en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ድል_በድል (ድ)ል የተደረገ:እድለኛ (ል)ቤ ነበረ:እምቢተኛ (በ)ፍቅር የዳነ:ህመምተኛ (ድ)ግስ ነጋሪ:ሆነ ተረኛ (ል)ዑል የማረከው:ምርኮኛ!! . . . ራእይ 19 (Revelation) 9፤ እርሱም፡— ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው፡ ብለህ ጻፍ፡ አለኝ። ደግሞም፡— ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ነው፡ አለኝ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ወላጅህን ውደደው! አፍቅረው!! ----------------------------------------- ወላጁን የሚጠላ ልጅ እንብዛም ባይኖርም ነገር ግን ለወላጁ ደንታ የሌለው ልጅ ብዙ ነዉ። ይህ ምንአልባትም ያለማወቅ ወይም ደግሞ የትዕቢት ውጤት ይሆናል። መጽሐፍ ቅዱስ “አባትህንና እናትህን አክብር፤ እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም።” — ዘጸአት 20፥12 ይላል። ወላጅን ማክበር ዘመንን ያበዛል። ፍቅር የእውነት በማክበር ይገለጻል! ለወላጁ ክብር የሌለው ልጅ ፍቅር የለውም ማለት ነዉ! አባቴን እወደዋለሁ ነገር ግን አላከብረውም ማለት አይቻልም! የእግዚአብሔር ቃል በእምነት የተቆረጥንበት ድንጋይ የተቆፈርንበት ጉድጓድ ነዉ: በክርስቶስ ስናምን ከእግዚአብሔር ቃል ተወልደናል! #የእግዚአብሔር_ቃል_ወላጃችን_ነዉ!! መጽሐፍ ቅዱስ “ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 1፥23 ይላል! በእግዚአብሔር ቃል ተወልደናል! ተወዳጆች ሆይ በዚህ በአድሱ ሕይወታችሁ መብዛት ከፈለጋችሁ ወላጃችሁን አክብሩ ወደዱ! አቋራጭ መንገድ የለም ከምንጫችን ጋር ቀጣይና የማይቋረጥ ሕብረት ሊኖረን ይገባል! ሩቅ መጓዝ የሚወድ ሁሉ ይህንን ሰምቶ ወላጁን ያከብራል!! ተወዳጆች ሆይ እንደዚህ ብዬ ልባርካችሁ #ከእግዚአብሔር_ቃል_ጋር_ፍቅር_ይያዛችሁ!!!!!! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዘካርያስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እርሱም ታላቁን ካህን ኢያሱን በእግዚአብሔር መልአክ ፊት ቆሞ አሳየኝ፥ ሰይጣንም ይከስሰው ዘንድ በስተ ቀኙ ቆሞ ነበር። ² እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ፤ ኢየሩሳሌምን የመረጠ እግዚአብሔር ይገሥጽህ፤ በውኑ ይህ ከእሳት የተነጠቀ ትንታግ አይደለምን? አለው። ³ ኢያሱም እድፋም ልብስ ለብሶ በመልአኩ ፊት ቆሞ ነበር። እርሱም መልሶ በፊቱ የቆሙትን፦ እድፋሙን ልብስ ከእርሱ ላይ አውልቁ አላቸው። እርሱንም፦ እነሆ፥ አበሳህን ከአንተ አርቄአለሁ፥ ጥሩ ልብስም አለብስሃለሁ አለው። ⁵ ደግሞ፦ ንጹሕ ጥምጥም በራሱ ላይ አድርጉ አለ። እነርሱም በራሱ ላይ ንጹሕ ጥምጥም አደረጉ፥ ልብስንም አለበሱት፤ የእግዚአብሔርም መልአክ በአጠገቡ ቆሞ ነበር። @TheDeepThingsOfTheSpirit

የ አሜርካ ምርጫ የትራምፕ እና የባይደን ትግል የሚመስላቸው ወይም የ Republican እና የ Democrats ትግል የሚመስላቸው ሰዎች ብዙ ናቸው! ነገር ግን ነገሩ ከዛ የራቀ ነዉ!

እግዚአብሔር #ትራምፕ ስል ሰው ደግሞ #ባይደን ይላል! እግዚአብሔር የሚለው ለዓለም የተሻለ ነዉ!!!!! @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉ይህንን መልእክት ያስቀመጥኩት ትናንት እኩለ ቀን ለይ ነበር! ስለ #ስለ_ሰሜን_ኢትዮጵያ_ጸልዩ ይላል! ስንት ሰው እየጸለየ ነዉ!? መንፈስ ቅዱስ በሪዕይ ያሳየኝ ነገር አስፈሪ ስለነበረ ነዉ: አብራችሁኝ እንድትጸልዩ ጥር ያቀረብኩት: አሁን በሰሜን ኢትዮጵያ እየሆነ ያለውን ነገር የምታውቁት ነዉ: አሁንም እንጸልይ እግዚአብሔር ነገሩን እንድቆጣጠረው! መንፈስ ቅዱስ የሚለው ይህንን ነዉ!

በምትሰሙት በምታዩት እና በምታነቡት ሁሉ ነፍሳችሁን እየመገባችሁ ነዉ! ከእግዚአብሔር እውነት እና ሃይል ዝቅ ያለ ነገር ነፍሳችሁን በመመገብ የእናንተ ያልሆነን ተራ የሕይወት አይነት አትኑሩ!!!! ለራሳችሁ ስትሉ ሕብረታችሁን አስተካክሉ: ከማን ጋር ሕብረት ላድርግ ብላችሁ ከጠየቃችሁኝ ይህንን በጥልቀት አሰላስሉ👉"እናንተ ደግሞ ከእኛ ጋር ኅብረት እንዲኖራችሁ ያየነውንና የሰማነውን ለእናንተ ደግሞ እናወራላችኋለን። ኅብረታችንም ከአባት ጋር ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው።” — 1ኛ ዮሐንስ 1፥3 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የምጸልየው አገልጋይ ስለሆንኩ አይደለም! #የምጸልየው_ክርስቲያን_ስለሆንኩ_ነዉ!!! #የጸሎት_ሰዎች_ነን! #የተለየን_ሰዎች_ነን!! #ጸሎት_የሕይወት_ስርዓታችን_ነዉ!! #ተራራ_ደግሞ_ምርጡ_ቦታ_ነዉ!
የምጸልየው አገልጋይ ስለሆንኩ አይደለም! #የምጸልየው_ክርስቲያን_ስለሆንኩ_ነዉ!!! #የጸሎት_ሰዎች_ነን! #የተለየን_ሰዎች_ነን!! #ጸሎት_የሕይወት_ስርዓታችን_ነዉ!! #ተራራ_ደግሞ_ምርጡ_ቦታ_ነዉ!!😍 #We_are_people_of_prayer!!! 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች ፍትህ የእውነት የምናገኝበት መንግስት የእግዚአብሔር መንግስት ብቻ ነዉ! ኢትዮጵያ ለይ የእግዚአብሔር መንግስት በሃይል እንድትገዛ ጸልዩ: ለሰሜን ኢትዮጵያ ደግሞ አጥብቃችሁ ጸልዩ!! #Voice! @TheDeepThingsOfTheSpirit

“በገለዓድ የሚቀባ መድኀኒት የለምን? ወይስ በዚያ ሐኪም አልነበረምን? ለሕዝቤ ቍስል፣ ለምን ፈውስ አልተገኘም?” — ኤርምያስ 8፥22 (አዲሱ መ.ት) 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭 @Th
“በገለዓድ የሚቀባ መድኀኒት የለምን? ወይስ በዚያ ሐኪም አልነበረምን? ለሕዝቤ ቍስል፣ ለምን ፈውስ አልተገኘም?” — ኤርምያስ 8፥22 (አዲሱ መ.ት) 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ያለሁበት Network በጸሎት ነዉ የሚሰራው😁 ስለትውልድም ስለ network ጸልዬ አልችልም😁....መልካም ቆይታ....

ሰላም ይብዛላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች አሁን የምገኘው ከከተማ ወጪ የጸሎት ተራራ ለይ ነዉ: ለአንድ ሳምንት ያህል እዚሁ ተራራ ለይ በጸሎት እቆያለሁ: ስለዚህ ለአንድ ሳምንት ያህል በዚህ ቻናል መልእክት አልለጥፍም: ከዛ በኃላ በሃይል እና በብዙ መረዳት እንደምንገናኝ አምናለሁ! እንድትጸልዩልንም ጥያቄዬ ነዉ። ለእናንተም እንደምንጸልይ ቃሌ ነዉ! ተባረኩ!!!

⛈⛈የኋለኛው ዝናብ🌧🌧 ------------------------------------- “በኋለኛው ዝናብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዝናቡን ለምኑ፤ እግዚአብሔር መብረቅ ያደርጋል፤ እርሱም የበልግ ዝናብን ለእያንዳንዱም በሜዳ ውስጥ ሣርን ይሰጣል።” — ዘካርያስ 10፥1 ይህ ዝናብ የሚያስፈልገን ትክክለኛው ጊዜ ለይ ነን! ምክንያቱም ልያጥበን ፣ልያነጻን ፣ ልያረሰርሰን እና ፍሬም እንድንሰጥ ሊያደርገን የሚቻለው እሱ ብቻ ነዉ!!! እንግዲህ ይህንን ዝናብ የፈለገ ሁሉ መጽሐፍ እንደሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ይለምን! የሚለምን ይሰጠዋል! ተወዳጆች ሆይ ከመንፈስ ቅዱስ ዝናብ ውጭ ምንም ሌላ ነገር ፍሬ እንድናፈራ ልያደርገን እንደማይችል ተረድቻለሁ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በአማኝ ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔርን አብ እና የእግዚአብሔርን ወልድ ሕልውና እሁን የሚያደርገው መንፈስ ቅዱስ ነዉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እግዚአብሔር ግን ይህን በመንፈሱ አማካይነት ለእኛ ገልጦልናል። መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥10 (አዲሱ መ.ት)

"Bend the Church and bow the World" 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭

የዌልስ ሪቫይቫል እውነተኛ የሪቫይቫል ትርጉም!! -------------------------------------------------------------- ብዙ ጊዜ ሰዎች ስለ ሪቫይቫል ስያወሩ ሰምታችሁ ይሆናል። ፈጽሞ ሪቫይቫል ለመባል የማይበቁ ነገሮችን እንኳ ሪቫይቫል እያሉ ስጠሩ ይስተዋላል! ይህንን የምለው ማንንም ለመቃወም ወይም ለማሳፈር አይደለም: እውነትን በማወቅ እውነተኛውን ሪቫይቫል ከእግዚአብሔር ዘንድ ሁላችንም እንድንለምን ነዉ። 👉ሪቫይቫል:- የቃሉ ትርጉም : #ወደ_ሕይወት_መመለስ ማላት ነው። ኢዮብ “የእግዚአብሔር መንፈስ ፈጥሮኛል፤ ሁሉን የሚችለውም አምላክ እስትንፋስ ሕይወት ሰጥቶኛል።” — ኢዮብ 33፥4 (አዲሱ መ.ት) ይህንን ማድረግ የሚቻለው ደግሞ የእግዚአብሔር እስትንፋስ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነዉ!!!! ወደ ሃሳቤ ልግባ በ 1906 በዌልስ ምድር የሆነው ሪቫይቫል በዘመናዊው የሪቫይቫል ተርኪ ውስጥ እውነተኛ ሪቫይቫልን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነዉ ብዬ አምናለሁ! በኢቫን ሮበርት መሪነት የተቀሰቀሰው ይህ ሪቫይቫል ጥልቅ በሆነ እና በማያቋርጥ የመሰጠት ጸሎት የጀመረ ነበር: መንፈስ ቅዱስ መንቀሳቀስ ስጀምር #ሁሉንም_ሰው_በሁሉም_ቦታ_ነካ!!!! "ሪቫይቫል ይህ ነዉ!!!!" በዌልስ ምድር ያልተነካ አልነበረም! በጥቅት ወራት ነበር የዌልስን ምድር ሙሉበሙሉ በወንጌል ሃይል የገዙት! በዚህ ወቅት ነበር አንድ በጣም የሚያስደንቅ ነገር በዌልስ ምድር የሆነው: የዌልስ ሰዎች የድንጋይ ከሰል የሚያወጡ ነበር: ይህንን ከሰል ለማጓጓዝ ይጠቀሟቸው የነበሩ አህዮች ከሪቫይቫሉ በፊት መታዘዝ የለመዱት በነውረኛ ስድብና ድብደባ ነበር: ነገር ግን ሪቫይቫሉ ምድርቱን ካጥለቀለቃት በኃላ እነዚህ ከሰል አውጪዎች አህዮችን እንኳ ለመሳደብና ለመደብደብ የቅድስና መንፈስ ይከለክላቸው ስለነበር: #አህዮች_እንኳ_ያረፉበት_ዘመን_ነበር! ይህ ነው ሪቫይቫል!!! የግዴታ በአገር ደረጃ አይሆንም ይሆናል ነገር ግን በግል ሕይወታችሁ ይህንን አይነት የእግዚአብሔር ፍርሃት ማየት ከቻላችሁ ሪቫይቫል እየሆነ ነዉ ማለት ነዉ!!! ለቀናት ለወራት የሞቱ ሰዎች እንኳ ቢነሱ ከፍተኛ እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ ከሌለ እውነተኛ ሪቫይቫል ነዉ ማለት አይቻልም ይሆናል። እግዚአብሔር በሃገር ደረጃ ሪቫይቪ እንዲያደርገን ጸሎቴ ነዉ። በመጨረሻም የዌልስ ሪቫይቫል አገልጋይ የነበረው ወንጌላዊው ኢቫን ሮበርት የተናገረውን እና እኛም መከተል አለብን ብዬ የማምነውን አንድ እውነት ልናገር እና ልጨርስ: ኢቫን ሮበርት ስለመጣው ተጽእኖ ስጠየቅ "Bend The Church and bow the world" ብሎ ነበር የመለሰው ይህ ማለት "ቤተክርስቲያን ስታጎነብስ ዓለም ትንበረከካለች" ማለት ነዉ። ተወዳጆች ሆይ እኛ በእግዚአብሔር ፊት መንበርከክ ከቻልን ዓለም በእግዚአብሔር ፊት በደረቷ ትወድቃለች!!!! ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ፊት ደረቷን ነፍታ በትዕቢት ከሄደች ዓለም እንዴት ትሆን!? መልሱን ለእናንተው! "Bend The Church and Bow The World" -Evan Roberts. 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit