en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
without the holy Spirit your study Of scriptures is Hypocrisy! @TheDeepThingsOfTheSpirit

የቅዱሳት መጽሐፍት ደራሲ (Author) መንፈስ ቅዱስ ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስን የለ መንፈስ ቅዱስ መሪነት ለመረዳት የሚደረግ ጥናት ግብዝነት ነዉ። መጽሐፍ ቅዱስን ለመረዳት በሁለት ጆሮ መካከል ያለች ትንሽ አእምሮ ብቁ አይደለችም! ከምታስቡት በለይ የተወሳሰበ መጽሐፍ ነዉ።እያንዳንዱ መጽሐፍ ከፍጥረታዊው ሰዉ የመረዳት አቅም በለይ የሆነ ጥልቅ ስነ መለኮትዊ ትምህርት መስጠቱ እንዳለ... የባህል፣ የአመለካከት፣ የስነ ቋንቋ ወዘተ ውስብስብነት አለው ከዛም በለይ በእጃችሁ የያዛችሁት የ66 መጻሕፍት(scriptures) ስብስብ አሁን ባለበት ደረጃ የትርጉም ( በስህተት እና ሆነ ተብሎ) የተዳረጉ ዝንፈቶች ይኖሩበት ይሆናል። የመጽሐፉ ደራሲ ያስፈልጋችኃል፤ ክርስቲያን ሁሉ የእግዚአብሔርን መንፈስ የሚሰማበት ጆሮ ሊኖረው ይገባል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Your fellowship is very important DON'T FOLLOW A MAN who is not worth following!!! # ➤Don't follow a channel which is not worth following! ➤Don't follow a friend who is not worth following! Don't play with your life! Be a person of value!

የአንድን አመት ዋጋ ( #ለማወቅ_ከፈለግህ ) ክፍሉን የደገመን ተማሪ ጠይቀው፤ የአንድን ወር ዋጋ............ካለወሩ የተወለደን ሕፃን የወለደችን ሴት ጠይቃት፤ የአንድን ሳምንት.............በየሳምንቱ የሚወጣን ጋዜጣ አሳታሚ ጠይቀው፤ የአንድን ቀን........የወሳኝ ፈተናን ውጤት ነገ ለማስማት የሚጠብቅን ተማሪ ጠይቀው፤ የአንድን ሰአት......ለመገናኘት የተቀጣጠሩ ትኩስ ፍቅረኞችን ጠይቃቸው፤ የአንድን ደቂቃ.........አውቶብስ ለትንሽ ያመለጠውን ሰው ጠይቀው፤ የአንድን ሰከንድ..........ከአደጋ ለጥቂት ያመለጠን ሰው ጠይቀው፤ የአንድን ሚሊ ሰከንድ........በኦሎምፒክ ሩጫ ለጥቂት የተቀደመን ሯጭ ጠይቀው። (ከወደላይ ያለው ፅሁፍ #የጊዜ አጠቃቀም ጥበብ ከሚለው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መፅሀፍ ሳነብ ያገኘሁት ነው።) እግዚአብሔር ለሁላችን እኩል ከሰጠን ሀብት ተርታ የሚሰለፈው #ጊዜ ቢሆንም ብዙዎቻችን ይህንን ጊዜ እንደ ሀብት ባለማየትና በአግባቡ ባለመጠቀማችን ገሚሱ ለትልቅነት ሌላው ደግሞ ለትንሽነት ተግባር ራሱን አሳልፎ ሲሰጥ ይስተዋላል ውድ እህቶቼና ወንድሞቼ ጊዜያቹን አትርፉበት እንጂ ልክ ባልሆነ የአያያዝ ሁኔታ አታባክኑት። አስተውሉ ክርስቶስን እንድትመስሉ ከማያግዛችሁ ከየትኛውም የህይወት አይነት ስር ጊዜያችሁን አጥብቃችሁ ጠብቁ!!...ዛሬ የምትውሏት አንዲት ቀን የነገ ህይወታችሁ ለይ በብዙ ተፅእኖ ታሳድራለችና ሁሉንም ነገር ለመስራትና ለመድረስ የማይበቃ ጊዜያችንን ጠቃሚ የሆነ ነገር ለይ ብቻ አውለነው እንለፍ መልእክቴ ነው!! .. .. .. .. .. 1 ተሰሎንቄ 5 (1 Thessalonians) 6፤ እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ።

Life is not a game, get serious with life!

ብዙ ጽሑፎች አንብባችኃል: ብዙ ድምጾች ሰምታችኃል ነገር ግን ያነበባችሁት ጽሑፍ ወይም የሰማችሁት ድምፅ ብቻ ሰይሆን ያልጠቀማችሁ የእግዚአብሔር ቃልም እንዳለ መናገር እችላለሁ! ወደ ውስጣችሁ የምገባ የትኛውም ነገር እናንተን መጥቀም ካለበት ጊዜ ሰጥታችሁ ከራሳችሁ ጋር መዋሃድ ይኖርባችኋል።በዚህ ቻናል መልእክቶች በጽሑፍም በድምጽም የምናስቀምጠው ለጊዜው እናንተን ለማነሳሳት ሰይሆን በቀጣይነት ፍጹም ለውጥን መለማመድ እንድትችሉ እና እንድንችል ነዉ!

ከእለታት አንድ(፩) ቀን በምእናቤ እርሳስ:የተሳለው ያ ሰው በሀሳቤ ንፋስ:የሚመላለሰው ማለዳ ተነሳ:ዘር ይዞ በእጁ ሀደራ ብሎት ነው:የላከው ወዳጁ እስከሚለያዩ:መንገድ አሳይቶት እኔም እመጣለሁ:ብሎ ብዙ መክሮት ሰደደው በቀጭን:በጠባቡ መንገድ ታምኖ እንዲያገለግል:ወደ ሌላ እንዳይሄድ ....👞👞.... እያሰላሰለ:መንገዱን ቀጠለ ዘር ሚዘራበትን:ስፍራ እየፈለገ ሀደራ ሰንቆ:እምነት ተቀብሎ ጨርሶ እስኪመለስ:እጅጉን ቸኩሎ ፈጠነ ተጓዘ:ቀናት ተከተሉት ብርድና ጨለማው:እያደካከሙት ለገባለት ኪዳን:ውጣውረድ ቢመጣ ዙርያው ባዶ ሲሆን:ቢመስለው ክፉ እጣ አመታት ሲነጉዱ:ወቅትም ሲፈራረቅ የወዳጁ መምጠት:ሲሆንበት ሩቅ ችላ ማለት ያዘው:ድሎትን ተመኘ ሩቅ ሚታየውን:ሰፊውን እያየ የተቀበለውን:ዘሩን አስቀምጦት መሬቱን ቆፍሮ:ሀደራውን ቀብሮት ሄደ ኮበለለ:ጓዙን ጠቀለለ በእጁ ያለውን ትቶ:ለሌላው ዋለለ ...🌍🌎... ፊቷን ፈገግ አርጋ:አለም ኖር ስትለው አሳስቃ እንድትወስድ:ያልተገነዘበው ለመኖሪያው ሚሆን:እረፍት እያሰበ በሞኝነት ልኬት:ኻላውን ኮነነ መሰረት መስርቶ:በፍላጎቱ ልክ አቆመ ከዳር ዳር:ለድካሙ ምትክ ማገሩን ጨርሶ:ጣራውን ሊመታ ቀና ከማለቱ :ቤቱ ወደቀበት:ራሱም ተመታ ቀድሞስ መሰረቱን:አሸዋ ለይ ጥሎት እንዴት ሊፀናለት:ንፋሱ ባለበት 😩 ...........😩 ያ የሀሳቤ ሰው:ክፉኛ ወደቀ መነሳት አቃተው:ጉልበቱም አለቀ ከእለታት አንድ ቀን:ባለቤቱ መጣ ዋጋውን ሊከፍለው:ፍሬውን ሲያመጣ በጠባቧ መንገድ:እያፈላለገው አልቻለም ሊያገኘው:ባለሀደራውን ሰው ሲቆይበት ጊዜ:እንዳይመጣ መስሎት አወይ ትቶ ሄዷል:ዋናውን ረስቶት ድንገት ከሀሳቤ:ባንኜ ተነሳሁ ልቤን ፍርሀት ሲለው:መፅሀፉን አነሳሁ አየሁ የቤቴን ጥግ:በቃሉ መሰረት የቆምኩበትን ልክ:እኔም ለዛች እለት .....🤔...🤔... ወዳጄ በእጅህ:ምን ያህል ትርፍ አለህ? በሀሴት ልትመልስ:ለላከህም ታምነህ ከምን ነው የቆምከው:እግርህ የተተከለው ዘር ዘርተህ በትዕግስት:ኖረህ ምታተርፈው ቀኑ ሳይጨልም:በሩ ሳይዘጋ በቤቱ ተገኝተህ:ከቤቱ ሳትጠፋ መኖርን ፈልገህ:ከህይወት ሳትጎድል ሀይልህን አድስና:ጠብቀው ሳትደክም ከእለታት አንዱ ቀን:ቅርብ ነው እንንቃ ጌታ በደጅ ነው:ይህ አለም ሊያበቃ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ስለሁሉም ነገር ለማወቅ የሚደረግ ጥረት ብዙ ሰዎች የሚሰሩት ስህተት ነዉ። ስኬት በአንድ ነገር ለይ ጥልቅ መረዳት ላላቸው እንጅ ስለነገሮች ሁሉ የተቀነጨበ እውቀት ላላቸው አይደለም። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

"እውነትን ተጠቀሙ" የምታነቡትን ተጠቀሙ : እውነትን ተጠቀሙ በአእምሮአችሁ ውስጥ አጽኑት: አድራጊዎች ሁኑ: የጸሎታችሁ ክፍል አድርጉት: ለሌሎችም እንድደርስ አድርጉ : በራሳችሁ ሕይወት ተግባራዊ አድርጉት : ምን ያህል ተጨማሪ ብርሃን እንደሚያስፈልጋችሁ ለማወቅ ስሩ። ራሳችሁን እንደዚህ ብላችሁ ጠይቁ " በገባኝ እውነት ብርሃን እየተመላለስኩ ነዉ?" "ሕይወቴን እየለወጠው ነዉ?" ➤ወንጌላዊ ኢቫን ሮበርት @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ከምትሰሙት እና ከምታዩት ነገር ጋር ህብረት ትፈጥራላችሁ። ህብረታችሁ ደግሞ የሕይወታችሁን አይነት ይወስነዋል! ለመምራት ብቁ ያልሆኑ ሰዎችን አትከተሉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

መስማት የሌላበችሁን ድምጽ አትስሙ ፣ ማየት የሌለባችሁን ምስል አትመልከቱ ፣ ማንበብ የሌለባችሁን ጽሑፍ አታንብቡ እናም መከተል የሌለባችሁን ሰዉ አትከተሉ።

ወንድሞቼ እና እህቶቼ አንዴ እንቁጣጣሽ አንዴ ደግሞ መስቀል ሌላ ጊዜ ደግሞ ልደት ...ወዘተ እያላችሁ ከንቱ በዓል እያከበራችሁ እና ፍጹም ለውጥን መለማመድ ሳትችሉና ካላችሁበት ሰትንቀሳቀሱ ዘመናችሁ እንዲያልቅ አትፈቀዱ! ከምቾት ክልላችሁ ውጡ እና ፍጹም ለውጥን ተለማመዱ! መለወጥ የግድ አለብኝ የእግዚአብሔር ፀጋ ልለውጠኝ በእኔ ነዉ በሉ!!!

🦋🔥Transfiguration🔥🦋 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉ይህን መልእክት ለእህቶች share አድርጉልኝ! ወንዶችም አንብቡት: በጣም የሚደንቅ ብርሃን ነዉ: የእግዚአብሔር ቃል ተናጋሪው መስታወት ነዉ ትላላች መልካህ! ተባረኪ!!👏

✍ተናጋሪው መስታወቴ ከበሬ መውጫ ላይ:የቆመው መስታወት ሚያሳየኝ አካሌን:ሁሌ ስመለከት ራመድ ወደ ፊት:መጣ ወደ ኻላ ደግሞ ፈገግ ኮስተር:ምስሌን ሳሰላ ይሄ መስታወቴ:በቁመት ልኬ ነው ሚያሳየው ከራሴ:እስከ እግር ጥፍሬ ነው አንድ ቀን እንዲህ ሆንኩ:ራሴን ላሳምረው ምሄድበት ቦታ:መችስ ቢኖረኝ ነው ከንፈሬን ሳደምቅ:አይኔንም ስኩለው ፀጉሬን ሳበጥር:ስጥር ላዘምነው ከግማሽ ሰአት በላይ:እንዲህ አሳለፍኩኝ እንዳላረፍድ ብዬ:ከቤቴ ወጣሁኝ መቼም ዛሬ ለኔ:ሌላ ቆንጆ የለም እራሴ እየገባሁ:በፈጠርኩት አለም በማልፍበት መንገድ:ይመለከቱኛል አላፊ አግዳሚው:ሁሉ ይታዘበኛል ገና ከመግባቴም:የሚያየኝ ሰው በዛ ስቆ ሚያስቅብኝ:እጁን እያነሳ ይባስ ተሸማቀቅኩ:አንዱ አፉን ከፈተ የለፋሁበትን:ድክመቴን ያላየ "ሲያጌጡ..." ሚለውን:ተረቱን ተርቶ ፊትሽን ጥረጊው:አለኝ ሶፍት አውጥቶ 👠👠🏃‍♀️🏃‍♀️🏃‍♀️🏃‍♀️ ቤቴ ተመልሼ:መስታወቴን አየሁ ፊትለፊቱ ቆሜ:ላይሰማኝ ተጣላሁ ምን አለ ብትነግረኝ:እንዳላማረብኝ ይህን አስተካክይ:እያልክ ብትመክረኝ ጫማዬን አንስቼ:ሁለት ሶስቴ አልኩት ቆሞ እንዳልነበረ:ዱቄት አደረኩት ይህን ሁሉ ቆማ:ምትመለከተው ታናሼ ናት ብዬ:ሀሳቧን ምንቀው መናገር ጀመረች:እኔን አረጋግታ እንቺ እያለችኝ:እጆቿን ዘርግታ አንቺ ላላየሽው:ላልተገነዘብሽው ሌላው እየናቀ:ልብሽን ላራደው እስቲ ተመልከቺው:ውስጠትሽን ዘልቀሽ ያንቺ ያልሆነውን:ሁሉን አስወግደሽ አለችኝ፦ካስተዋልሽ:ከተነጋገርሽው ይሄኛው መስታወት:ሚናገር ድምፅ ነው 👩‍👧(🗣📖)🎙🎙 እኔም ተቀበልኳት:ራሴን ማየት ጀመርኩ ከቃሉ መስታወት:እየተነጋገርኩ ልባም ሴት ዋጋዋ:ከእንቁ የሚበልጥ ለመልካም ተጋድሎ:ጠባቡን የምትመርጥ ወገቧ የታጠቀ:ክንዷ የበረታ ጨክና የቆመች:ከብርሀን ተርታ ብርታት ከበሬታን:ልብሷ ያደረገች አፍዋን በጥበብ ቃል:ከፍታ የተገኘች የሀኬት እንጀራን:ፈፅሞ ማትበላ ምስጋና ሚያተርፉ:ልጆች ምታፈራ ይህች ናት ታድያ:ከሁሉ የምትበልጥ ለፅድቅ ቅድስና:ቅድምያ የምትሰጥ 🤔🤔(..🤝..) ራሴን አየሁት:ከሁሉም ባሻገር ይሄ መስታወቴ:ህይወትን ሲናገር ለካ የእግዚአብሔር ቃል:ሁሉንም ያሳያል ልብን ኩላሊትን:መርምሮ ይደርሳል ውበትም ሀሰት ነው:ደምግባትም ከንቱ በዛኛው መስታወት:እንዳትሳሳቱ!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#የጊዜ_ተግባር!!! እግዚአብሔር ጊዜ የሰጣችሁ እንዲሰራላቸሁ ሰይሆን እንድትሰሩበት ነዉ። ወዳጆቼ ጊዜ አንድም ነገር አይለውጥም እናንተ ግን በጊዜ ውስጥ በነጻ ፈቃዳችሁ መለወጥ ያለበትን ነገር ሁሉ መለወጥ ትችላላችሁ! ጊዜ ነገሮችን እንደሆኑት የመግለጥ ተግባር ብቻ ነዉ ያለው። ይህ ማለት ካልተለወጣችሁ አለመለወጣችሁን ከተለወጣችሁ ደግሞ መለወጣችሁን ይገልጣል። የጊዜ ተግባር ነገሮችን እንደሆኑት መግለጥ ብቻ ነዉ!! 🦋🔥 Transfiguration🔥🦋 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

photo content

😍😍😍😍😍 Christ is coming The king of Glory No more sorrow No more weeping Tell the story among the nations Christ is coming bye and bye!😍 @TheDeepThingsOfTheSpirit

ለውጣችሁ ይህንን ዓለም የማስደነቅ ጉዳይ ብቻ አይደለም! በሚመጣውም ዓለም የሚጠቅማችሁ ሃይል ነዉ!።