TheDeepThingsOfGod
Open in Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Show more1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 810
የዘመን መጨረሻ ለይ መሆናችንን የሚጠቁም ምን አለ?
➤በዘመን መጨረሻ ጥናት ውስጥ የእስራኤል ብሔራዊ ሁኔታ እጅግ ትልቅ ትርጉም አለው።
ሉቃስ 21 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁹ ቀጥሎም እንዲህ ሲል ይህን ምሳሌ ነገራቸው፤ “በለስንና ዛፎችን ሁሉ ተመልከቱ፤
³⁰ ቅጠሎቻቸው አቈጥቊጠው ስታዩ፣ በዚያን ጊዜ በጋ መቃረቡን ራሳችሁ ታውቃላችሁ።
³¹ እንዲሁ ደግሞ እነዚህ ነገሮች መፈጸማቸውን ስታዩ፣ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች ዕወቁ።
➤በጌታችን ንግግር መሰረት የባለስ ማቆጥቆጥ(የእስራኤል እንደገና ወደ ብሔራዊ ህልውና መምጣት) የመጨረሻው ምልክት ነዉ የሚሆነው።
➤ሁላችንም እንደምናውቀው እ.እ.አ በ 1949 እስራኤል ማቆጥቆጥ ጀምራለች። ጌታ በበለስ ማቆጥቆጥ እና በእግዚአብሔር መንግስት መምጣት መካከል አንድ ትውልድ እንደማያልፍ ተናግሯል። በመጽሐፍ ቅዱስ አቆጣጠር አንድ ትውልድ 100 ዓመት ነዉ።
➤እነዚህ ሁሉ ግልጽ ሆነው እየታዩ ነዉ። ከሁሉም በይ የሚያስገርመው ግን "ἀποστασία" ወይም "apostasia" ነዉ። ይህ የግርክ ቃል ነዉ። በአማርኛ "ክህደት" ተብሎ ተተርጉሟል።
"apostasia" የሁለት የግሪክ ቃላት ስሪት ነዉ።
➤የመጀመሪያው ቃል "apo" ስሆን ትርጉሙም "መለየት ፣ መተው " ወይም በእንግሊዘኛው "Departure" ማለት ነዉ።
➤ሌላው ቃል "stasia" ስሆን ትርጉሙም "መቆም ፣ እምነት ፣ መሰረት " በእንግሊዝኛው "Stand" ማለት ነዉ። "stasia" ሌላም ትርጉም አለው "ማንነት" በእንግሊዝኛው "being" ማለት ነዉ። ስለዝህ በጥቅሉ "apostasia" ማለት "ከቆሙበት መለየት ፣ ከእምነት መለያ ፣ " ....departure from the stand, departure from faith" ይባላል።
ይህንን ቃል ሐዋርያው ጳውሎስ ከዛሬ 2000 ዓመት በፊት ለተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን በጻፈው መልእክቱ ለይ "የጌታ ቀን ከመምጣቱ በፊት "ክህደት" /
apostasia/ መምጣት እንዳለበት። ይህ ማለት የመጀመሪያ ሰዎች "ከእምነት እንደሚለዩ ፣ ከእግዚአብሔር ቃል እውነት እንደሚወድቁ ፣ የቆሙበትን የወንጌል መሰረት እንደሚለቁ ...የገለጸበት ቃል ነዉ። ይህንን ግልጽ በሆነ ሁኔታ በዓለም ሁሉ እያየን ነዉ። ሰዎች በእግዚአብሔር የማያምኑ የወንጌል ጠላቶች ፤ ከእግዚአብሔር ይልቅ የራሳቸውን ሰይንሳዊ ጥናቶች እውነት አድርገው የሚያቆሙ ሆነዋል። ዓለም ከመጀመሪያው ከእግዚአብሔር ተለያይታለች። ነገር ግን ቤተክርስቲያን ውስጥም ይህ "ከእምነት መለያየት"/
apostasia/ ግልጽ ሆኖ እየታየ ነዉ። የወንጌል መሰረታዊ እውነቶች ተዛብተዋል። ወንጌል ትክረቱን ከኢየሱስ ክርስቶስ ለይ እንድያነሳ ይደረጋል። በቤተክርስቲያን ውስጥ ሆኖ "ክርስቲያን" መሆን በራሱ ምን ማለት መሆኑን የማያውቅ አያሌ ሰዉ አለ። ሰዎች ራሳቸውን የሚወዱ ፣ ገንዘብን የሚወዱ እና ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወዱ ሆነዋል።
➤ሌላው "apostasia" ሁላችንም በግልጽ የምናየው የሰዎች "ከማንነት መለያየት" ወይም "departure from being" ነዉ። ይህ በዓለም ሁሉ እየሆነ እያየን ነዉ። ወንድ ከወንድነት ተለያይቶ ወንድን ማግባት ከጀመረ ቆይቷል። ሴት ከተፈጥሮ ውጭ ከሴትነት ተለያይታ ሴትን ስታገባ በየአደባባዩ ይታያል። አባት ከአባትነት ተለያይቶ የገዛ ልጁን ይደፍራል። እናት በውስጧ ያለውን በትክክለኛው መንገድ የመጸነስ ፣ የመውለድ እና አጥብታ የማሳደግን የእናትነት ባሕርይ ተለያይታ ጽንስ ለማስወረድ (abortion) ድፍረት አግኝታለች።
👉ἀποστασία
👉apostasia
👉ክህደት
➤የተባረከው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልሶ ይመጣል። አይዘገይም።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
“በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።”
— 2 ዜና 7፥14
#➤የእግዚአብሔርን ሃሳብ በምድር ለይ የምትፈጽም የክርስቶስ አካል ናት። ቤተክርስቲያን። ነገር ግን ከእግዚአብሔር እውነት እርቀ ከራሷ ጋር እንኳ መስማማት አቅቷታል።
#➤ይህንን ጽሑፍ የምታነቡ ወጣቶች ሁሉ የቤተክርስቲያን አንድ አካል በመሆናችሁ እግዚአብሔር እናንተን ለመጠቀም እና አካሉን ብሎም የጨለመውን ዓለም በወንጌል ብርሃን መሙላት ይፈልጋል! በዙሪያችሁ ካለው ማንኛውም ግርግር ወጣ በሉን እግዚአብሔርን የሚሰሙ ጆሮዎች ለራሳችሁ አድርጉ። በዝህ በዘመን መጨረሻ እና በመጽሐፉ የመጨረሻ ገጽ ለይ በእግዚአብሔር መንግስት መዝገብ ለይ ስራችሁ ይጻፍ።
#➤አንተ ወጣት ከዝህ ጠማማ ትውልድ እራስህን እንድትጠብቅ እመክርሃለሁ!!!
(Don't be deceived, Just focus on God and his purpose in your life)
#➤የመጨረሻው መጨረሻ ለይ ነን እግዚአብሔር ደግሞ ቤተክርስቲያንን ማንቃት እና ብዙዎችን ማዳን ይፈልጋል ። ለእግዚአብሔር ተገኝለት።
1 810
#➤God lives in you!
#➤You contain God!
#➤And I can surely say, If you can get the revelation of this you can't be the weakest in your Generation!!!
1 810
HOLY SPIRIT
**********
👉Holy Spirit in you is the representation of the presence of God the father and Jesus Christ.
(Benny hinn said "the Holy Spirit is Jesus Unlimited")
➤I think that's absolutely right! He is Jesus without limits and boundaries!
“Jesus answered and said unto him, If a man love me, he will keep my words: and my Father will love him, and we will come unto him, and make our abode with him.”
— John 14:23 (KJV)
#➤Notice Jesus spoke about the coming of the Holy Spirit on the above verses.“And I will pray the Father, and he shall give you another Comforter, that he may abide with you for ever;”
— John 14:16 (KJV)
So, this is why we say the Holy Spirit is the representation of the person of God the Father and Jesus Christ!!!
➤Having the Holy Spirit in you means, you have the whole God in you!!!
➤God resides in side you! If you can comprehend this truth you can set your Generation free!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
👉ምንድነው መጽሐፍ ቅዱስ እንዳላነብ ቃሉን እንዳላሰላስል እና እንዳልጸልይ እንቅፋት የሆነብኝ??? የሴት ጓደኛ ፣ የወንድ ጓደኛ ፣ የማህበራዊ ድረገጽ ወይስ የራሴ ድካም!??? ምንም ይሁን ምን ዛሬ በመሰጠት መሰዊያ ለይ ለቃጥለው ወስኛለሁ!!!
👉ለጌታ የተገባ ሰው ለመሆን ወስኛለሁ!!
ማቴዎስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤
³⁸ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።
³⁹ ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል።
➤የትኛውንም ነገር ከእግዚአብሔር ጋር ካለኝ ህብረት አላወዳደርም። ይህንን ውሳኔ ከልባችሁ የእውነት ማድረግ ከቻላችሁ ለእግዚአብሔር ትውልድን የሚመልስበት የክብር እቃ ትሆናላችሁ።
1 810
የእግዚአብሔር ሕይወት የሚቀዳው ከእግዚአብሔር ቃል እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በሚደረግ የማይቋረጥ ህብረት ነዉ!!!!
የእግዚአብሔር ሕይወት ሞት የማይጎበኘው ውድቀት እና ማጣት የሌለበት ሕይወት ነዉ።
👉የእግዚአብሔርን ቃል ያለማቋረጥ በማሰላሰል ቃሉ በሕይወታችሁ መገለጫ (Expression) እንድያገኝ ማድረግ ትችላላችሁ።
መዝሙር 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል።
³ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።
👉መዝሙረኛው ዳዊት በሚሰራው ነገር ሁሉ የሚከናወንበት ምስጥር የሄው ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል ትዝታው ነበር። ከበጎች እረኝነት ጀምሮ የእስራኤል እረኛ እስክሆን ለአንድም ቀን ያላቆመው ነገር የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰል ነበር።
1 810
“በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥12
➤እግዚአብሔርን እየመሰላችሁ ለመኖር የምታደርጉት ውሳኔ እና መሰጠት በሰዎች ዘንድ የሚያስመሰግናችሁ ወይም የሚያስጨበጭብላችሁ አይደለም። በጓደኞቻቸው ፤ በምትወዷቸው ሰዎች አንዳንዴ ደግሞ በቤተሰቦቻቸው እንኳ ሊያስነቅፋችሁ ይችላል። ምክንያቱም እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድ ለፍጥረታዊው ሰው ከምመች ብዙ ነገር ይለያችኃል!!!!
1 810
“የፈጣሪውን መልክ እንዲመስል በዕውቀት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችኋል፤”
— ቆላስይስ 3፥10 (አዲሱ መ.ት)
➤የለበስነው አድስ ሰው እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚያስፈልገውን ሁሉ በውስጡ የያዘ የፈጣሪውን መልክ እንድመስል እውቀትን በማግኘት የሚለወጥ ነዉ።
(👉የተጠራነው በነገር ሁሉ እግዚአብሔርን ለመምሰል ነዉ😍)
➤የእውነት እውቀት ደግሞ ለዝህ ውጤት ምክንያት ነዉ። እግዚአብሔርን ፤ በክርስቶስ ያደረገውን ፤ ፈቃዱን ፤ ዓላማውን ለማወቅ ፍጹም ትጋት እንድታሳዩ ላሳስባችሁ።
“ከዚህ የተነሣ እኛ ደግሞ ይህን ከሰማንበት ቀን ጀምሮ እግዚአብሔር የፈቃዱን ዕውቀት በመንፈሳዊ ጥበብና መረዳት ሁሉ ይሞላችሁ ዘንድ ስለ እናንተ መጸለይና መለመን አላቋረጥንም፤”
— ቆላስይስ 1፥9 (አዲሱ መ.ት)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
እግዚአብሔርን ለመምሰል ማደግ።
*************************
➤የክርስትና እምነት የመጨረሻ ግብ እናንተን እግዚአብሔርን ራሱን የምትመስሉ ማድረግ ነዉ። የእግዚአብሔር መልክ (ክብር) እና ምሳሌ (ባሕርይ) ያላችሁ ልጆች ማድረግ ነዉ።
➤ቅዱሳት መጽሐፍት “የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤”
— ቆላስይስ 3፥10 ...ይሉናል። እውቀትን እያገኘ እግዚአብሔርን ለመምሰል በመታደስ የሚለወጥ ማንነት ነዉ ያላችሁ። እውቀት የሁሉም ነገር መጀመሪያ ነዉ። ይህ እውቀት ግን የዓለም እውቀት ሰይሆን የእግዚአብሔር እውቀት ፣ የፈቃዱ እውቀት ፣ የመንፈሳዊ ዓለም እውቀት ፣ በክርስቶስ ያገኛችሁት ማንነት እውቀት ነዉ።
“ስለዚሁ እኛ ደግሞ ይህን ከሰማንበት ቀን ጀምረን የፈቃዱ እውቀት መንፈሳዊ ጥበብንና አእምሮን ሁሉ እንዲሞላባችሁ እየለመንን፥ ስለ እናንተ ጸሎትን አልተውንም፤”
— ቆላስይስ 1፥9
➤እውቀት ግን መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ አይደለም። እውቀት በሕይወት የሚገለጥ መሆን ይኖርበታል። እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ያለውን የፈቃዱን እውቀት ስታገኙ ሰሚዎች ብቻ ሰይሆን አድራጊዎች ለመሆን ትጉ። ቃሉን አድራጊ መሆን የተቀበልነው ትዕዛዝን ነውና።
➤እግዚአብሔርን መምሰልም በቀጥታ ከዝህ እውነት ጋር የተገናኘ ነዉ። ሐዋርያው ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ልጁ ለጢሞቴዎስ ያለውን እንመልከት:
“ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥7
እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚወሰዱ ድርጊቶች:-
1-ለዚህ ዓለም ከሚመች ከየትኛውም ትምህርት ፣ አመለካከት እና ልምምድ መራቅ።
2-በእውነት እውቀት እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድ።
👉እግዚአብሔርን መምሰል ከእግዚአብሔር በመወለድ ብቻ የምትታደሉት በረከት አይደለም። ደግም መወለድ የጉዞው መጀመሪያ እንጅ መጨረሻ አይደለም። መሄድ ያለባችሁ ረጅም መንገድ ከፊታችሁ አለ።
“እንግዲህ እነዚህን የመሳሰሉ ብዙ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፣ ሸክም የሚሆንብንን ሁሉ፣ በቀላሉም ተብትቦ የሚይዘንን ኀጢአት አስወግደን በፊታችን ያለውን ሩጫ በጽናት እንሩጥ።”
— ዕብራውያን 12፥1 (አዲሱ መ.ት)
👉ስለዚህ እግዚአብሔርንም መምሰል #በመለማመድ የሚመጣ ውጤት እንጂ በአንድ ጀንበር የሚፈጠር ታዓምራት አይደለም።
➤ሐዋርያው እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድን ከአካል ብቃት ልምምድ ጋር በንጽጽር ያቀርብልናል። የአካል ብቃት የምሰራ
ሰው በረጅም ጊዜ ድካም ስጋው ይፈረጥማል። ነገር ግን እንደዚህ ያለ የሰውነት አቋም ለይ ለመድረስ ለረጅም ጊዜ በየቀኑ ማለደ እና ምሽት ክብደት ማንሳት እና አመጋገቡን የተመረጠ መድረግ ይኖርበታል። በዚህ መልኩ ሁሉም ሰው በግልጽ ልመለከተው የምችለው ለውጥ ሰውነቱ ላይ ይመጣል።
➤እግዚአብሔርን መምሰልም እንደዚህ በነጻ ፈቃድ ለይ በተመሰረተ ትጋት የሚመጣ ለውጥ ነዉ። ስፖርተኛው ክብደት ማንሳቱን ከተወ ነገሮች ዝቅ እንደምሉ እኛም እግዚአብሔርን የመምሰል መንፈሳዊ ልምምዳችንን ማቆም የለብንም። ይህ ልምምድ የተባረከው ጌታችን ተመልሶ እስክመጣ በዘላቂነት የምቀጥል ነዉ።
➤በመጨረሻም እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስን ማስለመድ መንፈሳዊ ፈይዳ ብቻ ሰይሆን በዝህም ዓለም እጅግ ብዙ ጥቅም እንዳለው ሐዋርያው ያረጋግጥልናል።
“የአካል ብቃት ልምምድ ለጥቂት ነገር ይጠቅማልና፤ ለእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ራስን ማሠልጠን ግን ለአሁኑም ሆነ ለሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው ለሁለቱም ይጠቅማል።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥8 (አዲሱ መ.ት)
አስታውሱ: መንፈሳዊ እድገት የሙሉ ጊዜ ስራችን ነዉ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
👉መንፈስ ቅዱስን ማወቅ
*******
➤በክርስትና ጉዞ ውስጥ እያንዳንዱ ክርስቲያን በቅርበት ሊያውቀው የተገባ አካል ነዉ። የክርስትና እምነት የለ መንፈስ ቅዱስ ትርጉሙን ያጣል። ክርስትናን ከሌሎች ሰዉ ሰራሽ ከሆኑ ሐይማኖቶች የሚለየው አንዱ ነገር የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እኛ መሆናችንን ማስተማሩ ነዉ። ይህም የሆነው መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ በቀጣይነት ለዘለዓለም ያደረ እና የሚኖር በመሆኑ ነዉ። ሃሌሉያ ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።
“ለመሆኑ፣ ሰውነታችሁ በውስጣችሁ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደሆነ አታውቁምን? ይህም መንፈስ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት ነው። እናንተም የራሳችሁ አይደላችሁም፤”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19 (አዲሱ መ.ት)
➤ስለመንፈስ ቅዱስ ቅዱሳት መጽሐፍት የሚያስተምሩት ብዙ ነገር ያለ ብሆንም ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን በጥናት ለማወቅ መሞከር ብዙ ሰዎች እየሰሩት ያለ ትልቅ ስህተት ነዉ። ለመሆኑ መንፈስ ቅዱስን በሁለት ጆሮ መካከል ባለች ትንሽ አእምሮ ጥናት የምትደርስበት እና የምታውቀው ይመስልሃል? አይሆንም።
➤ጌታችን ስለ መንፈስ ቅዱስ በተናገረባቸው ቦታዎች ግልጽ በሆነ መልኩ መንፈስ ቅዱስ የሚታወቅበትን መንገድ አስታውቋል።
“እርሱም የእውነት መንፈስ ነው፤ ዓለም ስለማያየውና ስለማያውቀው ሊቀበለው አይችልም። እናንተ ግን፣ አብሮአችሁ ስለሚኖርና በውስጣችሁ ስለሚሆን ታውቁታላችሁ።”
— ዮሐንስ 14፥17 (አዲሱ መ.ት)
➤ዓለም መንፈሰ ቅዱስን የማይቀበለው የመጀመሪያ ስለማያየው ሁለተኛ ደግሞ ስለማያውቀው ነዉ ይለናል። በተባረከው ክርስቶስ ስለሚያምኑ ስናገር ግን #በውስጣችሁ_ስለምኖር ታውቁታላችሁ ይላል።
➤መንፈስ ቅዱስን የተቀበልነው ስላወቅነው ሰይሆን የምናውቀው በነጻ በእግዚአብሔር ፈቃድ ስለተቀበልነዉ እና በውስጣችን ስለምኖር ነዉ።
➤አንዳንድ ወዳጆቼ "መንፈስ ቅዱስ" ወይም "መንፈስ ቅዱስን ማወቅ" የምል በስነ-መለኮታዊ መልኩ የተተነተነ መጽሐፍ ስለነበቡ መንፈስ ቅዱስን ያውቁ ይመስላቸዋል ነግር ግን ጌታ መንፈስ ቅዱስን የምታውቁት ከራሱ ጋር በሚኖራችሁ የጠለቀ ህብረት ነዉ ያለን።(በውስጣችሁ ስለምኖር ተውቁታላችሁ)
➤መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ ስነ መለኮታዊ ትንታኔ የምሰጡም ሆነ አንድ አማኝ በግሉ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በለው ልምምድ ዙርያ የተጻፉትን ጽሑፎች ማንበብ መልካም ነዉ የሚናቅም አይደለም እንድያውም መሰረት ለመጣል ይረዳል። ነገር ግን መጨረሻው አይደለም!!! በየቀኑ የተወሰነ ሰዓት በጸሎት ክፍላችሁ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መነጋገር ይኖርባችኋል። ይህንን ስታደርጉ የመንፈስ ቅዱስን ባህርያት የልቡን ትኩረት ከእውቀት ያለፈ በሕይወት ማወቅ ትጀምራላችሁ።
➤መጸለይ ተለማመድ! ብያንስ ከእናታችሁ ጋር በሚታወሩት ልክ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መነጋገር ተለማመድ። አስተውሱ መንፈሳዊ ነገሮች የምንለማመዳቸው ናቸው። ከእግዚአብሔር ከራሱ ለመማር ፈልጉ።
“ወንዶች ልጆችሽ ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፤ የልጆችሽም ሰላም ታላቅ ይሆናል።”
— ኢሳይያስ 54፥13 (አዲሱ መ.ት)
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
The Church must do this two things now!
1-Centralizing the message of the Cross of Jesus Christ and bringing it back to it's rightful place!
2-Giving the ministry of headship back to Christ. Who is the blessed head of the Church(his body).
ቤተክርስቲያን አሁን ማድረግ ያሚኖርባት ሁለት ነገሮች:
1-የመጀመሪያው የጌታን የመስቀል መልእክት ማእከላዊ መልእክቷ ማድረግ እና ለዝህም መልእከት የተገባውን ቦታ መስጠት።
2-የራስነትን ተግባር ከሰዎች እና ከየትኛውም ሀይል መልሶ ራስ ለሆነው ለኢየሱስ ክርስቶስ ማስረከብ።
1 810
ሰለም ይብዛላችሁ!
ለኢትዮጵያ እንድትጸልዩ ላሳስባችሁ!
“ተማርካችሁ ለሄዳችሁባት ከተማ ሰላምና ብልጽግናን እሹ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጸልዩላት፤ ምክንያቱም እርሷ ብትበለጽግ እናንተም ትበለጽጋላችሁ።””
— ኤርምያስ 29፥7 (አዲሱ መ.ት)
1 810
👉We need men and women who walk with God, in our generation!!!
👉Make a decision today to pay the price and walk with God, God can transform million through you!!!
👉Open your eyes and see, in what kind of Generation you are, it takes the power of God to speak to this generation not just a certificate from a theological school!!!
👉May find Grace and Mercy to walk with God! Amen.🙏
@TheDeepThingsOfTheSpirit
