TheDeepThingsOfGod
Open in Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Show more1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 810
የመገረዝ ምስጥር
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
“ስለዚህ ሁላችሁም ሸለፈታችሁን ትገረዛላችሁ፤ ይህም በእኔና በእናንተ መካከል ላለው ኪዳን ምልክት ይሆናል።”
— ዘፍጥረት 17፥11 (አዲሱ መ.ት)
በሕይወታችን ውስጥ እግዚአብሔር የሰጠንን ተስፋ ለመቀበል የመገረዝ ምስጢር ወሳኝ ነዉ። አብርሃም እስማኤልን የወለደው ከመገረዙ በፊት ስሆን የእግዚአብሔር ኪዳን ግን ከእስማኤል ጋር አልነበረም: እግዚአብሔር ኪዳኑን የሚያቆምለትን የተስፋውን ልጅ ይስሃቅን ለመቀበል እስማኤል የመጣበትን መንገድ መቁረጥ ነበረበት: ስለዚህ እኛም በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሔርን ተስፋ ለመቀበል የእኛ የሆነውን ሥርዓት: እውቀት: ብቃት: ወዘተ የራሳችንን መንገድ ቆርጠን እግዚአብሔር በሚሰጠን ብርሃን መመላለስ ይኖርብናል።
👉ከወንድም_ዳኒ
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ዛሬና ነገ ከሃዋሳ ዉጭ አገልግሎት ለይ ነኝ: የእግዚአብሔር ፀጋ እንድበዛልኝ ጸልዩልኝ!
ሰዎች ይፈቱ: ሰዎች ብርሃን ይብራላቸው ሰዎች ይፈወሱ : ሰዎች ይዳኑ🔥
“ደግሞም መናገር እንደሚገባኝ ቃሉን በግልጽ እንድናገር ጸልዩልኝ።”
— ቆላስይስ 4፥4 (አዲሱ መ.ት)
1 810
ɴᴏᴛʜɪɴɢ 𝚠𝚒𝚕𝚕 𝚌𝚑𝚊𝚗𝚐𝚎 𝚝𝚘 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝚊𝚍𝚟𝚊𝚗𝚝𝚊𝚐𝚎 𝚞𝚗𝚝𝚒𝚕 𝚢𝚘𝚞 ᴄʜᴀɴɢᴇ 𝚝𝚘 𝚌𝚊𝚞𝚜𝚎 𝚌𝚑𝚊𝚗𝚐𝚎𝚜 𝚒𝚗 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝚠𝚘𝚛𝚕𝚍.
=𝚜𝚙𝚒𝚛𝚒𝚝𝚜𝚝𝚢𝚕𝚎
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#ድል_በድል
(ድ)ል የተደረገ:እድለኛ
(ል)ቤ ነበረ:እምቢተኛ
(በ)ፍቅር የዳነ:ህመምተኛ
(ድ)ግስ ነጋሪ:ሆነ ተረኛ
(ል)ዑል የማረከው:ምርኮኛ!!
.
.
.
ራእይ 19 (Revelation)
9፤ እርሱም፡— ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው፡ ብለህ ጻፍ፡ አለኝ። ደግሞም፡— ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ነው፡ አለኝ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የለ መንፈስ ቅዱስ መሪነት የሚደረግ የቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት ግብዝነት ነዉ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
𝚊𝚗𝚢 𝚊𝚝𝚝𝚎𝚖𝚙𝚝 𝚝𝚘 𝚕𝚒𝚟𝚎 𝚊 𝚌𝚑𝚛𝚒𝚜𝚝𝚒𝚊𝚗 𝚕𝚒𝚏𝚎 𝚊𝚗𝚍 𝚜𝚎𝚛𝚟𝚎 𝚝𝚑𝚎 𝚕𝚒𝚟𝚒𝚗𝚐 ɢᴏᴅ 𝚠𝚒𝚝𝚑𝚘𝚞𝚝 𝚝𝚑𝚎 𝚊𝚗𝚘𝚒𝚗𝚝𝚒𝚗𝚐 𝚘𝚏 𝚝𝚑𝚎 𝚙𝚎𝚛𝚜𝚘𝚗 𝚊𝚗𝚍 𝚝𝚑𝚎 𝚙𝚘𝚠𝚎𝚛 𝚘𝚏 𝚝𝚑𝚎 𝚑𝚘𝚕𝚢 𝚜𝚙𝚒𝚛𝚒𝚝 𝚒𝚜 𝚙𝚛𝚒𝚍𝚎.
=ᴠᴏɪᴄᴇ
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ᴛʜᴇʀᴇ ɪs ɴᴏ ʀᴇᴠɪᴠᴀʟ ᴡɪᴛʜᴏᴜᴛ ʀᴇᴘᴇɴᴛᴀɴᴄᴇ!
ያለ እውነተኛ ንስሃ ሪቫይቫል የለም! በሕይወታችን በቤተክርስቲያናችን በሃገራችን እውነተኛ ሪቫይቫል ማየት እና መለማመድ ካለብን የግዴታ እውነተኛ ንስሃና መመለስ ማድረግ አለብን። ከዛም በላይ በቀጣይነት እውነትን ፍርድን እና ፍትህን የሚያደርግ በጽድቅ እና በቅድስና እግዚአብሔርን በመፍራት የተሞላ የሕይወት እና የአኗኗር ስርዓት ልንኖር ያግድ ነዉ።
👉እውነት ነው እግዚአብሔር በዚህ በዘመኑ መጨረሻ የሚሰራው አስፈሪ እና አስደናቂ ስራ አለ: ነገር ግን ማነው ለዚህ ስራ ራሱን ሙሉ በሙሉ የሚሰጥ? ማነው ራሱን ለክብር የሚሆን የጽድቅ እቃ አድርጎ የሚያቀርብ??? ማነው ከዓለም ስርዓት የተጣላ? ማነው ለመላክ የተዘጋጀ????
“በስሜ የተጠራው ሕዝቤ ራሱን አዋርዶ ቢጸልይ፣ ፊቴን ቢፈልግና ከክፉ መንገዱ ቢመለስ፣ ከሰማይ እሰማዋለሁ፤ ኀጢአቱን ይቅር እላለሁ፤ ምድሩንም እፈውሳለሁ።”
— 2 ዜና 7፥14 (አዲሱ መ.ት)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ክብርህ ናፈቀኝ!😥
ለእግዚአብሔር ለአባታችን ህጻናት እንደሆንን እንቆይ: በእሱ ፊት የበቃን ለመምሰል እንሞክር! ማንስ በፊቱ በራሱ ብቁ ልሆን ይችላል!? ሁሌም ክብሩ መሪነቱ ሃይሉ ብርሃኑ ያስፈልገናል: !😥
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር፣ የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 13፥14 (አዲሱ መ.ት)
መንፈስ ቅዱስ ከእኔ ጋር ህብረት ልታደርግ ስለወደድክ እወድሃለሁ!😥
1 810
ይህንን ክፍል አሰላስሉ:
ሉቃስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁷ እርሱም መልሶ፦ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም አሳብህም ውደድ፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው።
²⁸ ኢየሱስም፦ እውነት መለስህ፤ ይህን አድርግ በሕይወትም ትኖራለህ አለው።
1 810
አራዳ ነህ/ነሽ?😁
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
👉በተለምዶ አራዳ የሚለው አገላለጽ የነቃ መሆንን ነገሮችን በቀላሉ የሚያወቅን ወጣት ለመግለጽ የሚጠቀሙበት ቃል ነዉ ወይም ይመስለኛል🤔። እውነት አራዳ ትርጉሙ እሱ ከሆነ: አራዳ ማን እንደሆነ ልንገራችሁ: አራዳ የነቃ (ነቄ😁) ከሆነ አራዳ የበራለት ከሆነ አራዳ የተገለጠለት እና ነገሮችን በቀላሉ የሚረዳ ከሆነ አራዳ እኔ ነኝ! የአራዳነት ትርጉም ይህ ከሆነ በጌታ በኢየሱስ አምኖ እንደዳነ በዓለም ካለው ጥፋት እንዳመለጠ የዓለምን ከንቱነት እና ጠፊ መሆንን እንደተረዳ ማነው አራዳ!? ከዚህም በላይ ነዉ ከሰይጣን ከኃጢአት እና ከሞት በላይ የመሆን ሚስጥር እንደበራለት ማነው አራዳ🤔!? በእግዚአብሔር ቃል ብርሃንና የማይበሰብስን ሕይወት እንደምለማመድ የዘላለም ሕይወት እንዳለው: በእግዚአብሔር ውስጥ ቦታ የማግኘትን ጥበብ አጥብቆ እንደያዘ ማነው አራዳ!? መልሳችሁ ማንም የሚል እንደሆነ አምናለሁ። አራዳነት ነቄነት ከሆነ በፍጹም ጫት መቃም: ስጋራ ማጨስ: ሱር ዝቅ አድርጎ መልበስ: መዋሸት: ተላላቆችን አለማክበር: ነውረኛ ቃላት መናገር ...ወዘተ አራዳነት ልሆን አይችልም። አራዳነት ነቄነት ከሆነ እውነተኛ ክርስትያኖች ናቸው አራዶች: ነቄ ያደረገን በብርሃኑ ያበራን ጌታ ይባረክ።
“ከእናንተ ጥበበኛና አስተዋይ ማን ነው? በመልካም አንዋዋሩ ስራውን በጥበብ የዋህነት ያሳይ።”
— ያዕቆብ 3፥13
Join
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
𝚠𝚑𝚎𝚗 𝚢𝚘𝚞 𝚏𝚒𝚗𝚍 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝚙𝚕𝚊𝚌𝚎 𝚒𝚗 𝚌𝚑𝚛𝚒𝚜𝚝, 𝚢𝚘𝚞 𝚠𝚒𝚕𝚕 𝚒𝚖𝚖𝚎𝚍𝚒𝚊𝚝𝚎𝚕𝚢 𝚜𝚝𝚘𝚙 𝚕𝚘𝚘𝚔𝚒𝚗𝚐 𝚏𝚘𝚛 𝚟𝚊𝚒𝚗 𝚟𝚊𝚕𝚒𝚍𝚊𝚝𝚒𝚘𝚗 𝚏𝚛𝚘𝚖 𝚖𝚎𝚗.
=𝚜𝚙𝚒𝚛𝚒𝚝𝚜𝚝𝚢𝚕𝚎
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“ኢየሱስም እንዲህ አለው፤ “የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤....”
— ዮሐንስ 14፥23 (አዲሱ መ.ት)
ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማል -ፍቅር:
በብሉይ ኪዳን ሰዎች (እስራኤላውያን) እግዚአብሔር ይታዘዙ የነበረው: አብዛኛውን ጊዜ መታዘዝ ይዞት የሚመጣውን በረከት አስበው እና አለመታዘዝ ደግሞ የሚያስከትለውን መዘዝ ፈርተው ነበር። እግዚአብሔር ግን በዚህ መልኩ እንድሆን አልፈለገም። ለዚህ ነዉ በአድስ ኪዳን ለሰው ያለውን ከመታወቅ የሚያልፍ ፍቅር የገለጠው: በዚህም ምክንያት ከፍቅር ተነስተን እንድንታዘዘው ነዉ። ተወዳጅ ሆይ እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የገለጠልህን ፍቅር ስትረዳ ለእግዚአብሔር አለመኖር አትችልም: በእግዚአብሔር በፍቅር ስትኖር ኃጢአትን ማድረግ አትችልም። በፍቅሩ ስትኖር ከዓለም ከኃጢአት እና ከሰይጣን በላይ ትኖራለህ። እግዚአብሔርን መታዘዝ ያለብህ መጽሐፍ ቅዱስህን ያለማቋረጥ ማጥናት ያለብህ መጸለይ ያለብህ ሰዎችን መውደድና ለሌሎች ታማኝ መሆን ያለብህ ራስህን መውደድ ያለብህ ከእግዚአብሔር ፍቅር ተነስተህ ነዉ።
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የእግዚአብሔርን ፍቅር በጥልቀት መረዳት ይሁን: በልባችሁ የእግዚአብሔር ፍቅር በመንፈስ ቅዱስ በሃይል ይፍሰስ። አሜን።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ᴅɪsᴄᴏᴠᴇʀ ᴛʜᴇ 🆆🅷🆈 ᴏғ ʏᴏᴜʀ ʟɪғᴇ:
🅽🅾🆃🅸🅲🅴: ɪғ ʏᴏᴜƦ ᴡʜʏ ᴅᴏᴇsɴ'ᴛ ᴍᴀᴋᴇ ʏᴏᴜ ᴄʀʏ ᴛʜᴀᴛ ɪs ɴᴏᴛ ʏᴏᴜʀ ᴡʜʏ!
-𝚟𝚘𝚒𝚌𝚎
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
አይን👀
¯¯¯¯¯¯
አይናችሁ መንገድ ከመምረጥ እና ወደ ገደል ከመውደቅ የሚያድናችሁ ነዉ። ነገር ግን ይህንን ከመንፈሳዊ መነጸር ተመልከቱት። አይናችን ትልቅ ትርጉም ካላቸው የሰውነታችን ክፍሎች አንድ ነዉ: ውስጣዊው ሰው የምገነባበት አብዛኛው ግብዓት ወደ ውስጥ የሚገባው በአይናችን በኩል ነዉ። የምታዩትን በጥንቃቄ መምረጥ ያለባችሁ ለዚህ ነዉ። ጌታችን እንደዚህ በምለው ቃሉ የአይንን ሃይል ገልጾታል““ዐይን የሰውነት መብራት ነው፤ ስለዚህ ዐይንህ ጤናማ ከሆነ መላው ሰውነትህ በብርሃን የተሞላ ይሆናል።”
— ማቴዎስ 6፥22 (አዲሱ መ.ት)
በቀላል አገላለጽ ሰውነት ብርሃን የሚያገኘው በአይን በኩል ነዉ: የምታዩትን ምረጡ! ጤናማ እይታ ይኑራችሁ። ሕይወትን እዩ!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“....ምን ታያለህ?.....”
— ኤርምያስ 1፥11
የዚህ ቻናል አባላት ለዚህ ጥያቄ ግልጽ መልስ ሊኖራችሁ ይገባል! "ምን ታያለህ? ምን ታያለሽ?" ስለ ራሳችሁ ምን ይታያችኋል? ነገን ስታዩ ምን ይታያችኋል? እግዚአብሔር ምን ታያለህ ይላል? እግዚአብሔር ምን ታያለሽ? ይላል።እግዚአብሔር ኤርምያስን ይህንን ጥያቄ ስጠይቀው "የለውዝ በትር አያለሁ" ነበር ያለው። ከለውዝ በትር ማየት የማይቻል ቢመሰስልም እግዚአብሔር ኤርምያስን "ከባድ ነገር አይተሃል" አላለውም። "መልካም (ትክክል) አይተሃልና ቃሌን እፈጽመው ዘንድ እተጋለሁ" አለው። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን የለውዝን ያህል ልፍስፍስ ብትሆኑም እግዚአብሔር ከእናንተ ውስጥ በትር አወጣለሁ ካለ: አሜን በሉ። እግዚአብሔር ቃሉን ለመፈጸም ይተጋልና። ምን ታያለህ? ምን ታያለሽ? "ራዕይ የሌለው ሕዝብ መረን ነዉ" ስለዚህ የግድ ነገን ስታዩ የሚታያችሁ ክብር ከፍታ ስራ ሊኖራችሁ ይገባል። ይህ የነገ ስዕላችሁ ግልጽና የተብራራ መሆን አለበት: የኤርምያስን ተመልከቱ "የለውዝ ብትር አያለሁ" በጣም በአጭሩ ነዉ እና ግልጽ በሆነ መንገድ ነዉ የገለጸው። ሰፊውን ራዕያችሁን በትንሽ ቃላት ግልጽ በሆነ መልኩ ማስቀመጥ አለባችሁ። 1 ሚልዮን ድምፅ ራዕይህ/ሽ ምንድነው? ብሎ ብጠይቃችሁ: ለ 1 ሚልዮን ሰው የምትሰጡት አንድ መልስ ይኑራችሁ።
👉እግዚአብሔር ምን ታያለህ? ይልሃል ምን ታያለሽ? ይልሻል። እግዚአብሔር ከእናንተ ከቤተሰባችሁ ከሰፈራችሁ ከላችሁ አቅም በላይ የሆነ ነገር ከሳያችሁ: ቃሉን ለመፈጸም ይተጋልና አትፍሩ: አይሆንም አትበሉ። እግዚአብሔር የሚያየውን ማየት ጀምሩ: ከራሳችሁ ከቤተሰቦቻችሁ እና ከአገራችሁ ክልል ውጡና እግዚአብሔር የሚያየውን ማየት ጀምሩ። ያያችሁትን ሁሉ ትወርሳላችሁ!
"ሰው ከሚያየው በታችም በላይም መኖር አይችለም: የሚያየውን ያንኑ ይኖረዋል" -ካትሪን ኩልማን
Join
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
