en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ ትናንት መንፈስ ቅዱስ ሰለ ኢትዮጵያ ያሳየኝ ነገር አለ: አብረውኝ የሚጸልዩ 60 ሰዎች ካገኘው መልእክቱን አስተላልፋለሁ: አብሮኝ የሚጸልይ🖐

እግዚአብሔር የሰጠንን ስናስብ አብዛኛዎቻችን ብንችል ለእግዚአብሔር የሆነ ነገር ብንሰጥ ብለን እንመኛለን: ይህ ምኞት ጤነኛ ነዉ😊 ለእግዚአብሔር መስጠት የምንችለው አንድ ነገር አላን እርሱም ሰውነታችን ነዉ: የእግዚአብሔርን ፈቃድ በማወቅ ሰውነታችንን ከዓለም እና ከኃጢአት ተጽእኖ በማላቀቅ ለእግዚአብሔር ብቻ መሰዋት እንችላለን። እግዚአብሔር የሚኖርበት መቅደስ አድርጋችሁ ሰውነታችሁን አቅርቡ😍🔥 @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሮሜ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። ² የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

ቤተክርስቲያንን እወዳታለሁ❤

🦋🔥 ፍጹም ለውጥ በሕይወታችሁ ይሁን በኢየሱስ ስም🔥🦋

ራስህን ስራ! ተስፋ አትቁረጥ። ምክንያቱም የነገ እንተ የዛሬ እንተ አይደለህም: ነገር ግን ነገ የምትሆነው አንተ ዛሬ በምታደርገው ለይ እንደሚደገፍ አትርሳ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#ᴡᴏʀᴋʜᴀʀᴅ💪 #ɪɴᴠᴇsᴛ ᴏɴ ʏᴏᴜʀsᴇʟғ! ᴅᴏɴ'ᴛ ʟᴏsᴇ ʜᴏᴘᴇ. 𝚠𝚑𝚊𝚝 𝚢𝚘𝚞 𝚊𝚛𝚎 𝚝𝚘𝚍𝚊𝚢 𝚒𝚜 𝚗𝚘𝚝 𝚠𝚑𝚊𝚝 𝚢𝚘𝚞 𝚠𝚒𝚕𝚕 𝚋𝚎 𝚝𝚘𝚖𝚘𝚛𝚛𝚘𝚠, 𝚢𝚎𝚝 ɴᴇᴠᴇʀ ғᴏʀɢᴇᴛ 𝚝𝚑𝚊𝚝 ᴡʜᴏ 𝚢𝚘𝚞 𝚠𝚒𝚕𝚕 𝚋𝚎 𝚝𝚘𝚖𝚘𝚛𝚛𝚘𝚠 ᴅᴇᴘᴇɴᴅs 𝚘𝚗 𝚠𝚑𝚊𝚝 𝚢𝚘𝚞 ᴅᴏ 𝚝𝚘𝚍𝚊𝚢. @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሉቃስ 13 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁶ ይህንም ምሳሌ አለ፦ ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው፥ ፍሬም ሊፈልግባት መጥቶ ምንም አላገኘም። ⁷ የወይን አትክልት ሠራተኛውንም፦ እነሆ፥ ከዚህች በለስ ፍሬ ልፈልግ ሦስት ዓመት እየመጣሁ ምንም አላገኘሁም፤ ቍረጣት፤ ስለ ምን ደግሞ መሬቱን ታጐሳቍላለች? አለው። ⁸ እርሱ ግን መልሶ፦ ጌታ ሆይ፥ ዙሪያዋን እስክኰተኵትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት። ⁹ ወደ ፊትም ብታፈራ፥ ደኅና ነው፤ ያለዚያ ግን ትቈርጣታለህ አለው።

የእግዚአብሔር ልጆች በክርስቶስ የተደረጋችሁትን እና የሆናችሁትን ለማወቅ በርቱ: ማንነት ዋጋ አለውና! በክርስቶስ ማን እንደሆናችሁ ስታውቁ ከዓለም ከኃጢአት እና ከሰይጣን በላይ እንደሆናችሁ ታውቃላችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።” — 2ኛ ቆሮ 5፥16 የእግዚአብሔር ልጆች በክርስቶስ የምናውቀው እግዚአብሔርን ብቻ አይደለም! እራሳችንንም የምናውቀው ልናውቀውም የሚገባው በክርስቶስ ነዉ። በፍጹም ራሳችሁን በስጋ በቤተሰባችሁ: በተወለዳችሁበት መንደር ወይም ሁኔታ አትወቁ: ማንም ከምድር ተነስቶ እናንተን እንድያብራራ አትፈቀዱ: እናንተን እራሳችሁም ሌሎችም ማወቅ ያለባቸው በክርስቶስ ነዉ። በፍጹም ምድራዊ ወይም ስጋዊ አይደላችሁም! በክርስቶስ ራሳችሁን ማወቅ ስትጀምሩ ጽድቅ ሰላምና ደስታ ዓለማችሁ: ተስፋ እምነትና ፍቅር በህላችሁ: ሃይል አሸናፊነት እና ገዥነት የሕይወት ስርዓታችሁ ይሆናል! የእግዚአብሔር ልጆች በክርስቶስ ራሳችሁን እንድታውቁ አበረታታችኋለው: በክርስቶስ ያለንን ማንነት የተረዳን ቀን ፍጥረት ከምጥ ያርፋል። 👉ከዚህ ዓለም የማመዛዘን አቅም ባለይ ነን!!! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉የእግዚአብሔር ልጆች በመንፈስ ሃይል የማይታደስ የሕይወት ፍርስራሽ የለም! ለፍርስራሻችሁ እናገራለሁ የትኛውም የፈረሰ ነገራችሁ በመንፈስ ሃይል ይታደስ! መንፈሳዊ ልምምዳችሁ ብሆን ስራችሁ ብሆን ግንኙነቶች ብሆኑ ጤናችሁ ቢሆን አሁን 🔥 በመንፈስ ሃይል ይታደስ! አሜን አሜን 🔥 @TheDeepThingsOfTheSpirit

የዛሬ ማታ ጥቅስ: “ጢሞቴዎስ ልጄ ሆይ፥ አስቀድሞ ስለ አንተ እንደ ተነገረው ትንቢት፥ በእርሱ መልካም ጦርነት ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ፤” — 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥18 👉ተዋጋ ✍️ብዙ ሰዎች ትንቢት ተነግሯቸዋል: ነገር ግን የሰማሁት ትንቢት አልተፈጸመም የሚሉ ሙግት እና ቅሬታ ብዙዎች አላቸው: ትንቢት እንድፈጸም ትንቢቱ ምን አይነት እንደሆነ ማወቅ የግድ ነዉ: የአብዛኛዎቹ ትንቢቶች ተፈጻሚነት በእናንተ ለይ የሚደገፍ ነዉ። የሁሉም አላልኩም የአብዛኛዎቹ ነዉ ያልኩት። ለዚህ ነዉ "ተዋጉ" ያልኳችሁ። ከላይ በስቀመጥኩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ መንፈሳዊ ልጁን "በሰማሀው ትንቢት መሰረት ተዋጋ" ይለዋል። ይህንንም ውጊያ "መልካም ውጊያ" በማለት ይገልጸዋል። ተወዳጆች ሆይ እኔም ይህንኑ ምክር ነዉ ዛሬ የምለግሳችሁ: ትንቢት ሰምታችሁ የምታውቁ ከሆነ እና ትንቢቱ እንድፈጸም የምትፈልጉ ከሆነ: መልካም ውጊያ ማድረግ ጀምሩ!!! ተነሱና ተዋጉ: የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማድረግ ሃይል አላችሁ። ጸሎት:- እግዚአብሔር ሆይ ፈቃድህን ለመፈጸም ሃይል እንዳለኝ አውቅያለሁ! በፀጋህ ጉልበት ፈቃድህን ለማድረግ መልካሙን ውጊያ እዋጋለሁ! የውጊያ መንፈስ አግኝቶኛል። አሜን🔥🔥🔥 ድል ከመሳሪያ በላይ ከጦርነት መንፈስ ጋር የተያያዘ ነዉ። ተነሱና ተዋጉ: የሰማችሁትን ትንቢት አድርጉት። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ድንቅ መልእክት ያለው መልእክት -በዘመኔ አያለሁ- አስቴር አበበ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በምድሬ ለይ እግዚአብሔርን በክብሩ ከፍ ብሎ አየዋለሁ!!! አሜን አሜን🔥

እግዚአብሔርን በክብሩ ማየት ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ “ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፥ የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር።” — ኢሳይያስ 6፥1 ✍️የዖዝያን መሞት እና የእግዚአብሔር በክብሩ መታየት የሚያገናኛቸው ሚስጢር ይህ ነዉ: ዖዝያን በኢየሩሳሌም የነበረ የይሁዳ ንጉሥ ነበር: በ 16 ዓመቱ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለመግዛት ክብር ያገኘ ስሆን አምሳ ሁለት አመት በኢየሩሳሌም ሆኖ ነግሷል። ዖዝያን ዘካርያስ እግዚአብሔርን መፍራት ባስተማረው ዘመን ሁሉ: እግዚአብሔር የተከተለ በመሆኑ እግዚአብሔር ደግሞ በምላሹ አስገራሚ መከናወን ሰጥቶ ነበር: በሁሉም እረገድ ነገሩ ተከናወነለት: በኢየሩሳሌም ዝርያ ምሽጎች ሰራ: ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት ገነባ: በሌሎች ሃገራት ሁሉ የራሱ ከተሞች ነበሩት: እግዚአብሔር ዝናብን በየወቅቱ ይሰጥ ነበረና በግብርናውም በኩል ትልቅ ስኬት ማስመዝገብ ችሎ ነበር: የሚዘራው መቶ አፍርቷል የሚተክለውን አለምልሟል ከዚህም በላይ ከብቶች እና ሌሎች እንስሳት በስተውለት ነበር....ይህንን ስኬት መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚህ ይገልጸዋል: “... እስኪበረታም ድረስ እግዚአብሔር በድንቅ ረድቶታልና ዝናው እስከ ሩቅ ድረስ ተሰማ።” — 2 ዜና 26፥15 ዖዝያን በእግዚአብሔር የተረዳ ንጉሥ የነበረ ቢሆንም በበረታ ጊዜ ወይም መንግሥቱ በጸናለት ጊዜ እብሪተኛ ልብ ሆነለት: ይህም ያበረታውን አምላኩን እግዚአብሔር በመበደል ለውድቀት ዳረገው። “ነገር ግን በበረታ ጊዜ ለጥፋት ልቡ ታበየ፥ አምላኩንም እግዚአብሔርን በደለ፤ ወደ መቅደስ ገብቶ በዕጣን መሠዊያ ላይ ዐጠነ።” — 2 ዜና 26፥16 ✍️ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ማጠን: ለዚህ ስራ የተቀደሱ የአሮን ልጆች የካህናት ተግባር እንጅ የነገስታት ተግባር አልነበረም። ዖዝያን ግን ነገሩ ሁሉ እንደተከናወነለት ባየ ጊዜ ለማጠን እንኳ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት እንዳለው እስክሰማው ድረስ ልቡ ታበየ። በዚህም #በትዕቢት ተነሳስቶ የጸናውን የእግዚአብሔርን ስርዓት በመተው: ወደ ቤተመቅደስ ገብቶ በመሠዊያው ለይ ለእግዚአብሔር ለማጠን ሞከረ: ነገር ግን እግዚአብሔር በዚህ ተግባሩ እጅግ ተቆጥቶ በተቀደሱት ካህናት ፊት በዚያው ቤተመቅደስ ውስጥ በመሰዊያው ፊት ዖዝያን ጥናውን በእጁ እንደያዘ: ስለቀሰፈው: ለምጽ በግንባሩ ለይ ታየ። በዚህም እግዚአብሔር እብሪተኛ ልብን ወይም ትዕቢትን የቱን የህል እንደሚቀጣ አሳየ። 👉መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር በግሉ ወይም በራሱ "ይቃወማል" የተባለው "ትዕብተኛን ሰው" ነዉ! እግዚአብሔር የሚቃወመው ሰው ምን ይደርስበት ይሁን!?( 1ኛ ጴጥሮስ 5:5) ✍️የዖዝያን መሞት እና የእግዚአብሔር በክብሩ መታየት የሚያገናኛቸው ሚስጥር ይሄ ነዉ: ዖዝያን በዚህ ክፍል የትዕቢት ተምሳሌት ሆኖ ነዉ የቀረበው: በመሆኑም ትዕቢት ስሞት እግዚአብሔር በክብሩ መታየቱን በግልጽ የሚያሳይ ነዉ። ዖዝያን የእስራኤል ልብ በሆነችው በእየሩሳሌም የነበረ በስልጣን ደግሞ የይሁዳ ትልቁ ሰው በመሆኑ የእሱ ትዕቢት እንደብሔራዊ ኃጢአት ነዉ: የሱ ትዕቢት ወድቀት ደግሞ እንደ ብሔራዊ ድል ነዉ። በግል ሕይወታቸውን በቤተክርስቲያናችን እና በሃገራችን እግዚአብሔርን በክብሩ ተገልጦ ማየት የምንሻ ከሆነ: እያንዳንዳችን ትዕቢትን የመግደል ሃላፊነት አለብን። ትዕቢት በሞተበት አመት የእግዚአብሔር ክብር ይገለጣል: ምድርም ከክብሩ ትሞላለች!!! ✍️በመጨረሻም ትልቁ ትዕቢት አለመጸለይ ነዉ! የማይጸልይ ክርስትያን ትዕቢተኛ ነዉ: የማትጸልይ ቤተክርስቲያን ትዕቢተኛ ሆናለች: የማትጸልይ ሃገር ትዕቢተኛ ናት! 👉ትዕቢትን እንግደል ትሁታን እንሁን! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ከላይ ያለውን የመጽሐፍ ክፍል በጸሎት በቀስታ እና በተደጋጋሚ አንብቡት: እና የዖዝያን መሞት እና የእግዚአብሔር ክብር መታየት ምን እንደሚያገናኛቸው ከመንፈስ ቅዱስ ተማሩ። (ሁለተኛ ዜና 26 ሙሉ ምዕራፍ የዖዝያንን የሕይወት ዘመን እና ተግባር የሚተርክ ክፍል ነዉ ስለዚህ አንብቡት) 👉የእግዚአብሔርን ክብር የምናይበት ሚስጥር በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለይ እናገኘዋለን።

ኢሳይያስ 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፥ የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር። ² ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር፥ ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው፤ በሁለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ ይበር ነበር። ³ አንዱም ለአንዱ፦ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር። ⁴ የመድረኩም መሠረት ከጭዋኺው ድምፅ የተነሣ ተናወጠ፥ ቤቱንም ጢስ ሞላበት። ⁵ እኔም፦ ከንፈሮቼ የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ! አልሁ። ⁶ ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እኔ መጣ፥ በእጁም ከመሠዊያው በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ። ⁷ አፌንም ዳሰሰበትና፦ እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ አለኝ። ⁸ የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ማንስ ይሄድልናል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ አልሁ።

ሚዛን መጠበቅ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ “... አምላክህ እግዚአብሔር በሚሰጥህ ምድር ላይ ዕድሜህ ይረዝም ዘንድ #እውነተኛና_ፍጹም_ሚዛን_ይሁንልህ፤ እውነተኛና ፍጹም መስፈሪያም ይሁንልህ።” — ዘዳግም 25፥15-16 ኢ-ሚዛናዊነት ወይንም ሚዛንን መጠበቅ የማንችልበት ቦታ በሕይወታችን የክፉ ነገር በር ይሆናል። በእያንዳንዱ ነገር እውነተኛ ፍጹም ሚዛን ልኖረን የሚገባው ለዚህ ነዉ። ይህ እውነተኛ እና ፍጹም ሚዛን ምንድነው? ለእኛ ለምናምን እንደ እግዚአብሔር ቃል ያለ እውነተኛ እና ፍጹም ሚዛን የለም! የእግዚአብሔር ቃል የነገሮች ሁሉ ሚዛን ነዉ እውነት እና ውሸት: ሕይወትና ሞት ኃጢአት እና ጽድቅ ትክክለኛ ዋጋቸው ተመዝኖ የተሰጠን በእግዚአብሔር ቃል ነዉ: የየትኛውም ሰው ወይም ፍጡር ቃል ወይም ምልከታ በእግዚአብሔር ቃል ያልተቃኘ ካልሆነ እውነትነቱ ጥያቄ ውስጥ ነዉ። ምክንያቱም የእውነት ሚዛን የእግዚአብሔር ቃል ነውና። ይህንን የሚላችሁ በአንድ ነገር ዙርያ ብዙ የቤተክርስቲያን ሰዎች ያላቸውን የተሳሳተ ምልከታ ወደ እግዚአብሔር ቃል እውነት ለመቀልበስ እና ለማረም ነዉ። አንድ ወዳጄ የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት ስናገር እና አብረውኝ ለነበሩ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል እውነት ከምንም በላይ አጥብቀው እንድይዙ እና ከቃሉም እውነት የሚጣረስ የትኛው ትምህርት ወይንም አመለካከት ወይንም ልምምድ ፈጹሞ ከሕይወታቸው ማስወገድ እንዳለባቸው በአጽንኦት ስናገር ማህበሩ ውስጥ እሱም ስለነበር ይህንን ጠንካራ ንግግሬን ሰምቶ ነበር: ከዝግጅቱም በኃላ ሰዎች ሁሉ በሌሉበት እንደዚህ አለኝ " አንተ በጣም ቃል ለይ ትኩረት እያደረክ ነዉ ከመንፈሳዊ ነገር ዝቅ እንዳትል እፈራለሁ" አለኝ። ይህ ስሁት አመላካከት ብዙ ክርስትያኖች ጋር ያለ በመሆኑ በጣም ያሳዝናል። በአሁኑ የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት ማወቅ እና የእግዚአብሔርን ቃል መሰረት ማድረግ ከማንፈሳዊነት ዝቅ ያደርጋል???? በፍጹም! አያደርግም። ቃሉና መንፈሱ አንድ ናቸው! የአንድ ሳንትም ሁለት ገጽታዎች ናቸው እንኳ ልንላቸው አንችልም። ምክንያቱም አንድ ናቸው! ተዋህደው ነዉ የሚኖሩት። ጌታችን ኢየሱስ “..እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም ነው።” — ዮሐንስ 6፥63 ....በማለት ገልጾታል። እንደውም እውነታው ይህ ነዉ: የወቃችሁት የእግዚአብሔርን ቃል ከሆነ ከየትኛውም ጊዜ በላይ ለእውነተኛ መንፈሳዊነት ያበቃችኃል! ነገር ግን የእግዚአብሔርን ቃል እያወኩ ነው እያልን ከመንፈሳዊነት ዝቅ እያልን ከመጣን: ያወቅነው ነገር ቀድሞውኑ የእግዚአብሔር ቃል አልነበረም። የእግዚአብሔር ቃል የመንፈሳዊ ዓለም በር ነዉ እንጂ በፍጹም ከመንፈሳዊነት የሚያጎድል አይደለም። በዚህም ምክንያት ነዉ: በቃሉና በመንፈሱ ረገድ ክርስትያኖች የራሳችንን ምልከታ ወደ ጎን ትተን እውነተኛ እና ፍጹም የሆነው ሚዛን ማመን እና መጠበቅ ያለብን። ቃሉና መንፈሱ አንድ ለይ የሚሄዱ እንጅ በፍጹም የሚጣረሱ ወይንም የማይስማሙ አይደሉም። መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር "ቃሉን መንፈሱን በመላክ እንደሚያረጋግጥ" ያስረዳል። ስጀምር ያስቀመጥኩትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በጥንቃቄ ተመልከቱ: እግዚአብሔር በሚሰጠን ርስት ለይ ዘመናችን እንዲረዝም ከፈለግን ማድረግ ያለብን እውነተኛውን እና ፍጹም የሆነውን ሚዛን መጠበቅ ነዉ። ለአንዳንዶቻችን እግዚአብሔር የሰጠን ምድር አገልግሎት ይሆናል: ስለዚህ በአገልግሎት ሩቅ መሄድ የሚፈልግ አገልጋይ ሁሉ ይህንን ሚዛን ይጠብቃል: በዋናነትም የቃሉን እና የመንፈሱን ሚዛናዊነት። 👉ቃል ብቻ ከልክ እና መንፈስ ከሌለህ ትደርቃለህ። 👉መንፈስ ብቻ ከልክ እና ቃል ከሌለህ ትተናለህ። 👉መንፈስና ቃል ከሉህ ግን እግዚአብሔርን ወደመምሰል ታድጋለህ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ለሁለት ቀናት ከአጥቢያ ቤተክርስቲያን ሽማግሌዎች: የተለየዩ ዘርፍ መሪዎች እና ከቤተክርስቲያን አባላት ጋር ጌታ ድንቅ ጊዜ ሰጥቶናል: የእግዚአብሔር መንፈስ በቃል እና በጸሎት መክሮናል አጽናንቶናል አንጾናል። 👉የቃልና የጸሎት ትኩረት የነበረው የመንፈስ ድምፅ እናንተንም ስለሚመለከት በአጭሩ ልጻፍ። የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል: ““ምድሪቱን እንዳላጠፋት ቅጥሩን የሚጠግን፣ በፈረሰውም በኩል በፊቴ የሚቆምላት ሰው ከመካከላቸው ፈለግሁ፤ ነገር ግን አንድም አላገኘሁም።” — ሕዝቅኤል 22፥30 (አዲሱ መ.ት) ✍️እግዚአብሔር በዚህም ትውልድ መካካል አንድ ሰው ወይም አንድ ቤተክርስቲያን ይፈልጋል። ይህ አንድ ሰው ወይም ቤተክርስቲያን ሁለት ተግባር አላቸው:- 1) በትውልድ ቅጥር የመስራት ተግባር ነዉ። 2) በፈረሰው( ክፍት በሆነው) በኩል በትውልዱ ምትክ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም ነዉ። ✍️የመጀመሪያው ተግባር ትርጉም በትውልድ መካካል የእግዚአብሔር ድምጽ የመሆን እና እውነትን ጽድቅን እና ፍርድን የመስበክ የማስተማር እና በማይታዘዙ ልጆች ለይ ከሚመጣው የእግዚአብሔር ቁጣ ትውልድን ለማትረፍ መስራት ነዉ። ✍️ሁለተኛው በፈረሰው በኩል የመቆም ተግባር ደግሞ ለትውልድ የማማለድን ሥራ የመስራት ተግባር ነዉ። እነዚህን ሁለት ግብሮች መፈጸም የምትችል ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር እና በሰው መካከል ያለው የክርስቶስ አካል መሆኗን በስራ ማረጋገጥ ትችላለች። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የሕይወት ማረጋገጫው እድገት ነዉ። ᴛʜᴇ ᴘʀᴏᴏғ ᴏғ ʟɪғᴇ ɪs ɢʀᴏᴡᴛʜ. 👉በሕይወት ያለ ነገር ሁሉ ያድጋል! በመንፈሳዊ ሕይወታችን እያደግን ካልሆነ መንፈሳዊ ሕይወት የለንም ማለት ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit