያያዝ ላይ ያሉ ክፍተቶችን ለማረም እና ወደ ከተማው ደረጃውን የጠበቀ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አስተዳደር ዘይቤ ማምጣት እንዲያስችሉ ተቋማቱ በትምህርት ቢሮ ይዞታ ማዕቀፍ ውስጥ እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ደንብ አስፈላጊ በመሆኑ አፅድቀዋል። 3ኛ. የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሰው ኃይል ስምሪት በማዕከል ፣ በክ/ ከተማ እና በወረዳ ለማመጣጠን እንዲቻል በተዘጋጀው የዝውውር እና ምደባ ረቂቅ ደንብ በየተቋማቱ ያለንን የሰው ሀብት በውጤታማነት ለመጠቀም እንዲያችል የሚያግዝ በመሆኑ በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል። መስከረም 28/2017 አዲስ አበባ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728 TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau

#ማስታወቂያ
ቀን 26/01/2017 ዓ.ም ለሁሉም የመንግስት እና የግል ቅደመ አንደኛ (ኬጅ)ትምህርት ቤቶች በሙሉ፣ ከሠኞ መስከረም 27/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 30/2017 ዓ.ም ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የፖሊዮ በሽታ ክትባት በአዲስአበባ ከተማ ጤና ቢሮ አማካኝነት ይሰጣል። በመሆኑም የጤና ቢሮ የህክምና ባለሙያዎች ወደ ተቋማችሁ ሲመጡ ህጋዊ መታወቂያ በመጠየቅ አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉላቸው እናሳስባለን ። #ማሳሰቢያ:- 1)ክትባቱ የሚሰጠው ከዚህ ቀደም ለተከተቡም ላልተከተቡም ህፃናት ነው። 2)ክትባቱ ከአንድ ወር በኋላ በድጋሜ ለሁም ህፃናት ይሰጣል።
#አንድም ህፃን በፖሊዮ በሽታ ሊጠቃ አይገባውም!

በቀስተ ዳመና ቅድመ አንደኛ ት/ቤት ከ5 አመት በታች የሆኑትን ተማሪዎች በዛሪው ዕለት የፓሊዮ ክትባት በጤና ባለሙያወች ተሰጥቷል

+2
Snapchat-1406373325.jpg7.97 KB

በቀን 12/01/2017ዓ.ም በበጎ አድራጎት ክበብ አማካኝነት የተማሪ ወላጆች፣ መምህራን የተሳተፉበት የእጣ ትኬት በዚህ ሁኔታ እድለኞች ተለይተዋል። 27/01/2017

እነኳን አደረሳችሁ ለኢሬቻ በዓል! ነገ ከሰዓት  በኋላ ትራንስፖርት ሊኖር ስለማይችል(ስለሚዘጋጋ) በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች ትምህርት ዝግ ይሆናል፡፡ Akkam  Bultan?  Guyyaa Borii Sa’aa  Boodaa Karaan Waan Cuccufamuuf Barnoonni  Sa’aa Duraa Malee Sa’a Booda hin jiru