TheDeepThingsOfGod
Open in Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Show more1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 810
ትላንትና በሆሳዕና ጎዳናዎች ላይ ከወንድሜ ካቦድ እና ሌሎች ወንድሞች ጋር ባደረግነው ወንጌል ማጋራት ብዙዎች ጌታችንን ተቀብለዋል እጅግ ትልቅ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በንስሐ ተመልሰዋል የተወሰኑ ሰዎች ደግሞ ከአጋንንት እስራት ነጻ ወጥተዋል። ክብር ሁሉ ድል በመንሳት ለሚያዞረን ለእግዚአብሔር ይሁን!
1 810
ክፍል 2
~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት"
~ልጅ ዳን።
ክፍል 3ን ለማግኘት
👇👇👇
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ክፍል 1
~"የእግዚአብሔርን ክብር ማየት"
የእግዚአብሔር ክብር ምንድነው?
~ልጅ ዳን።
ክፍል 2ን ለማግኘት
👇👇👇
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
በግል የማሰለጥናቸው ጥቅት መንፈሳዊ ልጆች አሉኝ: በመንፈስ ልጆቼ ከሆኑት አንዱ "አስተማሪ ነቢይ ነዉ" ዳንኤል/ዳን/ ይባላል፥ እጅግ በጣም ትልቅ ተማሪ እና አስተማሪ ነዉ። "የእግዚአብሔርን ክብር ማየት" በሚል ርዕሰ በሦስት ክፍል በእርሱ የተዘጋጀውን አስደናቂ እና ሕይወት ለዋጭ ትምህርት ነገ እለቃለሁ፥ ለመቀየር ተዘጋጁ።
እመኑኝ የሚመጣው ዘመን የእግዚአብሔርን ክብር ተገልጦ የምናይበት ነዉ።
1 810
ዋው የዛሬው አገልግሎት እሳት 🔥 ብቻ ነበር! ብዙዎች ከአጋንንት እስራት ተፈተዋል፣ ብዙዎች በትንቢት ተጎበኙ😭 ሁሉም ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ ረሰረሱ🔥!
ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!
1 810
በጌታ ያልሆነ ሰው:-
ከአንተ ወዳጅነት በላይ የኢየሱስ አዳኝነት ያስፈልገዋል።
ከጓደኝነትህ በላይ ሰባኪነትህ ያስፈልገዋል።
ከካፌ ግብዣህ በላይ አንተ ጋር ያለው ወንጌል ያስፈልገዋል።
ከቀልድህ በላይ በልብህ ያለው የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ያስፈልገዋል።
የኢየሱስ አዳኝነት እንጂ የአንተ ወዳጅነት ከዘላለም ሞት አያድነውም፥ በልብህ ያለው ወንጌል እንጂ የካፌ ግብዣህ አይለውጠውም፥ የተቀበልከው የእግዚአብሔር እውነት እንጂ ጓደኝነትህ ከኃጢአት ባሪነት ነጻ አያወጣውም።
ወንጌልን በግልጥ ስበክ!
1 810
I did it!😂
ዛሬ በሕይወቴ ለሁለተኛ ጊዜ ባደረኩት የምግብ ማብሰል የሚደንቅ ሽሮ መስራት ችያለሁ! ብትቀምሱት ቪክቶር ከላበሰለ አልበላም ነው የምትሉት😂😂... ምን ለማለት ነው ወንዶች ማብሰል ልማዱ እህቶች በሚቀጥለው ዘመን በእሳት ተቀብተው እንደ ወንድሞች ሁሉ በሃይል ያገለግላሉ ለማለት ነዉ፥ ስለዚህ ከአሁኑ😂🔥
ምንጭ -ትንቢተ ኢዮኤል 2:29።
እህቶች ደግሞ ቪክቶር እንደዚህ አለ ብላችሁ አናበስልም፧ አይቻልም! 😂
Thank you Apostle Kabod!
1 810
የእግዚአብሔር ልጆች ዋጋችሁ ከምታስቡት በላይ ውድ ነዉ፥ ውስጣችሁ ያለው መዝገብ እጅግ የከበረ ነዉ።
በቀን ውስጥ ሰፊውን ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል በሚባለው መስታወት ፊት በመቆም ፎቶግራፎቻችሁ፣ ግድግዳችሁ ላይ የተንጠለጠለው መስታወት፣ መልካም ጓደኞቻችሁ ወይም ፌስቡክ ወይም ሌሎች መጽሐፍት ያልነገሯችሁን መልካችሁን በራሳችሁ የልቦና አይኖች ተመልከቱ፥ ፈጽሞ ተለወጡ፥ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ጊዜ ማሳለፍ በዓለም እንኳ እንደ ከዋክብት እንድትታዩ ያደርጋችኋል።
1 810
አፍጋኒስታን ላይ ታሊባን 229 ሚሺነሪዎች በመግደል ወንጌልን የሚያስቆም መስሎት ነዉ። የሰማዕታት ደም የቤተክርስቲያን ዘር እንደሆነ አልገባውም፥ በሚቀጥለው ዘመን የወንጌል እሳት ከሚነድባቸው አገራት አንዷ አፍጋኒስታን ናት።
1 810
ሰላም እና ፀጋ ይብዛላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች። የፊታችን ማክሰኞ ሆሳዕና ያላችሁ በተጠቀሰው አድራሻ አይቀርም፥ ሆሳዕና ላሉ አጋሩ የታመሙ እና በአጋንንት እስራት ውስጥ ያሉትን ይዛችሁ እንድትመጡ። መንፈስ ቅዱስ ድንቅ ነገር ያደርጋል።
1 810
Saron: (Testimony Via-inbox)
open talk ❤️...kal yelegnim betam nw touched yehonkut ...mskrnet ayche nw voicun krb seat yesemahut..mndn nw yihen yahl yetekabedew bye nbr gn noo😁
መልዕክቱን ከመስማቴ ከደቂቃዎች በፊት ማለዳ ላይ እቤት ለእንግድነት ለመጡት አማኝ ላልሆኑ ለአክስቶቼ ልጆች ቃል ሳካፍል ነበር ያካፈልኩትም ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ነበር።በጣም ተገርመው ጌታ ጆሮዎቻቸውን ሰጥቶኝ ሰሙኝ።ልምዱ የለኝም አና አብሬያቸው በፀሎት ጌታን ተቀብዬ ንስሀ ገባሁ 😁 ግን ገና አልወሰኑም ባይገርምህ አንድኛዋ ትንሽ በባህሪ ከመስመር ወጣ ስላለች አባቴ ለእኛ ፈርቶ ነበር። እኔ ግን How?? ነው ያልኩት እኛ ነን እንጂ እነርሱ እንዴት influence ያደርጉናል🤷♀... ብቻ ሁሉም ከvoice በኋላ ቢሆን ይበልጥ አሪፍ ይሆን ነበር🙈...በህይወቴ ላይ ተፅዕኖ እንደሚያመጣ አልጠራጠርም።ትልቅ መረዳትን አግኝቻለሁ። ከሰሞኑ አንድ ነገር ገብቶኛል እኛ በምድር ላይ ያለነው #ውለታው #በዛ እያልን እየዘመርን እንድንሞት አይደለም ለውለታው እና ለጥልቅ ፍቅሩ ምላሽ ባይሆን እንኳ በተሰጠን ፀጋ እርሱን መውደድ እንድንችል ነው።ኢየሱስ ወዶናል እርሱ አንዴ ስራውን ጨርሷል ። full package ነው የሰጠን ለእርሱ ያለው የእኛ ነው እርሱ ራሱ የእኛ ነው እኛም የእርሱ ።እኛ ግን በራሳችን ኢየሱስን መውደድ አንችልም ። አይገርምም ተወዶ መውደድ ራሱ ፀጋን ይሻል ።ቀሪ ዘመናችን ፍቅሩን ለገለፀልን እንደ ፀጋው ብዛት ፍቅራችንን የምንገልፅበት ይሁንልን።🙏
1 810
Saron: (Testimony Via-inbox)
open talk ❤️...kal yelegnim betam nw touched yehonkut ...mskrnet ayche nw voicun krb seat yesemahut..mndn nw yihen yahl yetekabedew bye nbr gn noo😁
መልዕክቱን ከመስማቴ ከደቂቃዎች በፊት ማለዳ ላይ እቤት ለእንግድነት ለመጡት አማኝ ላልሆኑ ለአክስቶቼ ልጆች ቃል ሳካፍል ነበር ያካፈልኩትም ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ነበር።በጣም ተገርመው ጌታ ጆሮዎቻቸውን ሰጥቶኝ ሰሙኝ።ልምዱ የለኝም አና አብሬያቸው በፀሎት ጌታን ተቀብዬ ንስሀ ገባሁ 😁 ግን ገና አልወሰኑም ባይገርምህ አንድኛዋ ትንሽ በባህሪ ከመስመር ወጣ ስላለች አባቴ ለእኛ ፈርቶ ነበር። እኔ ግን How?? ነው ያልኩት እኛ ነን እንጂ እነርሱ እንዴት influence ያደርጉናል🤷♀... ብቻ ሁሉም ከvoice በኋላ ቢሆን ይበልጥ አሪፍ ይሆን ነበር🙈...በህይወቴ ላይ ተፅዕኖ እንደሚያመጣ አልጠራጠርም።ትልቅ መረዳትን አግኝቻለሁ። ከሰሞኑ አንድ ነገር ገብቶኛል እኛ በምድር ላይ ያለነው #ውለታው #በዛ እያልን እየዘመርን እንድንሞት አይደለም ለውለታው እና ለጥልቅ ፍቅሩ ምላሽ ባይሆን እንኳ በተሰጠን ፀጋ እርሱን መውደድ እንድንችል ነው።ኢየሱስ ወዶናል እርሱ አንዴ ስራውን ጨርሷል ። full package ነው የሰጠን ለእርሱ ያለው የእኛ ነው እርሱ ራሱ የእኛ ነው እኛም የእርሱ ።እኛ ግን በራሳችን ኢየሱስን መውደድ አንችልም ። አይገርምም ተወዶ መውደድ ራሱ ፀጋን ይሻል ።ቀሪ ዘመናችን ፍቅሩን ለገለፀልን እንደ ፀጋው ብዛት ፍቅራችንን የምንገልፅበት ይሁንልን።🙏
1 810
ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማለት ነዉ። ክርስቶስን መስበክ አቆምኩ ማለት ከቅባት ጋር ተለያየሁ ማለት ነዉ።
-ሐዋሪያው ተዓምራት ታረቀኝ
1 810
መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ለእናንተ ያለውን የከበረ ዓላማ በግልጽ እንዲያሳያችሁ እጸልያለሁ። የእግዚአብሔር ልጆች ሰላማችሁ፣ ደስታችሁ፣ ድላችሁ፣ ከፊታችሁ ሁሉ ያለው በዚያ ነዉ።
1 810
የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ እንዴት ማወቅ እችላለሁ?
ከላይ ያለው ጥያቄ በግልጽ እንዲመለስላችሁ ሌላ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፧ የእናንተን ፈቃድ እና እቅድ ማወቅ የሚችለው ማነው? መጽሐፍ ቅዱስ በ - 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥11 “በእርሱ ውስጥ ካለው ከሰው መንፈስ በቀር ለሰው ያለውን የሚያውቅ ሰው ማን ነው?” ይላል፥ የእናንተን ፈቃድ እና እቅድ ከራሳችሁ ሌላ የሚያውቅ የለም። ፈቃዳችሁን እና እቅዳችሁን ማወቅ የሚፈልግ ሰው የግዴታ እናንተን እራሳችሁን መጠየቅ አለበት ወይም ከመንፈሳችሁ መረጃ መቀበል አለበት፥ ሁለተኛው እቅዳችሁን እና ፈቃዳችሁን ለማወቅ የሚችልበት መንገድ 'እቅዳችሁን እና ፈቃዳችሁን በጽሑፍ ያስቀመጣችሁበት መጽሐፍ ከለ እርሱን መጽሐፍ አግኝቶ በጥንቃቄ መፈተሽ ነዉ። የመጨረሻው አንድ ሰው የእናንተን ፈቃድ እና እቅድ ለማወቅ የሚችልበት መንገድ እናንተ አስቀድማችሁ ፈቃዳችሁን እና እቅዳችሁን የገለጸችሁለትን ሰው አግኝቶ ከእርሱ በመስማት ማወቅ ነዉ። ሌላ ሰው የእናንተን እቅድና ፈቃድ ማወቅ የሚችለው በእነዚህ መንገዶች ነዉ።
በተመሳሳይ መልኩ “... ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር ለእግዚአብሔር ያለውን ማንም አያውቅም።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥11
የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ የሚያውቀው የእግዚአብሔር መንፈስ ነዉ፥ ስለዚህ የመጀመሪያው የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ የምናውቅበት መንገድ መንፈስ ቅዱስን በጸሎት መጠየቅ ነዉ። መልካሙ ነገር መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ በመረጣቸው ሰዎች በነቢያቱ እና በሐዋርያቱ በኩል በጽሑፍ ገልጦልናል፥ ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን። እኛ ማወቅ የሚገባን የእግዚአብሔር ፈቃድ እና እቅድ በሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጽፏል፥ ይሄ እጅግ በሃሴት የሚሞላ ነዉ፥ ሃሌሉያ። የእኛ ድርሻ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በጸሎት ሕብረት እያደረግን ይህንን መጽሐፍ ቅዱስ በጥንቃቄ መመርመር ነዉ፥ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ ሁሉ እናገኛለን። የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ ማወቅ ደግሞ ከመለኮት ጋር አብሮ-ሰራተኛ ወደመሆን መንፈሳዊ ከፍታ ያደርሳል፥ ታዲያ በዘመናችሁ ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ-ሰራተኛ መሆን የምትፈልጉ የእግዚአብሔር ልጆች ምን ትጠብቃላችሁ? መጽሐፍ ቅዱሳችሁን ተመልከቱ በጥንቃቄ መርምሩ፥ የእግዚአብሔርን ቃል አግኙ በሚቀጥለው ዘመን እግዚአብሔር የሚሰራው ከእናንተ ጋር ነዉ።
#GetInToTheWord
〽️ 🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉን🔺 〽️ @TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ከመለኮት ጋር አብሮ-ሰረተኛ ወደመሆን መንፈሳዊ ከፍታ የሚያወጣው የመጀመሪያው ቁልፍ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እና እቅድ ማወቅ ነው።
-Victor
