TheDeepThingsOfGod
Open in Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Show more1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 810
#ፈቃዳችሁን_ለእግዚአብሔር_ፈቃድ_አስገዙ
---------------------------------------------------------
ምድር የሰው ልጆች ግዛት ናት: ይህንን የውሰነው እግዚአብሔር ራሱ በሉአላዊነቱ ነዉ: የትኛውም መንፈስ ወይም ሰማያዊ አካል በዚህ ምድር ለይ ለመሄድ እና ፈቃዱን ለመፈጸም የግዛቱ ባለአደራ የሆነውን የሰውን ልጅ እሺታ ማግኘት የግድ ይለዋል። ሉዓላዊ የሆነው እግዚአብሔር እንኳ ፈቃዱን ምድር ለይ ለመከወን የሰዎችን ፈቃድ ይፈልጋል: ለዚህም ነዉ: መምህራችን ኢየሱስ “...ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤”
— ማቴዎስ 6፥10...ብላችሁ ጸልዩ ብሎ ያስተማረን። የእግዚአብሔር ፈቃድ ምድር ለይ በሰማይ እንዳለው የሚሆነው የሰው ልጆች እሽታቸውን የሚሰጡ ከሆነ ነዉ። ይህ ማለት ግን እግዚአብሔር በነጻ ፈቃዱ አይሰራም ማለት አይደለም። የእግዚአብሔር ፍጹም ፈቃዱ( 𝙩𝙝𝙚 𝙥𝙚𝙧𝙛𝙚𝙘𝙩 𝙬𝙞𝙡𝙡 𝙤𝙛 𝙜𝙤𝙙) በዚህ ምድር ለይ መፈጸም ካለበት ሰው መሳተፍ ይኖርበታል። ለዚህም ነዉ እግዚአብሔር ቃሉን( 𝙡𝙤𝙜𝙤𝙨) ሰው ያደረገው: በሱ መታዘዝ ብዙዎች እንዲድኑ እና ለእምነት በማይታዘዙት ለይ ደግሞ በመጨረሻ ለመፍረድ ነዉ። ጌታችን ይህንን እንደዚህ በማለት ገልጾታል “የሰው ልጅም ስለ ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው።”
— ዮሐንስ 5፥27
በአጠቃላይ በዚህ ምድር ለይ የሰው ልጅ ገዥ ነዉ: መጽሐፍ “የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።”
— መዝሙር 115፥16...ይላልና!
ተወዳጆች ሆይ በዚህ ምድር ለይ እስካላችሁ ድርስ እግዚአብሔር ስለፈቀደ ብቻ በሕይወታችሁ የሚሆን ነገር የለም: የእናንተ ፈቃድ ለእግዚአብሔር ፈቃድ መገዛት ይኖርበታል! የእናንተ ፈቃድ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር መስማማት መቻል አለበት። እግዚአብሔር ከእናንተ ፈቃድ ውጭ አንገታችሁን ጠምዝዞ የሚያስኬዳችሁ ጨቋኝ አምላክ አይደለም። በምትኩ ሁልጊዜ መልካም የሆነውን እና ሕይወት የምታተርፉበትን ፈቃዱን በመግለጥ: በዚህ ተመላለሱ ይላል: ነገር ግን በሱ እንድትመላለሱ አያስገድድም! እምቢ በሚል እብሪተኛ ልብ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ፈቀቅ በትሉ እና በፈቃዳችሁ ብትሄዱ ውጤቱን የመቀበል ሃላፊነት አለባችሁ: ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ የሚደረግ የትኛውም ነገር ደግሞ ውጤቱ ሞት እንደሆነ ከመጀመሪያው የተገለጠ ነዉ። እኛ ግን የምንታዘዝ እና ተስፋውንም የምንጨብጥ ልጆች እንጂ በለመታዘዝ ጠንቅ ለጥፋት የተወሰንን አይደለንም!*እግዚአብሔር አልተናገረኝም እንዳትሉ! ተባርካችኋል።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#በለውጥ_እመኑ
የሌለህን መስጠት አትችልም: ዓለምን መለወጥ የሚችሉ ሰዎች የተለወጡ ሰዎች ብቻ ናቸው። የመንፈስ ቅዱስ ሃይልና የእግዚአብሔር ቃል እውነት ፍጹም ለውጥን መለማመድ እንድንችል ከእግዚአብሔር ተሰጥተውናል!
Join us
👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Listen to this song every single day!!!
#KeepOn Telling to yourself and your environment that you #Overcame!! and you live because HE LIVES!😁
1 810
ADA I Overcame!
#SpeakVictory!!
#HeWonTheVictory!
#that's_how_we_live_our_life!😊
💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#መንፈሳዊ_ድህነት
ይህ: አገላለጽ: መንፈሳዊ እጦትን ወይም አለመለወጥን የሚገልጽ አይደለም: ነገር ግን ሁልጊዜ #ፈላጊ_መሆንን #የተራበ_መሆንን #ትሁት_መሆንን የሚገልጽ ነዉ።
በደረሳችሁበት መንፈሳዊ መድረክ ለይ አለመርካት እና የበለጠ መንፈሳዊ እውነትን ለመለማመድ መፈለግን የሚያሳይ አገላለጽ ነዉ! ምንም ያህል መንፈሳዊ ልምምድ ለይ ብትሆኑም ሌላ የበለጠ እንዳለ አትርሱ! በዚህ ሁሉ ግን ትኩረታችሁ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መፈጸም እና ክርስቶስን ማክበር ይሁን!
“መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።”
— ማቴዎስ 5:16
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ማቴዎስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።
…
¹³ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም።
¹⁴ እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።
¹⁵ መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል።
¹⁶ መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።
በዚህ ክፍል ለይ አሰላስሉ...
1 810
#ክርስቲያን_ደካማ_እና_ተጠቂ_አይደለም!!!
በአድስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል እንድናደርግ ታዘናል: ለማድረግ ደግሞ ሃይሉ አለን💪!
👉በኢየሱስ ስም ስናምን የተዳረግነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ መመላለስ የምችል አድስ ፍጥረት ነዉ: እንጅ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማድረግ የማይችል የስጋው የሰይጣን እና የዓለም ተጠቅ የሆነ ደካማ ፍጥረት አይደለም!
“የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤”
— ቆላስይስ 3:10
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ሃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ #ሁሉን #እችላለሁ! የእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነን ነገር ሁሉ ማድረግ እችላለሁ!
#መቀደስ_እችላለሁ! #ደስተኛ_መሆን_እችላለሁ!
#ማሸነፍ_እችላለሁ! #ከችግሮች_ሁሉ_በላይ_መሆን_እችላለሁ!
#መከናወን_እችላለሁ!
#ሕልሜን_ማልበስ_እችላለሁ!
#ወንጌልን_መስበክ_እችላለሁ!
#በጤንነት_መኖር_እችላለሁ!
#ስጋዬን_መግዛት_እችላለሁ!
#በወጀብ_ውስጥ_ያለመናወጥ_መቆም_እችላለሁ!
#በአደጋ_ፊት_በንቀት_መሳቅ_እችላለሁ!
#አሸናፊ_ነኝ!!!!!!!!!!!!!😁😁😍😍😊😊
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
IN THE FACE OF THE STORM STAY CALM!😊
#Remember : you are #Victorious! Because you have the seed of God in you!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤”
— ዕብራውያን 4:12
#የእግዚአብሔር_ቃል_በራሱ_ሕይወት_አለው! የእግዚአብሔርን ቃል ስታሰላስሉ በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ያለው ሕይወት በመንፈሳችሁ ትቀበላለች!
#MeditatingUponTheWord!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በዳግም ልደት ከእግዚአብሔር የተወለደ ሰው ፍጹም በሆነ በረከት ተባርኳል: የሚጎድለውም የለም: ነገር ግን ይህ በረከት በሰማያዊ ስፍራ ያለ በመሆኑ:አእምሮን በክርስቶስ እውቀት በማደስ ምድር ለይ የመለማመድ ሃለፊነት አለበት!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
#የኢየሱስ_ስም!
👉አብ ያለ ልክ ያከበረው ስም!
👉ስልጣን የተቀበልንበት ስም!
👉የዳንበት ስም!
👉የተፈወስንበት ስም!
👉ነጻ የወጣንበት ስም!
👉የተቀባ ስም!
👉የምናሸንፊበት ስም!
👉የምንገዛበት ስም!
👉ጉልበት ሁሉ የሚንበረከክለት ስም!
👉ከስሞች ሁሉ በላይ የሆነ ስም!
“የጌታን ስም የሚጠራም ሁሉ ይድናል።”
— ሐዋርያት 2፥21
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥17-18
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በሸክላ ሠሪው እጅ
---------------------------
----------------------------
“ከጭቃም ይሠራው የነበረ ዕቃ በሸክላ ሠሪው እጅ ተበላሸ፥ ሸክላ ሠሪውም እንደ ወደደ መልሶ ሌላ ዕቃ አድርጎ ሠራው።”
— ኤርምያስ 18፥4
በመንፈስ ልጅ እያለሁ ልጅ ስህተት እንደሚሰራው ስህተት ሰርቼ አውቃለሁ ከእግዚአብሔር እውነትም ፈቀቅ ብዬ አውቃለሁ! ለእግዚአብሔር ስርዓትም ከመታዘዝ የወደኩበት ጊዜ ነበር: እውነት ለመናገር ያለቀልኝ: የተበላሸው ያለፈበኝ መስሎ የተሰማኝ ጊዜ ነበር!!! ነገር ግን መንፈሳዊ ህጻንነቴን እና የስጋ ምኞቴን ተጠቅሞ ፈትኖ ለጣለኝ ሰይጣን እግዚአብሔር አልተወኝም: ባይመስለኝም በዛ ፈታኝ ጊዜ እንኳ መልካም እጁ ለይ ነበርኩ: የተበላሸው የነበረ ቢሆንም ሸክላ ሠሪው የተበላሸውን መልሶ እንደወደደ አድርጎ እንደሚሰራው እግዚአብሔርም በሰራተኛ እጆቹ እኔን መልሶ ለክብር የሚሆን እቃ አድርጎ ሰራኝ! ቢያስጨንቀኝም ለመልካም ሆኖልኛል: አሁን ስርዓቱን አስተምሮኛል: ሕጻንነቴን አስቀርቶ እንደምወደው ሰርቶኛል: : ተወዳጆች ሆይ በምኞታችሁ ስትፈተኑ አሁን ወድቃችሁ እንኳ ቢሆን በመልካሙ እግዚአብሔር እጅ ናችሁ! ሰይጣን ተስፋ እንድያስቆርጣችሁ አትፈቀዱለት: እግዚአብሔር እንደገና ይሰራችኋል! አሁን ባላችሁበት "እግዚአብሔር ሆይ አንተ እንደ ሸክላ ሰሪው ነህ እኔ እንደ ሸክላው ነኝ: እንደወደድክ አድርገህ ስራኝ" ብላችሁ ጸልዩ።
“የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ይህ ሸክላ ሠሪ እንደሚሠራ በውኑ እኔ በእናንተ ዘንድ መሥራት አይቻለኝምን? እነሆ፥ ጭቃው በሸክላ ሠሪ እጅ እንዳለ፥ እንዲሁ እናንተ በእኔ እጅ አላችሁ።”
— ኤርምያስ 18፥6
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የእግዚአብሔር ልጆች በዚህ በሚያስጨንቅ ዘመን እንኳ ፍጹም ሰላም የምናገኝበት ሚስጥር አለልን ይህም #በእግዚአብሔር_ፈቃድ_ውስጥ_መኖር_ነዉ!!!
የልብ ሰላም ምድር ለይ የትኛውም ገበያ ውስጥ የሚገኝ አይደለም! ሁሉም ነገር የሚያስከፋ ስሆን በቀስታ ፊታችሁ ፈገግ የሚል ይህ ይገባችኋል! በልባችሁ ስላለው ፍጹም ሰላም እግዚአብሔርን አመስግኑት!!!
#appreciate God for the heart peace!
#peace_is_everything!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የሚያስጨንቅ ዘመን (𝙥𝙚𝙧𝙞𝙡𝙤𝙪𝙨 𝙩𝙞𝙢𝙚𝙨)
--------------------------------------------------------
በዚህ ዘመን የሰውን ልጅ ክህደት( 𝙖𝙥𝙤𝙨𝙩𝙖𝙨𝙮) በግልጽ የሚያሳዩ 18 የወደቀ ሰው ባሕርያት:-
1-ራስን መውደድ (𝙨𝙚𝙡𝙛 𝙡𝙤𝙫𝙚)
2-ገንዘብን መውደድ (𝙡𝙤𝙫𝙚 𝙤𝙛 𝙢𝙤𝙣𝙚𝙮/𝙘𝙤𝙫𝙚𝙩𝙤𝙪𝙨)
3-ትምክህት (𝙗𝙤𝙖𝙨𝙩)
4-ትዕቢት (𝙥𝙧𝙞𝙙𝙚)
5-ተሳዳቢነት (𝙗𝙡𝙖𝙨𝙥𝙝𝙚𝙢𝙮)
6-አለመታዘዝ (𝙙𝙞𝙨𝙤𝙗𝙚𝙙𝙞𝙚𝙣𝙘𝙚)
7-አለማመስገን (𝙪𝙣𝙩𝙝𝙖𝙣𝙠𝙛𝙪𝙡)
8-አለመቀደስ (𝙪𝙣𝙝𝙤𝙡𝙮)
9-ያለ ፍቅር መሆን (𝙬𝙞𝙩𝙝𝙤𝙪𝙩 𝙣𝙖𝙩𝙪𝙧𝙖𝙡 𝙖𝙛𝙛𝙚𝙘𝙩𝙞𝙤𝙣)
10- ለእርቅ አለመሸነፍ (𝙩𝙧𝙪𝙘𝙚𝙗𝙧𝙚𝙖𝙠𝙚𝙧𝙨)
11- ሐሜት (𝙛𝙖𝙡𝙨𝙚 𝙖𝙘𝙘𝙪𝙨𝙚𝙧𝙨)
12- ራስን አለመግዛት (𝙞𝙣𝙘𝙤𝙣𝙩𝙞𝙣𝙚𝙣𝙩)
13- ጨካኝነት (𝙛𝙞𝙚𝙧𝙘𝙚)
14- መልካሙን አለመውደድ (𝙙𝙚𝙨𝙥𝙞𝙨𝙚𝙧𝙨 𝙤𝙛 𝙜𝙤𝙤𝙙)
15- ከዳተኝነት (𝙩𝙧𝙖𝙞𝙩𝙤𝙧𝙨)
16- ችኩልነት (𝙝𝙚𝙖𝙙𝙮)
17- ከሆኑት በላይ ስለ ራስ ማሰብ (𝙝𝙞𝙜𝙝𝙢𝙞𝙣𝙙𝙚𝙙)
18- ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን መውደድ (𝙥𝙡𝙚𝙖𝙨𝙪𝙧𝙚 𝙡𝙤𝙫𝙚𝙧𝙨)
-------------------------------------------------------
👉እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን የሚያመልኩ የሚመስሉ እና የሚመስላቸው ነገር ግን ሃይሉን የካዱ ናቸው!! እንደዚህ አይነቱ ባሕርይ ካላችሁ ራሳችሁን አንጹ እንደዚህ አይነት ባሕርይ ከላቸው ሰዎች ደግሞ ራቁ!
#የተባረከው_ቤዛችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ተመልሶ_ይመጣል!!!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
በመንፈሳችሁ የበሰላችሁ ስትሆኑ ስጋችሁ የለመንፈሳችሁ ፈቃድ እና እውቅና ውጪ ምንም ማድረግ አይችልም። #ይህ_ስጋዊ_ምኞትን_እና_ኃጢአትን_ስታሸንፉ_ነዉ።
የመንፈሳችሁ ጥንካሬ ደረጃ ስጋን የሚታሸንፉበትን እና ለእግዚአብሔር የምትታዘዙበትን ልክ ይወስነዋል! ስለዚህ መንፈሳችሁን የእግዚአብሔርን እውነት እና የመንፈስ ቅዱስን ሃይል በመመገብ በሁሉም ረገድ ጠንክሩ! #የእግዚአብሔርን_ቃል_ያለማቋረጥ_አሰላስሉ!!
#Spiritstyle
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
