en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
____________ ያልጠቀማችሁ የእግዚአብሔር ቃል ------------------------------------------- ➤የእግዚአብሔር ቃል ሁልጊዜ የሚመጣው ሊጠቅመን ልፈውሰን እና ልያድነን ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ “ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።” — መዝሙር 107፥20...ይለናል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ወደ ምድር የወረደው ያስተማረውን ሁሉ ያስተማረው ያደረገውን ሁሉ ያደረገው ሕይወት እንዲሆንልን እንድበዛልንም ነዉ። በጌታችን ሞትና ትንሳኤ ያመንን እለት ሕይወት ሆኖልናል። ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕይወት የሚበዛም ነዉ። እንዴት ካላችሁኝ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ከቃሉ(Logos + Rema) ጋር በምናደርገው የማያቋርጥ ህብረት ነዉ። "የማያቋርጥ" የሚለውን ቃል አስምሩበት። ሁላችንም የሚበዛ የሚጨምር ነገር እንወዳለን ደግሞም እንፈልጋለን። እግዚአብሔር የሰጠን ሕይወት የሚበዛ ነዉ። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን። ዛሬ መንፈስ ቅዱስ እንድናገረው የሚፈልገው ሃሳብ "ስላልጠቀማችሁ የእግዚአብሔር ቃል" ነዉ። የማይጠቅም የእግዚአብሔር ቃል አለ እንዴ? ብላችሁ ከጠየቃችሁች: መልሴ ፈጽሞ የለም የሚል ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል በራሱ ፍጹም እና በጥቅሞች የተሞላ ነዉ። ነገር ግን እናንተን ያልጠቀማችሁ ቃል እንዳለ በድፍረት መናገር እችላለሁ። ጌታን ከወቃችሁበት ቀን ጀምሮ መጽሐፍ ቅዱስ ስታነቡ ከወንድሞች ጋር ህብረት ስታደርጉ ትምህርቶች እና ስብከቶች ስተሰሙ እንደነበር አምናለሁ። በዚህ አግባብ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስብከቶች አልያም ትምህርቶች እንደሰማችሁ ግልጽ ነዉ። ነገር ግን የሰማችሁት የፀጋ ቃል ሁሉ በሕይወታችሁ የምትገልጡት እውነት ሆኗል ወይ የሚለው ጥያቄ ለእናንተው የሚተው ነዉ። ከሰማችኃቸው በመቶ ከምቆጠሩ ስብከቶች የጠቀማችሁ እና በሕይወት የገለጣችሁት ጥቅት እንደምሆን አውቃለሁ አብዛኛው ግን አልጠቀማችሁም። ለምን!? የጠቀማችሁ የእግዚአብሔር ቃል በትኩረት የሰማችሁት ፤ ጊዜ ሰጥታችሁ ያሰላሰላችሁት እና በእምነት ከራሳችሁ ጋር የዋሃዳችሁት ብቻ ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል "የእግዚአብሔር ቃል" ስለሆነ ብቻ አይጠቅማችሁም የግድ "በእምነት ከእናንተ ጋር መዋሃድ" ይኖርበታል። ይህንን በእምነት የማዋሃድ ስራ ደግም የሚሰራው እግዚአብሔር ሰይሆን እናንተው ራሳችሁ ናችሁ። ይህንን የሚታደርጉት በነጻ ፈቃዳችሁ ፍጹም መሰጠት ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስ “ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።” — ያዕቆብ 1፥22 ...ይለናል። የእግዚአብሔርን ቃል በትኩረት ካደመጣችሁት በኃላ የእውቀት ክፍላችሁ እና የሕይወታች ስርዓታችሁ እስክሆን ድረስ ደጋግማችሁ አስቡት አሰላስሉት ከዛም ከፍ በለ ደምጽ አውጁ! መጽሐፍ ቅዱስ...“ነገር ግን፦ አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤” — 2ኛ ቆሮ 4፥13 ። ይህንን በተደጋጋሚ ያለማቋረጥ አድርጉ። ➤በትኩረት የማትሰሙት የማታሰላስሉት እና በእምነት ከራሳችሁ ጋር የማታዋህዱት የእግዚአብሔር ቃል አይጠቅማችሁም። ስለዚህ አንድ ስብከት ለይ አንድ ትምህርት ለይ አንድ መዝሙር ለይ አንድ ጥቅስ ለይ ውሎ ማደር ተለማመዱ። የእግዚአብሔርን ቃል መደጋገም የስንፍና ምልክት አይደለም የአስተዋይነት እንጅ። ፍጹም ለውጥን ማሳካት የምትችሉት በዚህ ደረጃ ከመንፈስ ቅዱስ እና ከቃሉ ጋር ሕብረት ስታደርጉ ነዉ። 🔥Transfiguration🔥 ፍጹም ለውጥ🔥 #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሳቱ ፍጹም ለውጥ "Transfiguration" አሁን ምድር ለይ የሚኖርብን እውነት ሆኗል። @TheDeepThingsOfTheSpirit

Transfiguration intro: የህንን መልእከት ስሙት ለሌሎችም አሰሙት: በዚህ አመት መንፈሳዊ ለውጣችሁ አካላችሁ ለይ የሚገለጥ እውነት ይሆናል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

🌻🔥 Transfiguration 🔥🌻 ➤A complete Change of life and appearance by the renewing of MIND is our focus this year. ➤This year I must Transfigure! ➤This year my story Must Change! 🌻🔥Transfiguration will be the focus of our massage the whole year🔥🌻 “But we all, with open face beholding as in a glass the glory of the Lord, are changed into the same image from glory to glory, even as by the Spirit of the Lord.” — 2 Corinthians 3:18 (KJV) Transfiguration is more than a change! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

🌻"TRANSFIGURATION"🌻

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻አርብ 01/01/2013 የመጀመሪያው ቀን። እንደዚህ ልባርካችሁ 2013 አንድም ሰከንድ ስትባክኑ አይለፍ!!! እያንዳንዱ ሰከንድ ፤ ደቂቃ ፤ ሰዓት ፤ ቀን ፤ ሳምንት እና ወር ለእግዚአብሔር እና እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ላለው ዓላማ የሚትኖሩበት ነዉ። መልካም አድስ አመት ነዉ። 🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 -Voice

ሰላም ለእናንተ ይሁን! ወደ 2013 ልንገባ የተወሰኑ ሰዓታት ናቸው የቀሩን! እግዚአብሔር ስለ ቸርነቱ የተመሰገነ ይሁን የማይቋረጥ ምህረቱ እና ፍቅሩ ሁልጊዜም ከእኛ ከልጆቹ ጋር ነበር። ወዳጆቼ የሚቀጥሉት ዓመታት በታደሰ አእምሮ የተለወጠ ሕይወት የሚንኖርበት እና የእግዚአብሔርን ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስን መልክ በምድር ለይ የምንገልጽበት ዓመታት ናቸዉ። መንፈስ ቅዱስ የሰጠኝን መልእክት ነገ እንድትሰሙት አደርጋለሁ። መንፈስ ቅዱስ የሰጠኝ መልእክት "መለወጥ"/ Transfiguration/ ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።” — ሮሜ 12፥2

“ሰው ከእግዚአብሔር (ያህዌ) አፍ በሚወጣው በእያንዳንዱ ቃል እንጂ፣ በእንጀራ ብቻ እንደማይኖር ሊያስተምርህ አስራበህ፤ አንተም ሆንህ አባቶችህ የማታውቁትን መና መገበህ፤” — ዘዳግም 8፥3 (አዲሱ መ.ት) በአመጋገብ ስርዓት ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል(ሬማ) የግድ መካተት ይኖርበታል። እንጀራና ኬክ ብቻ አይደለም የኖረን ነገር ግን ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ እያንዳንዱ ሬማ ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና.....” — ምሳሌ 23፥7

“በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረ ይህ አሳብ በእናንተ ዘንድ ደግሞ ይሁን።” — ፊልጵስዩስ 2፥5 የእግዚአብሔርን መንፈስ በክርስቶስ ለሉ ሁሉ የሚያቀርበው የመጀመሪያው እና ትልቁ ጥር ይህ ነዉ። የአስተሳሰብ ስርዓታችሁ የሕይወት አይነታችሁን ይወስናል። አስተሳሰባችሁን እንደ ቃሉ ማድረግ ከቻላችሁ ሕይወታችሁ ይለወጣል። እንደ ክርስቶስ አስባለሁ እናገራለሁ ደግሞም አደርጋለሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ወዳጆች ጊዜ በራሱ የሚለውጣው አንድም ነገር የለም።20_13 ነገሮችን በነጻ ፈቃዳችሁ እና በእግዚአብሔር ፀጋ ለመለወጥ ወስኑ። ማናችንም 2013ን እንደ 2012 አይነት መንገድ መድገም እንፈልግም ስለዚህ የሚጠይቀንን ዋጋ ከፍለን ነገሮችን እንለውጥ። አእምሮን በእግዚአብሔር ቃል ከማደስ ጀምሮ ሁሉንም ነገር መለወጥ ይቻላል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እንቅልፍ ከመተኛታችሁ በፊት አእምሮችሁ የሚያስበው እና አንደበታችሁ የሚያወራው የመጨራሻው ነገር ስለኢየሱስ ይሁን! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit

photo content

“በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤” — ኤፌሶን 6፥18

የ 2012 ማገባደጃ ለይ ነን በዚህ አመት ስለተገኙ ድሎች እግዚአብሔር ይመስገን። ከፊታችን የቀሩ የተወሰኑ ቀናት ስላለፈው ጊዜ እግዚአብሔርን የምናመሰግንባቸው እና ከፊታችን ያሉትን ብዙ ቀናት የምንዋጅባቸው ይሁኑ። በእነዚህ ቀናት ለምመጣው ጊዜ ግልጽ የሆነ ራዕይ ከእግዚአብሔር እንድትቀበሉ ይሁን። እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ነዉ።

“እናቱም ለአገልጋዮቹ፦ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።” — ዮሐንስ 2፥5 ኢየሱስ ክርስቶስ የሚላችሁን ሁሉ ለማድረግ የምትታዘዙ ከሆነ ሕይወታችሁ እንደ #ውሃ ቀለም የሌለው ሽታ የሌለው እና ጣእም የሌለው እንኳ ብሆን እንደ #ወይን ቀለም ሽታና ጣእም ያለው ሆኖ ይለወጣል። ጥያቄው የሚላችሁን ሁሉ ታደርጋላችሁ እንዴ የሚል ነዉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

God can change your life. God can transform a colorless life into something beautiful, as he changed the water into wine! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit