en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ኤፌሶን 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ¹⁸-¹⁹ ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ 👉ይህ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የክርስቶስ አካል አባላት ለሆኑ ሁሉ የጸለየው ጸሎት ነዉ። ይሄ ማለት ጸሎቱ እኛንም ያቅፈናል ማለት ነዉ። በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በዚህ እውነት እንመላለሳለን! የክብር አባት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባት የሆነውን እግዚአብሔርን በማወቅ #የጥበብና #የመገለጥ መንፈስ ይበዛልናል! ይህም ደግሞ #የልብ_አይኖቻችን መብራት ነዉ! የልብ አይኖቻችን ስበሩ: 1-እግዚአብሔር ስጠራን ለምንስ አይነት ተስፋጰእንደጠራን እናውቃለን። 2-በቅዱሳን(በክርስቶስ ባመንን በእኛ) ውስጥ ያለውን ክብር ምን ያህል እንደሆነ እናውቃለን። 3- ለምናምን በሰማይም ሆነ በምድር እስከ ዛሬ ከተለቀቁ ሃይላት ሁሉ የሚበልጠውን: ኢየሱስን ከሙታን ስያስነሳው እግዚአብሔር ያደረገውን ሃይል እናውቃለን። በማወቅ ደግሞ በብርሃን እንመላለሰለን! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዛሬ በሐዋሳ አጅፕ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ከወጣቶች ጋር በነበረኝ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ፍጹም የሆነውን የእግዚአብሔር እውነት እና ሃይል አሳይቶናል! መንፈስ ቅዱስ ከሰጠን ድምጾች አንዱን ልንገራችሁ:- 👉ክርስቶስ የሚመጣላት ቤተክርስቲያን: “እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።” — ኤፌሶን 5፥27 ኢየሱስ ክርስቶስ ሚስቱ የምትሆን ቤተክርስቲያንን ለራሱ ልወስድ ይመጣል: ይህ ጥያቄ የለውም። ነገር ግን ይህች ኢየሱስ ለራሱ የሚወስዳት ቤተክርስቲያን ምን ትመስላለች? አሁን በሰፊው እንደሚታየው በቀጥታም በተዘዋዋሪም የዓለም የኃጢአት እና የሰይጣንም ተጠቂ የሆነችን ቤተክርስቲያን ለመውሰድ ነዉ የሚመጣው??? አይደለም! ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የሚነግሩን: ኢየሱስ የሚመጣው #ያለ_ነውር ለሆነች #ቅድስት ለሆነች #በክብር_ለተሞላች ቤተክርስቲያን ነዉ! ይህንን ማድረግ እንድንችል ደግሞ የሚያስፈልገን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተሰጥቶናል! መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ቃል: እግዚአብሔር ለመምሰል የሚያስፈልገን ነገር ሁሉ እንደተሰጠን ይነግረናል!.....“የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥2-3 ተወዳጆች ሆይ አስተውሉ: የሙሽሪት ክብር እንደ ሙሽራው መሆን አለበት! ሙሽሪት(ቤተክርስቲያን) ሙሽራው(ኢየሱስ) ባቀረበላት በረከት ሁሉ ራሷን የማዘጋጀት ኃላፊነት አለባት!!!! Join our channel 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መንፈስ ቅዱስ ------------------- 👉መንፈስ ቅዱስ ሃይል⚡️ አይደለም! 👉መንፈስ ቅዱስ እርግብ 🕊 አይደለም! 👉መንፈስ ቅዱስ እሳት🔥 አይደለም! 👉መንፈስ ቅዱስ ደመና🌫 አይደለም! 👉መንፈስ ልሳን🗣 አይደለም! ************************* መንፈስ ቅዱስ #እግዚአብሔር_ነዉ! አምልኮ የሚገባው እግዚአብሔር ነዉ! መንፈስ ቅዱስ ልክ እንደ እግዚአብሔር ወልድ እና እንደ እግዚአብሔር አብ እውቀት ስሜት እና ፈቃድ ያለው ነዉ! መንፈስ ቅዱስ በክርስቲያን ሕይወት የእግዚአብሔር አብና የእግዚአብሔር ወልድ ሕልውና ነዉ! ብዙ ሰዎች መንፈስ ቅዱስን እነሱ እንደፈለጉ የሚያንቀሳቅሱትና የሚጠቀሙት ሃይል አድረገው ያስባሉ። ይህ በጣም የተሳሳተ አካሄድ ነዉ! መንፈስ ቅዱስ ይጠቅመናል እንጂ አንጠቀመውም! ያንቀሳቅሰናል እንጅ አነንቀሳቅሰውም! መንፈስ ቅዱስን እንደ እግዚአብሔር ማወቅ እና መቅረብ ስትጀምሩ ያኔ በኢየሱስ የነበረውን ሃሳብ በእናንተ ታዩታላችሁ! #የእግዚአብሔር_መንፈስ_እግዚአብሔር_ነዉ! Join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አጥቦ ሊያነጻን፣ ልያረሰርሰን እና ፍሬ እንድናፈራ ሊያደርገን የሚችለው የመንፈስ ቅዱስ ዝናብ ብቻ ነዉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በ 1947 የእግዚአብሔር ጀነራል Smith Wigglesworth ስለ መጨረሻው ዘመን ሪቫይቫል እግዚአብሔር አሳይቶት የተናገረው ትንቢት:- በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ሪቫይቫል ወደ ምድር ስመጣ አያለሁ። የማይቆጠሩ ብዙዎች ይድናሉ: ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚመጡትን ማንም መቁጠር አይችልም። በዚህ ሪቫይቫል ጊዜ የትኛውም አይነት በሽታ በእግዚአብሔር ሕዝብ ፊት መቆም አይችልም። ሆስፒታሎች ሁሉ ባዶ ስሆኑ አያለሁ! ዶክተሮች ሁሉ እየጮኹ መንገድ ለይ ሲሮጡ እያየሁ ነዉ። ሪቫይቫሉ ዓለም አቀፋዊ ነዉ የሚሆነዉ: የአንድ አጥቢያ አይደለም። በዓለም ዙሪያ ሁሉ የእግዚአብሔር ሃይልና ቅባት በሰዎች ለይ ይወርዳል። -Smith Wigglesworth ነቢዩ ኢዩኤል የተናገረው ትንቢት ሐዋሪያቱ እንዳስፈጸሙት: በጌታ ኢየሱስ ስም የህ ትንቢት በዚህ ትውልድ መካከል በአንተና በአንቺ ይፈጸማል!!! ራሱን የሚሰዋ አንድ ሰው የዚህ ሪቫይቫል አስጀማሪ ይሆናል! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

መዝሙር 23 ሙሉ ምዕራፉን በጥልቀት አሰላስሉ: ከዛም ድምጻችሁን እየሰማችሁ አውጁ! የእግዚአብሔር ቃል እውነት ነዉ! በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በሕይወታችሁ ተገልጦ ታዩታላችሁ!!!!

#የዳዊት_መዝሙር_የክርስትያን_የኑሮ_ስርዓት! #The_song_of_David_The_reality_of_a_Christian! መዝሙር 23 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። ² በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። ³ ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። ⁴ በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል። ⁵ በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፤ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። ⁶ ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የዚህ ቻናል አባላት የምንለጥፋቸውን መልእክቶች ወደሌሎች ጉሩፖች በማጋራት: ሌሎችን ወደዚህ ቻናል እንድቀላቀሉ እኔድታደርጉ #በጌታ_ፍቅር_አሳስባችኋለሁ! መልእክቶቹ የሚያንጹት አባል ወደሌሎች የማጋራት ሃላፊነት አለበት! ተባረኩ!!😍

𝙡𝙞𝙫𝙚 𝙖𝙣 𝙖𝙘𝙩𝙞𝙫𝙚 𝙘𝙝𝙧𝙞𝙨𝙩𝙞𝙖𝙣 𝙡𝙞𝙛𝙚 -------------------------------------------- 👉𝙘𝙝𝙧𝙞𝙨𝙩𝙞𝙖𝙣𝙞𝙩𝙮 is a life of the SUPERNATURAL!🔥 👉It is the religion of the DIVINE!🔥 👉Christianity is a PERSONAL spiritual relationship with CHRIST!🔥 👉#Be_Conscious_Of_This_Truth!🔥 👉Meditate on it DAY and NIGHT!🔥 #Voice 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የነቃ የክርስትያን ሕይወት እንኑር ------------------------------------------ 👉ክርስትና ልዕለ-ተፈጥሮአዊ የሕይወት አይነት ነዉ!🔥 👉ክርስትና የመለኮት ኃይማኖት ነዉ!🔥 👉ክርስትና ከክርስቶስ ጋር የሚደረግ ግላዊ የሆነ መንፈሳዊ ሕብረት ነዉ!🔥 👉ይህ እውነት የንቃተ ሕልናችሁ ክፍል ይሁን!🔥 👉በቀንም በሌሊትም ይህንን እውነት አሰላስሉ!🔥 ቻናሉን ለመቀላቀል 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Jesus you have the greatest name of all!😍 #Be_blessed join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉የሕይወት ማሳ “እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።” — ማቴዎስ 4፥4 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድረበዳ ከዲያብሎስ ለ
👉የሕይወት ማሳ “እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።” — ማቴዎስ 4፥4 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድረበዳ ከዲያብሎስ ለቀረበለት ጥያቄ የመለሰው መልስ ነዉ: ጥያቄው "#ለምን_ትጾማለህ? ለምን እንደዚህ ትጠወልጋለህ? ትርፍ የለውም: እንደዚህ በረሃብ ከምትጠወልግ: ይህንን ድንጋይ እንጀራ እንድሆን እዘዝ ከዛም በመብላት እና የስጋህን ምኞት በማርካት ጉዞህን በአጭሩ ቅጨው" የምል መንፈስ ያለው ጥያቄ ነበር: የተባረከው የእምነታችን ሐዋርያ ግን እንደ ፊተኛው "አዳም" በሰይጣን ተንኮል በስጋ ምኞት ተታሎ አልወደቀም! #ሰው_የሚኖርበትን_ምስጢር_በሚገባ_ተርድቶታል! ሰው #እንጀራ በመመገብና ስጋውን በማወፈር ብቻ #በሕይወት እንደማይኖር በግልጽ አስረድቷል! #ከእግዚአብሔር_አፍ_የሚወጣ_ቃል የግዴታ የሰው የአመጋገብ ስርዓት ውስጥ መካተት አለበት!!! ይህ የማይሆን ከሆነ እና ሰው በእንጀራ ብቻ የሚኖር የሚመሰለው ከሆነ ራሱን እያሳተ ነዉ!!!! የእግዚአብሔር ቃል ሕይወት የሚገኝበት ማሳ ነዉ!!!! #የእግዚአብሔርን_ቃል_ያዙ_ሕይወታችሁ_ነውና!! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የዚህ ቻናል አባላት የሆናችሁ እና ከዚህ በኃላም የምትቀላቀሉን: በዚህ መገኘታችሁን ትልቅ ዋጋ የምንሰጠው መሆኑን ማሳወቅ እፈልጋለሁ! አምናለሁ አብረን የምናሳልፈው ጊዜ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን እውነት እና ሃይል የሚገልጥልን: እግዚአብሔርን ለመምሰል ፍጹም የሚለውጠን ጊዜ ነዉ! ሁላችንም እወዳችኋለሁ! @TheDeepThingsOfTheSpirit

sticker.webp0.26 KB

ይህች የምትመለከቷት ብራብሮ ከዚህ በፊት ትል ነበር የምትመስለው: በጣም አስጠሊታም ነበረች ቢባል ማን ያምናል? ምን አልባት የቢራቢሮን ተፈጥሮአዊ የለውጥ ጉዞ የሚያውቅ ሰው ከሆናችሁ "አዎ እንደዚህ
ይህች የምትመለከቷት ብራብሮ ከዚህ በፊት ትል ነበር የምትመስለው: በጣም አስጠሊታም ነበረች ቢባል ማን ያምናል? ምን አልባት የቢራቢሮን ተፈጥሮአዊ የለውጥ ጉዞ የሚያውቅ ሰው ከሆናችሁ "አዎ እንደዚህ ከመሆኗ በፊት ትል ትመስል ነበር" ትላላችሁ። ነገር ግን ይህ የቢራቢሮን ተፈጥሮአዊ የለውጥ ጉዞ ለማያውቅ ሰው "ለማመን የሚከብድ ተዓምራት ነዉ የሚሆንበት!"። እውነታው ግን አዎ ይህቺ ቢራቢሮ እንደዚህ አይነት ድንቅ ፍጥረት ከመሆኗ በፊት ትል ነበር የምትመስለው: ውስጧ የለውን ዘር እና የመለወጥ አቅም: በነጻ ፈቃዷ መራራ ቅጠል በመብላት ስትደግፈው: በአንድ ጀንበር ባይሆንም በጊዜ ሂደት ይህንን መሆን ችላለች! አስተውሉ የቢራቢሮ ለውጥ #በአንድ_ጀንበር_የመጣ_ተዓምራት_አይደለም! ነገር ግን በጊዜ ሂደት እልህን በሚፈታተን ጉዞ የመጣ ለውጥ ነዉ! በዳግም ልደት ከእግዚአብሔር በመወለድ የእግዚአብሔር ዘር በእናንተ ያላችሁ ተወዳጆች: አሁን ዛሬ ለይ ባላችሁበት ሁኔታ ምን አልባት ኢየሱስን የሚመስል አንድም ነገር በራሳችሁ ለይ እያያችሁ አይደለም ይሆናል: ነገር ግን እመኑኝ ውስጣችሁ ያ ዘር ተደብቆ አለ! ለአሮጌው ሰዋችሁ መራራ የሚመስለውን ነገር ግን ክብር የሞላበትን የክርስትና መንገድ በእምነት በፍቅር እና በተስፋ ለመሄድ ዛሬ መወሰን የምትችሉ ከሆነ: "እርሱን ራሱን እስክትመስሉ ደረስ የመለወጥ አቅም በእናንተ እንዳለ ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ!" ቅዱሳት መጽሐፍት ይህንን በአጭሩ እንደዚህ በማለት ይጠቀልሉታል ----“እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።”— 2ኛ ቆሮ 3፥18! አሜን!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#የእግዚአብሔር_ቃል አውቃለሁ ብዙ ጊዜ ጸልያችኋል: በጸሎት ክፍላችሁ ወይም የቤተክርስቲያን መሰብሰብያ ውስጥ አምርራችሁ አልቅሳችሁ ታውቃላችሁ: ነገር ግን የፈለጋችሁትን ውጤት ማግኘት አልቻላችሁም!
#የእግዚአብሔር_ቃል አውቃለሁ ብዙ ጊዜ ጸልያችኋል: በጸሎት ክፍላችሁ ወይም የቤተክርስቲያን መሰብሰብያ ውስጥ አምርራችሁ አልቅሳችሁ ታውቃላችሁ: ነገር ግን የፈለጋችሁትን ውጤት ማግኘት አልቻላችሁም! ለምን ? “በእኔ ብትኖሩ #ቃሎቼም_በእናንተ_ቢኖሩ_የምትወዱትን_ሁሉ_ለምኑ_ይሆንላችሁማል።” — ዮሐንስ 15፥7 የእግዚአብሔር ቃል አለህ? የእግዚአብሔር ቃል አለሽ? በልባችሁ የእግዚአብሔር ቃል አላችሁ? ጸሎት እውነት ነዉ ትልቅ መንፈሳዊ መሳሪያ ነዉ! ነገር ግን እንዴት ነው የምንጸልየው? እንዴት ነዉ ይህንን መሳሪያ የምንጠቀመው???? ብዙ ሰዎች ጸሎቴ አልተመለሰም ይላሉ: ለዚህም እግዚአብሔርን ተጠያቂ ያደርጋሉ: ነገር ግን እነሱ የሚጸልዩበትን መንገድ በእግዚአብሔር ቃል አይፈትሹም። የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ከሌላ ጸሎታችሁ አብዛኛውን ጊዜ የተፈለገውን ውጤት ይዞ አይመለስም!!!! ኢየሱስን እንስማው: የራሳችንን ስሜት ወይም ሰዎች አይደለም ኢየሱስን ራሱን እንስማው: "#ቃሎቼም_በእናንተ_ቢኖሩ_የምትወዱትን_ሁሉ_ለምኑ_ይሆንላችሁማል።” አለ! ይሄ ግልጽ ነዉ! አንድን ሰው ለጸሎት የሚያበቃው #በውስጡ_ያለ_የኢየሱስ_ቃል_ነዉ!!! የእግዚአብሔር ቃል የሌለው ሰው ጸሎትን በትክክለኛው መንገድ ማድረግ በፍጹም አይችልም! ለዚህም ጸሎቱ መልስ አይኖረውም። የእግዚአብሔርን ቃል እንውደድ!!!!! የእግዚአብሔር ቃል በመንፈሳችን ካለን የጠየቅነውን ሁሉ ይሰጠናል!!!!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ትዝታዬ ቃልህ ይሁን -ቤተልሔም😍 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“የሰማያት ሰማይ ለእግዚአብሔር ነው፤ ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።” — መዝሙር 115፥16

#ፈቃድህ_በሰማይ_እንደሆነች_እንዲሁ_በምድር_ትሁን_ብለን_የምንጸልይበት_ምክንያት: 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የለእግዚአብሔር ሰው ማድረግ አይችልም የለሰው እግዚአብሔር ማድረግ አይፈልግም! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ይሄንን በየቀኑ የምታሰላስሉት እና ለራሳችሁና ለአከባቢያችሁ የምታውጁ ከሆነ ሕይወታችሁ #ወደፊት_እና_ወደላይ ብቻ ነዉ የሚሆነዉ!!🔥

የምናሰላስለው ጥቅስ👉“ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።” — 1ኛ ዮሐንስ 4፥4 #ማስታወሻ👉ክርስቲያን ከዓለም በታች የሆነ የሰይጣን ተጠቂና በውድቀት መንፈስ የሚያለቅስ ደካማ አይደለም የምንለው: እውነት ነዉ። ታድያ ክርስቲያኖች ለምንድነው አሁን ባሉበት ሁኔታ ያሉት ካላችሁኝ: መንፈስ ቅዱስ ከመንፈሴ ጋር ሆኖ የሚሰጠኝ አጭር መልስ "አለማወቅ" (𝙞𝙜𝙣𝙤𝙧𝙖𝙣𝙘𝙚) የሚል ነዉ!!!! ተወዳጆች ሆይ የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ #በማወቅ በትክክለኛው ማንነታችን በዓለም ለይ የምንመላለስበት ጊዜ ነዉ!!! 👉#ድምጼን_አሰምቼ_ይህንን_አውጃለሁ! የእግዚአብሔር ቃል እንደገለጠልኝ: የተገኘሁት ከእግዚአብሔር ነዉ! #አሸናፊ _ነኝ: በፍጹም የሰይጣን የኃጢአት እና የዓለም ተጠቂ አይደለሁም! በዓለም ካለው በእኔ ያለው ይበልጣል🔥!!!! በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሄ የሕይወት ስርዓቴ ነዉ! አሜን። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit