en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
“ራእይ በሌለበት ሕዝብ መረን ይሆናል፤...” — ምሳሌ 29፥18 ስለ ራዕይ ስናስብ ወድያው ነገ ለይ ልንሰራው ስላለው ነገር ማሰብ የተለመደ ነዉ! ነገር ግን ልንሰራው ስላለው ነገር የእውነት እውቀት እንድኖረን ቀድሞ ስለራሳችን የጠራ እውቀት ሊኖረን የገባል! ራዕይ አለህ/ሽ? በክርስቶስ ስላለው ሕይወትህ/ሽ የጠራ እውቀት አለህ/ሽ? ለዚህ ጥያቄ መልስ ከሌለህ/ሽ ተኝቶ ለማደር አትውደድ/ አትውደጂ! ከእግዚአብሔር መልስ እስክታገኙ ፈልጉ! ምክንያቱም መረን መሆን አትፈልጉምና! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በጌታ በኢየሱስ ስም አውጃለሁ በእውቀት እና በሕይወት ኢየሱስ ክርስቶስን የሚመስለው አንድ ሰው ይነሳል! መራራ ለሆነው ዓለም ጨዉ ለጨለመበት ትውልድ ብርሃን ይሆናል! ያ ሰዉ አንተ ከሆንክ አንቺ ከሆንሽ የእግዚአብሔርን እውነት በመመገብ እና በመንፈስ ቅዱስ በመቀጣጠል ተዘጋጅ/ ተዘጋጂ! እግዚአብሔር በትክክለኛው ጊዜ በሰማያት ለይ እንዳሉ ብርሃናት የማይሰወር ምልክት ያደርግሃል/ያደርግሻል! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ክርስትና በዳግም ልደት ፍጹም ለውጥን ለመለማመድ የጀመርነው ፍጹም እውነተኛ የሕይወት መንገድ ነዉ። ክርስትና ስዖል ከሚባል ቦታ ለማምለጥ ብቻ ሮጠን የተጠለልንበት ድንኳን የሚመስላቸው ክርስትያኖች አያሌ ናቸዉ! ይህ አስተሳሰብ ከመንፈስ ቅዱስ የተማሩት ወይም ከቅዱሳት መጽሐፍት የተረዱት አይደለም! ያሉበት ተቋም ያስተማራቸው እንጂ። ክርስትና በዳግም ልደት የጀመርነው ፍጹም እውነተኛ መንገድ ስሆን ግቡም የእውነትን እውቀት በማግኘት እግዚአብሔርን ራሱን መምሰል ነዉ! ቢያምም እውነቱ ይህ ነዉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በዚህ ቀን ትዝታችን እግዚአብሔር ይሁን! ተባረኩ!😍

መጽሐፍ ቅዱሳችሁን በፍጹም ሌሎች ጽሑፎችን እንደምታነቡ አታንብቡ! መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ያለባችሁ በጸሎት ፣ በዝግታ ፣ በተደጋጋሚ እና በቀጣይነት ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

እግዚአብሔር አባቴ ነዉ ስል እያልኩ ያለሁት:- ➤እግዚአብሔር ምንጬ ነዉ! ➤የተገኘሁት ከእግዚአብሔር ነዉ! ➤የወጣሁት ከእግዚአብሔር ነዉ! ➤የሃይሌ ምንጭ እግዚአብሔር ነዉ! ➤የእውቀቴ ምንጭ እግዚአብሔር ነዉ! ➤የሕይወቴ ምንጭ እግዚአብሔር ነዉ! ➤ከእግዚአብሔር ውጭ ሕልውና የለኝም! “በእርሱ ይህን ተስፋ የሚያደርግ ሁሉ፣ እርሱ ንጹሕ እንደሆነ ራሱን ያነጻል።” — 1ኛ ዮሐንስ 3፥3 (አዲሱ መ.ት) @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናታችሁ ሁልጊዜ ከቀድሞም ውስጣችሁ የነበረን እውቀት ለማጠንከር ከሆነ የኃይማኖት መንፈስ እያጠቃችሁ ነዉ ማለት ነዉ! መጽሐፍ ቅዱስ ስታጠኑ እግዚአብሔር በዛ ጊዜ ለዛ ትውልድ የተናገረውን ሃሳብ ማወቅ የመጀመሪያው ነገር ስሆን በዛ ቃል ውስጥ ግን እግዚአብሔር ለዛሬ ምን እየተናገረ ነዉ የሚለውን ማግኘት የእውነተኛ መንፈሳዊነት ምልክት ነዉ። እግዚአብሔር ትናንት የተናገረ አምላክ ብቻ ሰይሆን ዛሬም የሚናገርለት አምላክ ነዉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ከእግዚአብሔር የመወለድህን እውነት በጥልቀት ስታውቅ ፍጹም ለዉጥን መለማመድ የሕይወት ስርዓት እንጅ ትግል አይሆንም! @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ስለዚህ ጉዳይ የምንናገረው ብዙ ነገር አለን፤ ነገር ግን ለመማር ዳተኛ ስለ ሆናችሁ ለማስረዳት አስቸጋሪ ነው።” — ዕብራውያን 5፥11 ለመማር የተዘጋጀ መንፈስ የመጀመሪያው የለውጥ ሃይል ነዉ! አንዳንድ ሰዎች የማይነግሯችሁ የሚናገር አንደበት ስለሌላቸው አይደለም ነገር ግን የሚሰማ ጆሮ ስለሌላችሁ ነዉ። ሁሌ ማለዳ ስትነሱ በነፍሳችሁ የእግዚአብሔርን እውነት እና መንገድ ለማወቅ የተዘጋጀ ባዶ ክፍል መኖሩን እርግጠኛ ሁኑ! የሚማር መንፈስ ከሌላችሁ የሚለወጥ ህይወት አይኖራችሁም! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ፍጹም ለውጥ (🦋Transfiguration🦋) ለምን? የእግዚአብሔር ልጆች ፍጹም ለውጥን ለመለማመድ የጀመርነው መንገድ በለውጣችን ዓለማችንን ለማስገረም ብቻ አይደለም። የፍጹም ለውጥ ዋና ግብ በዝህ ሕይወት መግዛት ነዉ! ከትንንሾቹ ጀርሞች እስከ ትልልቆቹ ፍጥረታት ድረስ መግዛት ነዉ! “በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ።” — ሮሜ 5፥17 #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የለ እውቀት የሚደረግ የትኛውም ነገር ይህ ነዉ የሚባል ተጽዕኖ መፍጠር አይችልም። የእግዚአብሔር መንግስት በብርሃን(በእውቀት) የምንገዛበትን መንግስት ነዉ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን። ስለዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን ስላላወቀው እኛን አያውቀንም።” — 1ኛ ዮሐንስ 3፥1 የእግዚአብሔር ልጅ የመሆናችንን እውነት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በዘመኑ ለነበሩ ሰዎች ለማወቅ የሚያስቸግር ሚስጢር አድርጎ ነዉ የገለጸው! አሁን አሁን የእግዚአብሔር ልጅ የመሆናችን እውነት እንኳን አይደለም በውጭ ላሉት በቤት ላለን ለራሳችንም ሚስጥር የሆነብን ይመስላል። የእግዚአብሔር ልጆች እንደ እግዚአብሔር ልጆች የሚጋለጡበት ጊዜ ሩቅ አይደለም! የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ደግም የተወለድነው ከእግዚአብሔር ነዉ: በዚህ እውነት እግዚአብሔር አባታችን ነዉ። "አባት" ማለት ደግሞ አንደኛ ምንጭ /Source/ ማለት ነዉ። እግዚአብሔር አባቴ ነዉ ስለ እግዚአብሔር የእኔ ምንጭ ነዉ እያልኩ ነዉ ፤ የተገኘሁት ከእግዚአብሔር ነዉ ፤ የወጣሁት ከእግዚአብሔር ነዉ የተቆረጥኩት እና የተቆፈርኩት ከእግዚአብሔር ነዉ ማለቴ ነዉ! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Are you RAPTURE ready!?

ጸሎት (ᴘʀᴀʏᴇʀ) የጌታችንን ደቀመዛሙርት የነበሩት ጌታችን በወጣበት እና በገባበት ሁሉ አብረውት ሆነው ያደረገውን እና ያስተማረውን አይተዋል። የተለያዩ ድውይ ከልባቸው ሰዎች አንስቶ ሙታንን እንኳ ሲያስነሳ ተመልክተዋል። አጋንንት ተገዝተውለታል ፍጥረት ሁሉ እሱ በምፈልገው መንገድ ይመልስለታል የተፈጥሮ ህጎች ያልናቸውን ሰብሮ ትንሹን አብዝቷል ፤ በውሃ ለይ ሁሉ ተራምዷል! ይህንን ሁሉ በቅርበት የተመለከቱ ደቀመዛሙርቱ "ጌታ ሆይ እንዴት የሞተ ማስነሳት እንድንችል አስተምረን?" ወይም "እንዴት በውሃ ለይ እንድንሄድ አስተምረን?" ብለው አልጠየቁትም። ምክንያቱም የነዚህ ሁሉ ልምምዶች ሃይል ከየት እየመጣ እንደሆነ በተወሰነ ደረጃም የተረዱ ይመስላል። መምህራቸው ከፈሪሳውያን ከሰዱቃውያን ወይም ከሙሴ ህግ መምህራን የተለየ የሚያደርገውን ነገር እያስተዋሉ ይመስላል ቀኑ ከመንጋቱ በፊት ብቻውን ወጣ ያለ ቦታ ሄዶ የሚያደርገውን ተመልክተዋል አብዛኛውን ቀን ሌሊት ምን እያደረገ እንደሚያድርም ተመልክተዋል ፤ ከሌላ አካል ጋር ያለማቋረጥ የሚያወራ ይመስላል ይህ ጸሎት የሚባለው መንፈሳዊ ልምምድ እንደሆነ ተረድተዋል ጸሎት ግን ምን እንደሆነ እና እንዴትስ መጸለይ እንዳለባቸው አልገባቸውም ነበር ስለዚህ ወደ መምህራቸው ጠጋ ብለው ሁሉም ልምምዶችህ ከምን እንደምትቀዳቸው አውቀናል ጌታሆይ "እንዴት መጸለይ እንዳለብን አስተምረን" አሉት። ጌታችን ኢየሱስ በየቀኑ በጸሎት ጊዜው ሰማይ የሚያደርገውን ያያል የሚናገረውን ድግሞ ይሰማል ("ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች") ይህንን በሰማይ ያለን የአብ ፈቃድ በምድር ለይ ይከውነዋል! ("እንዲሁ በምድር ትሁን") ጸሎት ይሄ ነዉ! ሰማይ ዛሬ ምንድነዉ እየሰራ ያለው ምንስ ነዉ እየተናገረ ያለው። ይህንን ማወቅ ከቻላችሁ የምያንቀጠቅጥ ወይም የሚያንዘፈዝፍ ሃይል አትጠብቁ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከወቃችሁ ተነስታችሁ አድርጉት አለመሆን አይችልም። #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

🦋Transfiguration🦋 ወይም ፍጹም ለውጥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ለሚያምኑ ሁሉ እንዲለማመዱት የተሰጠ ብሆን ነገር ግን ይሄንን በክብር እጅግ የላቀ አካል ለይ እንኳ ልገለጥ የሚችል መንፈሳዊ ልምምድ የምለማመዱ በከፍተኛ የአእምሮ ዝግጁነት እና መንፈሳዊ ውሳኔ መራራውን መንገድ ለመጓዝ እና ረጅሙን ተራራ ለመውጣት የተዘጋጁ ክርስትያኖች ብቻ ናቸው። እውነታው ይሄ ነዉ! #Spiritstyle @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እግዚአብሔርም፦ ብርሃን ይሁን አለ፤ ብርሃንም ሆነ።” — ዘፍጥረት 1፥3 በሕይወታችሁ ብርሃን ይሁን! በልባችሁ ብርሃን ይብራ ሕይወታችሁ ደስ ያሰኛችሁ!!! @TheDeepThingsOfTheSpirit

እናቶቻችን ስወልዱን ምድር ወደሚባል ዓለም እና አካላዊ ስፍራ ነዉ ያስገቡን። በኢየሱስ ክርስቶስ ስናምን እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ እና በቃሉ ደግም ስወልደን ደግሞ የሰማይ መንግስት ወደሚባል መንፈሳዊ ስፍራ ነዉ ያስገባን። ይህ መንፈሳዊ ስፍራ ልንይዘው፣ ልናየው እና ልንዳስሰው የምንችለው እውነትም ነዉ! ነገር ግን በዚህኛው አካላዊ ዓለም ለይ መስራት(Function) ማድረግ የቻልነው ሀ ለ ሐ መ ...እያልን ነገሮችን በህደት በመማር እና በመሰልጠን እንደሆነ ሁሉ ደግም በተወለድንበት ሰማያዊ መንግስትም ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ እውነቶች ጀምሮ ጥልቅ እስከሆኑት መንፈሳዊ ሚስጥራት አንድ በአንድ በመማር እና በመሰልጠን መስራት(Function) ማድረግ እንችላለን! ሐዋርያው ጳውሎስ “እንዲሁ ሰው እኛን እንደ ክርስቶስ ሎሌዎችና እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቍጠረን።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 4፥1...እንዳለ እነዚህን የመንግስት ምስጢራት በውስጣቸው የሰነቁ ጥቅት ሰዎች አሉ! እነዚህን ሰዎች የሚሰሙ ጆሮዎች ካሉን: በዚህ መንግስት ሥር ሆኖ የማይቻል ነገር የለም! እያንዳንዱ መንግስት የሚሰራበት የራሱ ሕግ እና ስርዓት አለው እያንዳንዱ የመንግስቱ ዜጋ ደግሞ እነዚህን ሕጎች እና ስርዓቶች በማወቅ በእነሱ ስመላለስ የመንግስቱ ንቁ ዜጋ ነዉ ማለት ነዉ: ይህ ንቃት በመንግስቱ ውስጥ የሚኖረውን ቦታ ይወስናል! የእግዚአብሔር መንግስት ጥልቅ ሚስጥራት ለማወቅ ራሳችሁን አዘጋጁ በየቀኑ እነዚህን ምስጢራት ለማወቅ ትጉ ይህ በዚህኛው በሚመጣውም ዓለም የሚጠቅም ነዉና! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

😍🦋😍🦋😍🦋😍🦋😍🦋😍🦋 Jesus you have the greatest name of all, Jesus you always hear me when i call Jesus because of you I WILL NEVER FALL You have the greatest, The greatest name of all. GLORY TO HIS HOLY NAME! 🦋😍🦋😍🦋😍🦋😍🦋😍🦋😍 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“..መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥10 @TheDeepThingsOfTheSpirit
“..መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥10 @TheDeepThingsOfTheSpirit