TheDeepThingsOfGod
Open in Telegram
Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!
Show more1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 810
Only 5 mb download it and be blessed!!!
what a friend we have in Jesus!!
One of my favorite song!!
1 810
➤እግዚአብሔር አድስ ጅማሬ መስጠት ይችላል።
(God can give You a fresh Start)
“በዙፋንም የተቀመጠው፦ እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ አለ። ለእኔም፦ እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸውና ጻፍ አለኝ።”
— ራእይ 21፥5
➤ብዙ ጊዜ ሰዎች "ሁሉንም እንደገና የመጀመሪ እድል ባገኝ" እያሉ ስናገሩ እሰማለሁ። እውነት ነዉ ሁላችንም ነገሮችን እንደገና ብንጀምር ፤ እነዛን ማሰብ የማንፈልጋቸውን ስህተቶች መሻር ብችል ...ብለን አስበን እናውቃለን። ይሄ ማለት ሁላችንም "እንደገና የመጀመሪ እድል" (A fresh start) ያስፈልገናል ማለት ነዉ። እኔ በሕይወቴ እንደገና መጀመር ያሰፈለገኝ ወቅት ነበር። እናንተም እንደዛው አልነበረም ብትሉኝ እንኳ ቃል እገባላችኃለው አንድ ቀን ሁሉም እንደገና መጀመር እፈልጋለሁ ማለታችሁ አይቀርም።
➤መልካሙ ዜና አባታችን እንደገና የሚያስጀምር ሁሉንም አድስ ማድረግ የምችል መሆኑ ነዉ። ቃል ገብቶልናል ይሄ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ እና በብዙ ደስታ የሚሞላን ይመስለኛል።
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።”
— 2ኛ ቆሮ 5፥17
➤ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥለውት ለሸሹ ደቀመዛሙርቱ ለካደው ጴጥሮስ እንኳን እንደገና ራሱን ተገልጦላቸዋል።
“ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በጥብርያዶስ ባሕር አጠገብ ለደቀ መዛሙርቱ እንደ ገና ተገለጠላቸው፤”
— ዮሐንስ 21፥1
➤ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን!!!🙏
👉አንዳንዶች አሁን ይሄንን አድስ ጅማሮ ትፈልጉ ይሆናል። ለእናንተ መልካም ዜና አለኝ። ሁሉንም እንደ አድስ መጀመር ትችላላችሁ! በምንም አይነት ድካም ውስጥ እያለፈችሁ ልሆን ይችላል። ነገር ግን እግዚአብሔር ታማኝ ነዉ ፀጋው ስለምረዳችሁ ተነሱና እንደአዲስ ጀምሩ።
➤ወደ እግዚአብሔር ተጠጉ። እርሱን ለማወቅ ትጉ "ምን እንዳደርግልህ ትወዳለህ" በሉት።
እግዚአብሔር አድስ ጅማሬ እንድሰጣችሁ በኢየሱስ ስም እጸልያለሁ🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
👉የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት ክፍል 1!
መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብ ብቻውን በቂ አይደለም።
የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት ይጠበቅብናል።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
“ከሁላችሁ የበለጠ በልሳን ስለምናገር እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥18 (አዲሱ መ.ት)
1 810
👉የመንፈሳዊ ዓለም መክፈቻዎች
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
“በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፤ ትንቢትን የሚናገር ግን ቤተ ክርስቲያንን ያንጻል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥4 (አዲሱ መ.ት)
👉ብዙዎቻችሁ ትንቢት መናገርና የክርስቶስን አካል ማነጽ(መገንባት፤ ማስዋብ ፤ መፈጸም ፤ ሙሉ ማድረግ...) እንደምትፈልጉ አውቃለሁ። ደግሞ ልክ ናችሁ ሐዋርያው ጳውሎስም ይህንኑ እንድንፈልግ ያበረታታናል።“ስለዚህ፣ ወንድሞች ሆይ፤ ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ፤ በልሳን መናገርንም አትከልክሉ፤”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥39 (አዲሱ መ.ት)
ነገር ግን ትንቢት "የምያንጸው" እናንተን ሰይሆን ሌሎችን ነዉ።
👉በልሳን ስትናገሩ የምታንጹት እራሳችሁን ነዉ። በልሳን መናገር በሌሎች ቦታዎች ለይ በመንፈስ መጸለይ ተብሎ ተገልጿል።
“በልሳን በምጸልይበት ጊዜ መንፈሴ ይጸልያል፤ አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥14 (አዲሱ መ.ት)
“በሁሉ ዐይነት ጸሎትና ልመና፣ በማንኛውም ሁኔታ #በመንፈስ_ጸልዩ፤ ይህንም በማሰብ ንቁ፤ ስለ ቅዱሳንም ሁሉ በትጋት ልመና አቅርቡ።”
— ኤፌሶን 6፥18 (አዲሱ መ.ት)
“እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤ እጅግ ቅዱስ በሆነው እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤ #በመንፈስ_ቅዱስም_ጸልዩ።”
— ይሁዳ 1፥20 (አዲሱ መ.ት)
👉በመንፈስ መጸለይ ያለው ጥቅም ከፍተኛ ነዉ። ሐዋርያው ጳውሎስ በልሳን የምንጸልይ ከሆነ #ሚስጥርን እንደምንናገር ይነግረናል።
“በልሳን የሚናገር ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርምና፤ ምስጢር የሆነውን በመንፈስ ስለ ሚናገር የሚረዳው የለም።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥2 (አዲሱ መ.ት)
👉ለመንፈሳዊ ሚስጥራት እራሳችንን እያጋለጥን ነዉ።
👉በልሳን ለሰዓታት ከጸለይኩ በኃላ የማላውቃቸውን ነገሮች በአእሮዬ ውስጥ አግኝቼ አውቃለሁ። የማላውቀውን ቋንቋ ተናግሬ አውቃለሁ። በልሳን መናገር አንዱ መንፈሳዊ አለምን የሚከፍት ቁልፍ ነዉ።
👉ሐዋርያው ጳውሎስ ስለራሱ ስናገር እንደዚህ ነዉ ያለው
“ከሁላችሁ የበለጠ በልሳን ስለምናገር እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥18 (አዲሱ መ.ት)
ጳውሎስ የደረቀ የስነመለኮት ምሁር እንዳይመስልህ "ቀኑን ሙሉ በልሳን ስናገር ውሎ ነዉ የምያድረዉ"!!!
👉የጳውሎስ አንዱ የመንፈሳዊ ስኬት ሚስጥር በልሳን መናገር ነዉ። ምን እንዳለ ተመለከቱ "ከሁላችሁ ይልቅ በልሳን ስለምናገር እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ"!
👉በመንፈሳዊ ሕይወትህ ማደግ ትፈልጋለህ??? እንግዲህ በልሳን ለረጅም ሰአት መጸለይ ተለማመድ።
👉ዛሬ ቀኑን ሙሉ በልሳን ስትጸልይ ዋል ከዛ ልዩነቱን እየው።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
ዛሬ ማታ የምናሰላስለው ጥቅስ:
“እኔ በአባቴ እንዳለሁ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ በዚያን ቀን ታውቃላችሁ።”
— ዮሐንስ 14፥20
Verse to remember:
“At that time you will know that I am in My Father, and you in Me, and I in you.”
— John 14:20 (AMP)
👉ይሄ የኛ ዓለም ነዉ። የኛ አለም እግዚአብሔር ነው። የምንኖረው በእግዚአብሔር ውስጥ ነዉ። ክርስቶስ በእኛ ውስጥ እኛ ደግሞ በክርስቶስ ውስጥ ክርስቶስ ደግሞ በእግዚአብሔር ውስጥ። ምን ያክል ከዓለም የራቃችሁ እንደሆነችሁ ተመልከቱ???? ሃሌሉያ!!!!
የእግዚአብሔር ልጆች ይህንን አሰላስሉ እናንተ በዓለም ካሉት ፈጽሞ የተለያችሁ ናችሁ። መንፈሳዊ ዓለም የእናንተ ዓለም ነዉ።
This is our reality Christ is in Us and we in Christ and Christ in God the Father!!! Don't you see how far greater we are from this world??? Child of God, meditate on this truth, you are not Like those who are out there!! you are different from the world. Your realm is Spiritual!!!
I confess boldly the truth of God! I am hid in Christ!!! Christ is in me!!! I can never be the weakest in my generation!! I am a blessing to Others!!Amen.
የእግዚአብሔርን እውነት አውጃለሁ በክርስቶስ ውስጥ ተሰውሪያለሁ። ክርስቶስ በእኔ ውስጥ ነዉ። መቼም በትውልድ ተራ ሰው አልሆንም። ለሌሎች በረከት ነኝ። አሜን።
#KeysToTheSupernatural
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መንፈስ ቅዱስ (Holy Spirit)
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
👉ብሩክ እና እጅግ ትሁት የሆነው የእግዚአብሔር መንፈስ እግዚአብሔር ነዉ። ብዙ ሰዎች እንደሚመስላቸው እርሱ እሳት ወይም ደግሞ ደመና ፤ ንፋስ ፤ ሃይል ፤ ቅባት ፤ ልሳን ፤ እርግብ ...ወዘተ አይደለም። እነዚህ ሁሉ የተባረከው የእግዚአብሔር መንፈስ መገለጥ ምሳሌዎች(Similitude's of His Holy Presence) ናቸዉ። እርሱ ግን እግዚአብሔር ነዉ። እግዝአብሔርን የሚመስል አይደለም ራሱ እግዚአብሔር ነው።
👉መንፈስ ቅዱስ የተባረከው የስላሴ አንዱ አካል ነዉ። ብዙ ሰዎች እንደሚሉት ሦስተኛው አካል ነዉ ለማለት አልደፍርም። ምክንያቱም በስላሴ የአንድ አምላክ አካላዊ ህብረት ውስጥ ደረጃ አለ ብዬ ስለማላምን። መንፈስ ቅዱስ አንዱ የስላሴ አካል ነዉ።
👉መንፈስ ቅዱስ የሆነ ነገር ሰይሆን "ማን" የምንለው "ማንነት" ያለው በቀላሉ "Person" ነዉ። Person የምንለው ነገር ሁሉ ሦስት ነገሮች ያሉት ነዉ እውቀት(Intellect) ፤ ፈቃድ(Will) እና ስሜት(feelings & emotions) የተባረከው የእግዚአብሔር መንፈስ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ በተደጋጋሚ እንዚህ ሦስት ነገሮች እንዳሉት ተገልጧል።
👉በዚህ Channel አንዱ በጥልቀት ለማወቅ ከእግዚአብሔር ፀጋን የምንለምነው "መንፈስ ቅዱስን" ነዉ።
ከአመታት በፊት በአንድ ወቅት ዮሐንስ ወንጌልን እያጠናሁ
“ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ #ለዘላለምም_ከእናንተ_ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤”
— ዮሐንስ 14፥15-16 ....ይህንን ቃል አገኘሁት ቃሉም እኔን ስላገኘኝ ምን ማለት እንደሆነ ግልጽ ሆና ታየኝ። ለረጅም ሰዓት ነበር ያነበሁት😭 ምክንያቱም ከእኔ ጋር #ለዘለዓለም የሚኖረውን መንፈስ ቅዱስን ለማወቅ ብዙ ትጋት በወቅቱ እያሳየሁ አልነበረም። ከዚሁ ቀን በኃላ ግን ከእኔ ጋር "ለዘለዓለም" የሚኖረው ብቸኛው አካል መንፈስ ቅዱስ ብቻ መሆኑ በጥልቀት ስለገባኝ የዘላለም ጓደኞዬን ለማወቅ እና ለመውደድ ፍጹም ትጋት ማሳየት ጀመርኩ።
👉አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ! መንፈስ ቅዱስ በዝህኛው ሕይወት ብቻ ሰይሆን በሚመጣውም ዓለም ከእናንተ እንደማይለይ ታውቃላችሁ???????
👉መልሳችሁ "አዎን" ከሆነ ይሄንን ትሁት ፤ ታማኝ ፤ ሃይለኛ እና አፍቃሪ ዘላለማዊ ወዳጃችሁን ለማወቅ ምን እያደረጋችሁ ነዉ????????????????????????????????????????????????????????
👉በእግዚአብሔር ፀጋ ስለመንፈስ ቅዱስ እንማራለን። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጥልቅ ነገሮች ሁሉ በስተጀርባ ያለው እርሱ ነዉ።
መንፈስ ቅዱስ እንወድሃለን🙏🙏🙏🙏
👉ፍቅር አንዱ መንፈሳዊ ዓለምን የሚከፍት ቁልፍ ነዉ።
@Voice..
#KeysToTheSupperNatural!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የዛሬ ማታ ጥቅስ:
“ነገር ግን ከጌታ ጋር የሚተባበር ከእርሱ ጋር አንድ መንፈስ ይሆናል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥17 (አዲሱ መ.ት)
Verse to remember:
“But the person who is united to the Lord becomes one spirit with Him.”
— 1Cor 6:17 (AMP)
Can you imagine being One Spirit with the Lord??? ohh what a privilege it's!!!!
We must meditate on this absolute truth of Gods Word!...we are united with the Lord and we have One Spirit with Him!! Glory to his Holy name!
you can see what he sees you can hear what he speaks because you are united with him!
👉Confession: I am one spirit with the Lord!!
ከጌታ ጋር አንድ መንፈስ መሆን እንዴት ያለ መታደል ነዉ???
መንፈሳችን ከጌታ መንፈስ ጋር አንድ እንደሆነ ማሰላሰል የግድ ነዉ። ከጌታ ጋር አንድ መንፈስ ስትሆኑ ጌታ የሚያየውን ማየት የሚናገረውን መስማት ትችላላችሁ። ክብር ለእግዚአብሔር ይሁን።
የእግዚአብሔር ልብ ማወቅ እንዴት መታደል ነዉ??? እግዚአብሔር ለሚያምኑ ሁሉ የሰጠው በረከት ብዙ ነዉ።
➤ይህንን ደጋግማችሁ አውጁ ለራሳችሁ።
👉ከጌታ ጋር አንድ መንፈስ ነኝ!!! አሜን!!
#KeysToTheSuppernatural
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
የዛሬ ማታ ጥቅስ
“ለእነርሱም እግዚአብሔር በአሕዛብ ዘንድ ያለው የዚህ ምሥጢር ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደ ሆነ ሊያስታውቅ ወደደ፥ ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ ነው።”
— ቆላስይስ 1፥27
Verse to remember
“To whom God was pleased to make known how great for the Gentiles are the riches of the glory of this mystery, which is Christ within and among you, the Hope of glory.”
— Col 1:27 (AMP)
➤ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ የክብር ተሰፋ ነዉ። ይሄንን አሰቡ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
➤May the Lord help Us to realize the Brevity of Time and may we invest all we have in the kingdom of God!🙏
➤Until You realize the brevity of Time you will not be an influential servant of God! When you know the power of Understanding time, everything about you changes, your values and interests change!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“ቀን ሳለ፣ የላከኝን ሥራ መሥራት አለብን፤ ማንም ሊሠራ የማይችልበት ሌሊት ይመጣል፤”
— ዮሐንስ 9፥4 (አዲሱ መ.ት)
➤ብዙዎቻችን እግዚአብሔር ብዙ ገንዘብ ብሰጠኝ እንድህ እና እንድያ አደርጋለሁ ፤ በዝህ ነገር ለይ አውላለሁ(Invest) አደርጋለሁ እንላለን። ነገር ግን እግዚአብሔር ከገንዘብ ቀድሞ የሰጠን ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ጊዜ(Time) ፤ ጉልበት (energy) ...ወዘተ ...ስለዚህ ገንዘብ invest ስለማድረግ ከማውራታችን በፊት እራሳችንን መጠየቅ ያለብን ነገሮች አሉ። ጊዜዬን ፤ ጉልበቴን ትክክለኛ በሆነ ነገር ለይ ነዉ እያዋልኩ ያለሁት???
ምክንያቱም እግዚአብሔር ቀድሞ በሰጠን ነገር ለይ ተማኞች ከሆንን ብቻ ነዉ በሌሎች ነገሮች ለይ የሚሾመን።
ያላችሁን ነገር invest ከማድረግ ጀምሩ። ጊዜያችንን ትክክለኛ ነገር ለይ invest እናድርግ። የጊዜን ትልቅነት እስካልተረዳችሁ ድረስ በመንፈሳዊ ህይወታችሁ ለውጥ(Progress) ማሳያት አስቸጋሪ ነዉ የምሆነው።
““እግዚአብሔር ሆይ፤ የሕይወቴን ፍጻሜ፣ የዘመኔንም ቍጥር አስታውቀኝ፤ አላፊ ጠፊ መሆኑንም ልረዳ።”
— መዝሙር 39፥4 (አዲሱ መ.ት)
➤ጊዜ ውስን ዘመናችሁም በእግዚአብሔር ተቆጥሮ የተወሰነ እንደሆነ ስትረዱ ለጊዜ ያላችሁ አመለካከት በጣም የላቀ ይሆናል። መቼ ምን ለይ ጊዜዬን ማዋል አለብኝ የምለው ሁሉ በጥንቃቄ የሚደረግ ይሆናል። የእናንተ ባልሆነ ነገር ለይ ከማባከን ነጻ ወጥታችሁ በትክክለኛው ነገር ለይ ውላችሁ ማደር ትጀምራላችሁ።
ዓለማችንን በአንድም በሌላም መንገድ የለወጡ እየለወጡም ያሉ ሰዎች ሁሉ ጊዜን በትክክል የተረዱ እና የተጠቀሙ ሰዎች ናቸው።
➤በመመኘት ብቻ የምሆን ነገር የለም ፤ በትክክለኛ የጊዜ investment ግን ከትውልድ ፊት ለይ እንባን ማበስ እንችላለን።
➤አልፎ እንዳይቆጨን አሁኑኑ እንጀምር ። ጊዜን በትክክለኛው ነገር ለይ እናውል።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Verse to remember:
“I am crucified with Christ: nevertheless I live; yet not I, but Christ liveth in me: and the life which I now live in the flesh I live by the faith of the Son of God, who loved me, and gave himself for me.”
— Galatians 2:20 (KJV)
የዛሬ ማታ ጥቅስ:
“ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።”
— ገላትያ 2፥20
➤በእናንተ የምኖረውን ክርስቶስ ፍጥረት ሁሉ የሚያይበት ዘመን ይሁን።🙏 አሜን።
Join 👇👇👇👇
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Be Uplifted by this blessed song!. HOLY SPIRIT🙏 blessed person !! #welcome Holy Spirit !!🙏😥🙏😥🙏 #ተባረኩ።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
“መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር በመንፈሱ በኩል ገለጠው።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥10
➤መንፈስ ቅዱስ እዚህ ያለው ለኛ ጥቅም ነዉ። አንድ ማስተዋል ያለብን ነገር ጌታችን ኢየሱስ ወደ ምድር ስመጣ ክብሩን ዙፋኑን ሁሉ ትቶ አብን ታዞ እንደመጣ ሁሉ መንፈስ ቅዱስም እንደዚያው ነዉ ያደረገው።
➤መንፈስ ቅዱስ ሰማይን ትቶ ወደ ምድር የወረዳው እግዚአብሔር ወልድን ታዞ ለክርስቶስ አካል ጥቅም ነዉ። ይህ ትሁት መንፈስ ራሱን ሰይሆን ኢየሱስን እና የክርስቶስን አካል ማክበር አንዱ ስራው ነዉ። ይህንንም ስራውን የምሰራው #እግዚአብሔር_ምስጥር_አድርጎ_የሰወረውን_ጥልቅ የእግዚአብሔር #ምስጥር ለእኛ በመግለጥ ነዉ።
መንፈስ ቅዱስን ከሰማችሁት ሁልጊዜ እሱ እነዚህን ጥልቅ ምስጥራት በመግለጥ ለይ ነዉ። የክርስቶስም አካል ወደ ተዘጋጀላት ከፍታ ልያወጣት የምችለው መንፈስ ቅዱስ በዚሁ የእግዚአብሔርን ምስጥራት በመግለጥ ስራው ነዉ።
“ነገር ግን #እግዚአብሔር_አስቀድሞ_ከዘመናት_በፊት_ለክብራችን_የወሰነውን፥ ተሰውሮም የነበረውን የእግዚአብሔርን ጥበብ በምሥጢር እንናገራለን።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥7
➤“But rather what we are setting forth is a wisdom of God once hidden and now revealed to us by God-- which God devised and decreed before the ages for our glorification .”
— 1Cor 2:7 (AMP-
#God devised and decreed before the ages for our glorification!
➤ከዝህ በኃላ በምኖረን ቆይታ ለእኛ ለክብራችን የተዘጋጁ ምስጥራትን በተከታታይ የምናይ ይሆናል። መንፈሳዊ ዓለምን የሚያስተዳድሩ መንፈሳዊ ምስጥራትን እናያለን።
➤በዝህ በዘመን መጨረሻ እግዚአብሔር ክብሩን ለዓለም ሁሉ የምገልጥብን ቅሬቶች ነን።
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
Shalom Everyone greetings in the Name of Our Lord Jesus Christ!
We are here by the instruction of The Spirit, to help You to get deeper in to things of the Spirit!
We will be giving you Spiritual principles that govern the Spiritual realm! get ready to move in the Spiritual realm! I personally believe it's going to transform you and prepare you for the coming move of God(Revival)!
If there is someone, that you love, please help them to join this channel by sharing the links of Our channel, so that they may also Learn the deep things of The spirit!
The Bible say “But God hath revealed them unto us by his Spirit: for the Spirit searcheth all things, yea, @the_deep_things_of_God.”
— 1 Corinthians 2:10 (KJV)
All we do is this by the Power of the Holy Spirit and by his Grace in our life we will be revealing those #Secrets of God!
➤Remember we are in a very serious PROPHETIC season!
➤Mystery's that Govern the Prophetic will be exposed to you very Soon!....and you will see in the Spirit!.
Get ready for greater levels and greater Manifestations!!!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
@TheDeepThingsOfTheSpirit
1 810
መንፈሳዊ እድገት የሙሉ ጊዜ ስራ ነዉ። ክርስቲያን ነን የምንል ከሆነ ይሄንን ማሰብ ይኖርብናል።
በመንፈሳዊ ህይወትህ እንድታድግ ምን እያደረግህ ነዉ ? ምን እያደረግሽ ነዉ??
Spiritual Growth is a full time Job! If you think you are a Christian you must grow spiritually!!
➤It is a full time Calling! you are called to be like Christ!
➤Remember being born again is just the beginning of The Journey! don't think you are done it all!
@TheDeepThingsOfTheSpirit
