en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በአድስ ኪዳን በተደጋጋሚ ግልጽ የሆነ የእግዚአብሔር ዓላማ ተገልጧል። እግዚአብሔር አላማውን ለውጦ አያውቅም። በአድስ ኪዳን እንደተገለጠው የእግዚአብሔር የመጀመሪያው አላማ( Objective) መንግስቱን በምድር መመስረት ነዉ። የኛንም የእግዚአብሔር ልጆች (Primary Concern) ሊሆን የሚገባው የመጀመሪያው ጉዳይ ይሄው ነዉ። “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።” — ማቴዎስ 6፥33 በምድር ለይ ሰዎች ሁሉ የምሹትን ፍጹም ሰላም ፤ ደስታ እና ፍትህ ሊያመጣ የምችል አንድም መንግስት ወይም የ ፖሎቲካ ቡድን የለም አይኖርምም። ይሄንን የሰዎች ሁሉ ፍላጎት ማሟላት የምችለው ብቸኛው መንግስት በተባረከው ጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ገዥነት የሚመሰረተው ዘላለማዊ መንግስት ብቻ ነዉ። “ስለ ልጁ ግን፦ አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ እስከ ዘላለም ድረስ ይኖራል፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው።” — ዕብራውያን 1፥8 በጣም የሚገርመው ግን ልዑል እግዚአብሔር በዝህ መንግስት ግንባታ ውስጥ ለእኛ ለምናምን ድርሻ መስጠቱ ነዉ። እግዚአብሔር ለፍጥረቱ ሁሉ ካለው ትልቅ ዓላማ ወይም እቅድ ጋር የሚስማማ ልዩ ልዩ እቅድ ለእያንዳንዳችን አለው። አንተ/ች አንድ ድንቅ ነገር ለመስራት በእግዚአብሔር ተጠርተሃል/ሻል። “ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን።” — ኤፌሶን 2፥10 (አዲሱ መ.ት) ➤ መልካሙ ስራ ይሄ ነዉ ማለት ባልችልም(For you Specifically)*ነገር ግን በእግዚአብሔር መንግስት ግንባታ ውስጥ መልካም ተጽዕኖ የምኖረው ነገር ነዉ። አንዳንዶቻችን ወንጌልን ለመስበክ (በስብከት ፤ በመዝሙር ...ወዘተ ሌሎች ደግሞ የፖሎቲካውን ተራራ ወይም የኢኮኖሚውን ተራራ ወይም የ ሚድያውን ተራራ...ወዘተ ለእግዚአብሔር መንግስት ጥቅም ለመቆጣጠር ተጠርታችኋል። በጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር እና ከቃሉ ጊዜ በመውሰድ /to the specific/ እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ያለውን አላማ በማወቅ የእግዚአብሔርን መንግስት በምድር እንድትገዛ ፍጹም ትጋት አሳዩ። መንፈስ ቅዱስ የሚናገራችሁ ነገር ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የሚጣረስ አይሆንም ነገር ግን ለግላችሁ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር በሚስማማ መልኩ ይናገራችኃል( it will never be out of scriptures, but it will be scriptural that's made personal for you by the holy Spirit, so open yourself to hear the Voice of God). 👉መቼም መረሳት የሌለበት እውነት: “..‘በመንፈሴ እንጂ በኀይልና በብርታት አይደለም’ ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት።” — ዘካርያስ 4፥6 (አዲሱ መ.ት) #መንግስትህ_ትምጣ🙏 አሜን። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ቀን ከእናንተ ጋር የነበረ እግዚአብሔር ስመሽም ከእናንተው ጋር ነዉ። እርሱ ጊዜ እና ሁኔታ አይለውጠውም። አሁን ባላችሁበት የእግዚአብሔር መንፈስ ህልውና እንድታወቃችሁ ጸሎቴ ነዉ። "...እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።” — ማቴዎስ 28፥19-20

“አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው።” — መዝሙር 119፥97 #ትዝታዬ_ቃሉ_ነዉ።

Amazing Grace How sweet the sound That saved a wretch like me I once was lost But now I'm Found Was blind but now I see It was Grace that taught My Heart to Fear And Grace my fears Relived How Precious Did That Grace Appear The Hour I First Believed Through Many Dangers Toils And Shares We Have Already Come It was Grace That Brought Us safe thus far And Grace Will lead us home When we have Been there Ten thousand years Bright Shunning As The Sun We have no less days To sing Gods Praise Then When we have First Begun @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉አድሱ የ LOCKDOWN ሕግ ሁሉም ሰው በጥንቃቄ ይከተለው! ➤ልባችሁን በኢየሱስ ደም መታጠብ እና ማንጻት። (መዝሙር 73 ፥ 1) ➤ከክፉ ሁሉ ማህበራዊ እርቀትን መጠበቅ። (ኢዮብ 28 ፥ 28) ➤ከ ፌዘኞች ጋር የሚኖርን መቀራረብ ፈጽሞ ማስወገድ። (መዝሙር 1 ፥ 1) ➤አእምሮን በ ኃጢአት እና ጥላቻ እንዳይበከል መሸፈን። (ዘሌዋውያን 19 ፥ 17) ➤ለእግዚአብሔር ጸያፍ ከሆነው ሁሉ ጋር በእጅ አለመጨባበጥ። (ዘዳግም 25 ፥ 16) ➤ሐሰተኛ ትምህርትን አቅፎ አለመቀበል። (2ኛ ጴጥሮስ 2 ፥ 1) ➤የእግዚአብሔርን ማዳን ተስፋ ማድረግ።(ኤርምያስ 17 ፥ 14) ➤ሕይወታችሁን በእግዚአብሔር ቃል ሳንታይዝ(Sanitize) ማድረግ። (መዝሙር 1 ፥ 2) ➤ምንአልባት የተለየ የኃጢአት ምልክት የሚያዩ ከሆነ ወደ ክርስቶስ ፀሎት በተባለው መስመር ይደውሉ። (ኤርምያስ 33 ፥ 3) ➤መንፈሳዊ immunity'ን በእምነት እና በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ከፍ ማድረግን ሁልጊዜ ያስታወሱ። ( ይሁዳ 1 ፥ 20) አሜን🙏 #PastorChris @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔርን ድምጽ ከራሴ አእምሮ ድምጽ እና ከሌሎች ድምጾች እንዴት መለየት እችላለሁ? ይህን ስሙት ለሌሎችም share አድርጉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እውነተኛ መንፈሳዊነት ሁልጊዜ የሚጀምረው በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ አምኖ ዳግም በመወለድ ነዉ። ሰዎች መንፈሳዊነትን በራሳቸው መንገድ ለመከወን ስሞክሩ ማየት የተለመደ ነዉ። አንዳንድ መንፈሳዊ ለመሆን ይጾማል ከሰው ተለይቶ ይኖራል ከመብል እና ከመጠጥ ሰውነቱን ይከለክላል አለባበሱን እና የሰውነቱን ሁኔታ ይለውጣል...ወዘተ። ነገር ግን ይህ ሁሉ ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያበቃ እውነት አይደለም። መንፈሳዊ ለመሆን የሚወድ ሁሉ እግዚአብሔር ያቀረበውን መንገድ መቀበል አለበት። ይህም መንገድ ደግም መወለድ ነዉ። 👉እውነተኛ መንፈሳዊነት~እግዚአብሔርን መምሰል ነዉ። #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

photo content

#ዛሬ_ወስን #ወስኝ። ምክንያቱም አለመወሰን ራሱ ላለመወን መወሰን ነዉና። አንተ ወስነህ ነገሮችን እስካልቀየርክ ድረስ በዚህ ሕይወት ውስጥ #በጊዜ #እርዝመት #ብቻ #በራሱ የሚቀየር ነገር የለም። ጊዜ ነገሮችን ይለውጣል ብሎ መጠበቅ #የሞኞች #ባዶ_ተስፋ ነዉ። ጊዜ እግዚአብሔር የሚሰጠን #እንድንሰራበት እንጅ #እንድሰራልን አይደለም። እመኑኝ ጊዜ አንድም ነገር አይለውጥም። በጊዜ ውስጥ ግን እናንተ ነገሮችን መለወጥ ትችላላችሁ። ግድየላችሁም ዛሬ ወስኑ። እግዚአብሔር ያሳያችሁን ለመከተል እና ለመሆን ወስኑ። #ትችላላችሁ። የእግዚአብሔር ዘር ናችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

ከዛሬ ምሽት በኃላ በኢየሱስ ስም ሰማያት ይከፈቱላችሁ።

“በዘላለም መንፈስ አማካይነት ራሱን ነውር አልባ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ያቀረበው የክርስቶስ ደም ሕያው እግዚአብሔርን እንድናመልክ ኅሊናችንን ከምውት ሥራ እንዴት ይበልጥ ያነጻ ይሆን!” — ዕብራውያን 9፥14 (አዲሱ መ.ት) የክርስቶስ ደም ኃጢአቴን ብቻ ሰይሆን ህሊናዬንም አንጽቶታል። ክብር ይሁንለት። @TheDeepThingsOfTheSpirit

Nothing but the blood of Jesus! Be blessed in Jesus Christ name. @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሰይጣን በተደጋጋሚ እናንተ የሚያጠቃበት የመጀመሪያው መሳሪያው "የበደለኝነት ስሜት" ነዉ። እውነተኛ ንሰሐ ከደረጋችሁ በኃላም ይህንን የጸጸት ስሜት ማምለጥ ከቃታችሁ ሰይጣን እንጂ መንፈስ ቅዱስ እንዳልሆነ እወቁ። በኢየሱስ ደም የመንጻታችሁንም ምስክርነት ደጋግማችሁ ተናገሩ። #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዛሬ የተባረከ ቀን ነዉ። የእግዚአብሔር መንፈስ ይሙላባችሁ።

“ሳታቋርጡ ጸልዩ፤” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥17 ሳያቋርጡ መጸለይ የሚቻል ይሆን? አዎ በሚገባ ይቻላል! እንደዚህ ባይሆን እንድናደርገው ባልተነገረን ነበር። 1-ጸሎት መንፈሳዊ ልምምድ እንጅ በፍጹም ከንቱ ሃይማኖታዊ ስርዓት አይደለም። የውጫዊ ሰውነታችን ሁኔታ [The position of our body] ይህ ነዉ የሚባል ፋይዳ የሌውም። ተንበርክከን አልያም ቆመን ወይም ተኝተን ወዘተ በዬትኛውም አካላዊ ሁኔታ ለይ ሆነን መጸለይ እና እግዚአብሔርን ማውራት እንችላለን። እያንዳንዱ ሰው የራሱን መንፈስ እና አእምሮ የማይረብሸውን መንገድ መርጦ መጸለይ ግን ይኖርበታል። 2-ጸሎት መናገር ብቻ ሰይሆን መነጋገር ነዉ [Prayer is not a monolog, it's a dialog] በሁለት አካላት መካከል የሚደረግ ንግግር ነዉ። በጸሎት ጊዜ የሚናገር አንደበት ብቻ ሰይሆን የሚሰሙ ጆሮዎችም [spiritual Understanding] ያስፈልጓችኃል። ልባችን[Our mind] የንግግር ጣቢያ ነዉ። ስለዚህ ድምጽ አብዛኛውን ጊዜ የሚትሰሙት ከውጭ ባለው ጆሮ ሰይሆን በውስጥ ልባችሁ[Understanding] ነዉ። [Pray without ceasing] ስትራመዱ ተቀምጣችሁ ቆማችሁ ስራ እየሰራችሁ በልባችሁ ያለማቋረጥ ጸልዩ። #spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን።” — ዕብራውያን 11፥3 #የሚታየው ነገር #ከሚታዩት_እንዳልሆነ የምናስታውል ከሆነ ሌላ አንድ ነገር ማስተዋል መቻል አለብን ይህም "ከሚታየው በላይ የማይታየው እሁን መሆኑን ነዉ"። ይሄ ለሁላችንም ግልጽ ነዉ ከወንዙ በለይ ምንጩ እሁን ነዉ። ወንዙ ህልውናውን ያገኘው ከምንጩ ነዉ። ምንጩን ማቆጣጠር ከቻላችሁ ወንዙን በፈለጋችሁት መልኩ መቆጣጠር ትችላላችሁ። ዓላም እጅግ ብዙ ችግሮች ያሏት ብሆንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተው ግን #የኃጢአት_መስዋዕት ሆኖ ነዉ። ለምን? ምክንያቱም ኃጢአት የሁሉም ችግሮች ምንጭ በመሆኑ ነዉ። ባህሩን ማድረቅ ከተቻለ አሶችን ሁሉ በራሳቸው ይሞታሉ። በዚህ አውድ መንፈሳዊነት ከችግሮቻችሁ በላይ የችግሮቻችሁን ምንጭ እንድትፈልጉ እንድታውቁትና እንድታደርቁት ይመራችኋል። ዋናው ችግር እሱም ኃጢአት በኢየሱስ ተሸንፏል። ሌሎችን የኃጢአት ውጤቶች እና ምርቶች ኢየሱስ ለምን ተዋቸው ትሉ ይሆናል መልሱ ቀላል ነዉ እግዚአብሔር እነደ ራሱ ተዋጊ ልጆች ይፈልጋል። እጆቻችንን ጦርነት ጣቶቻችንን ውጊያ እያስተማራቸው ነዉ። ተግዳሮቶች መውደድ ያለባችሁ ለዚህ ነዉ። ምክንያቱም የትኛውንም ተግዳሮት የማሸነፍ ብቃት ውስጣችሁ አለ። ነገር ግን ሁልጊዜ ከችግሮቻችሁ በስተጀርባ ያለውን #ስውር እጅ የሚያዩ አይኖች ባለቤት መሆን ይኖርባችኋል። #SpiritStyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሰዎች (ፍጥረታዊ ሰዎች) በሚሰሙት እና በሚያዩት ነዉ የሚመላለሱት። የመረጃ ምንጫቸው የሚያዩት ነዉ። የሚታየው ለነሱ እሁን ነዉ ከዚህም የላቀ እሁን የሆነ ነገር አለ ብለው አያምኑም። እግዚአብሔርን እና መንፈሳዊ ዓለምን ላቦራቶሪ ውስጥ ልትገልጣቸዉ የማትችል ከሆነ የሉም ማለት ነዉ ይላሉ። ነገር ግን የነዚህ ሰዎች ሰይንስ ፈጽሞ የማያብራራቸው ነገሮች አሉ። እሩቅ ስንሄድ ሁላችንም ንፋስ እንዳለ እናውቃለን አይተነው ወይም አሽተትነዉ አናውቅም ነገር ግን ንፋስ የሚያስከትለው ተጽዕኖ ለሁላችንም ግልጽ ነዉ። መንፈሳዊነት የማይታየውን ማየት ነዉ። እውነተኛ መንፈሳዊነት ንፋሱን እና ወጀቡን ማብራራት ሰይሆን ከንፋሱና ከወጀቡ በስተጀርባ ያለውን እጅ ማየት ነዉ። ደግም የተወለደ ሁሉ እውነተኛ መንፈሳዊ ጉዞ ጀምሯል። ደግም መወለድ ግን የጉዞው መጀመሪያ ብቻ እንጅ መጨረሻ አይደለም። የሚኬድ ብዙ ጎዳና አለ። እውነተኛ መንፈሳዊነት እግዚአብሔርን ራሱን እስከመምሰል የሚያደርስ ትልቅ ትጋት የሚጠይቅ መንገድ ነዉ። #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

DUNAMIS!!!!
DUNAMIS!!!!

ዋጋዬ ኢየሱስ ነዉ። ሃሌሉያ።

If you're busy posting on social media your Pics it's a sure sign that you are trying to gain a vain validation from people and you are not yet discovered yourself. Friends don't waste your time. Discover who you are and start living. #SpiritStyle. @TheDeepThingsOfTheSpirit