en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
መንፈሳዊ ዓለምን የለ መስዋዕት ማንቀሳቀስ ፈጽሞ አይቻልም። በዋናነት ለሰው ልጆች ቤዛነት ኢየሱስ ክርስቶስ የኃጢአት መስዋዕት ሆኗል። በዚህም መስዋዕት ያመነ ደህንነትን አግኝቷል። እግዚአብሔር የሚሰራበት ሰው መሆን ደግሞ ራስን መስዋዕት አድርጎ መቅረብ ይጠይቃል። ራስህን ለመሰዋት ተዘጋጅተህ ካልሆነ እግዚአብሔር እንደሚሰራብህ አታስብ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አፍሪካን ለምን? *********** እግዚአብሔር በመጀመሪያ ሕዝብን ለራሱ ሲለይ በሙሴ አማካኝነት ለዓለም ሁሉ ሃሳቡን ፣ ሀይሉን ፣ክንዱን እና ክብሩን በምድር ለይ እንደገለጠ ሁሉ በዘመን መጨረሻም እግዚአብሔር ለዓለም ሁሉ ክብሩን ሃሳቡን እና ሃይሉን እንደሚገልጥ ከቅዱሳት መጽሐፍት እንረዳለን። እግዚአብሔር ክብሩን ለእስራኤላውያን በተራራው ለይ በገለጠበት በዚያን ቀን ያናወጠው ምድርን ብቻ ነበር አሁን ግን አንድ ጊዜ ደግሞ ምድርን እና ሰማይንም እንደሚያናውጥ ቃሉን ሰጥቷል። ይህ ጥያቄ የሌለበት ነገር ነዉ እግዚአብሔር ክብሩን በምድር ለይ ሁሉ ይገልጣል። ስጋ ለባሽም ሁሉ በአንድነት ያየዋል። “የእግዚአብሔርም ክብር ይገለጣል፥ ሥጋ ለባሹም ሁሉ በአንድነት ያየዋል፥ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።” — ኢሳይያስ 40፥5 አፍሪካ ይህንን የእግዚአብሔርን የመጨረሻ ዘመን ሥራ ለመስራት በእግዚአብሔር እንደተመረጠች አምናለሁ። ይህ የእኔ እምነት ብቻ አይደለም የመንፈስ ቅዱስም ድምጽ ነዉ። "ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ" እንደተባለ ነዉ። ይህ ቃል በቀጥታ ለክርስቶስ የሚውል ብሆንም ቤተክርስቲያን ከክርስቶስ የተለየች አይደለችም። የአፍሪካ ቤተክርስቲያን ለዚህ ተመርጣለች። አስተውሉ እግዚአብሔር ሁልጊዜ ሰዎች በናቁት እና በጣሉት ነገር ነዉ የሚሰራው። ይህ የእግዚአብሔር ምርጫ ነዉ። 1ኛ ቆሮንቶስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁷ ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤ ²⁸ እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ፥ የአፍሪካ አህጉረ ቤተክርስቲያን ይሄንን የመጨራሻውን ዘመን የወንጌል ተልዕኮ በዓለም ሁሉ ለማወጅ እና የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጥረት ሁሉ ለመግለጽ እንደተመረጠች የለምንም መጠራጠር አምናለሁ። በጸሎት እና በጾም ለእግዚአብሔር ስራ የሚመች እቃ ለመሆን እራሳችንን እናዘጋጅ። እግዚአብሔር ልሰራ ያለው ዓለምን ሁሉ የሚያስገርም አብ የሳባቸውንም ሁሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን የሚያስገባ ድንቅ ሥራ ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በዓለም ፣ በስጋ እና በኃጢአት ለይ የሚገኝ ድል ክርስቶስን በእናንተ ውስጥ እንድኖር በሙሉ ፈቃዳችሁ እውቅና በመስጠት ይጀምራል። ብዙዎች እንደመሰላቸው ክርስትና አማኝ ለክርስቶስ በራሱ የማድረግ አቅም ለመኖር የሚያደርገው ጥረት አይደለም። ነገር ግን ክርስትና በአማኝ ፍጹም መሰጠት እና ፈቃድ ክርስቶስ በአማኙ ውስጥ የሚኖረው ሕይወት ነዉ። ጥያቄው ግልጽ ነዉ: ሰውነቴን ለእግዚአብሔር ሕያው ቅዱስ እና ደስ የሚያሰኝ መስዋዕት አድርጌ እንዳቀርብ ነዉ። #keysTotheSupernatural. @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

I was singing to today "out of darkness into his marvellous light". Be blessed. @TheDeepThingsOfTheSpirit

🔥The evidence of The Holy Spirit 🔥 What is the evidence that proves you have the Holy Spirit upon you? Simple and very clear Jesus Christ told his apostles what follows after they got baptized by the Holy Ghost. “But ye shall receive power, after that the Holy Ghost is come upon you: and ye shall be witnesses unto me both in Jerusalem, and in all Judaea, and in Samaria, and unto the uttermost part of the earth.” — Acts 1:8 (KJV) The primary thing that follows after you got baptized by the Holy Ghost is "POWER" the Greek word is "Dunamis" it means " a dynamic ability to cause change". my question to you most of the Christians today, do we have this kind of POWER? The Lord continued and said the second thing that follow after the baptism is that you being "a witnesses". Do you know what it means to be a witness? It means to be " a proof producer". These two things are the first testimonies that follow the baptism of the Holy Ghost. Let The Personality and the power of the Holy Spirit find expression in your life. In Jesus Christ mighty Name.Amen. @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እሳቱም በመሠዊያው ላይ ዘወትር ይነድዳል፥ አይጠፋም፤ ካህኑም ማለዳ ማለዳ እንጨት ያቃጥልበታል፤ የሚቃጠለውንም መሥዋዕት በዚያ ላይ ይረበርባል፤ በዚያም የደኅንነትን መሥዋዕት ስብ ያቃጥላል።” — ዘሌዋውያን 6፥12 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

I believe this song will bless you! be uplifted. @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት:- 👉እግዚአብሔር የሚናገርባቸው የተለያዩ መንገዶች አሉት። የእናንተ መንፈሳዊ እድገት እና የማዳመጥ አቅም እግዚአብሔር የሚናገራችሁን መንገድ ይወስናል። ምክንያቱም እግዚአብሔር ለጥቅማችን ስለሚናገር መረዳት በማንችለው መንገድ አይናገረንም። ነገር ግን አንዳዴ ለሰዎች ጥፋት በሉዓላዊነቱ ሰዎች ሊረዱት በማይችሉት መንገድ ይናገራቸዋል። ለእኛ ለጆቹ ግን ለጥቅማችን በመሆኑ የሚገባንን መንገድ እንደሚጠቀም በመጀመሪያ ከ ቅዱሳት መጽሐፍት ከዛ ደግሞ ከልምምዶቼም መረዳት ችያለሁ። 👉የተወሰኑ መንገዶች:- 1➤የእግዚአብሔር ቃል (The Word) 2➤የእግዚአብሔር ድምጽ( Voice) 3➤ሰዎች ( peoples) :-Notice የእግዚአብሔር ሰዎች ብቻ አላልኩም! 4➤ህልም (Dreams or night Visions) 5➤ራዕይ (Open Vision ) 👉እነዚህ የተወሰኑት እግዚአብሔር የተናገረባቸው አሁንም የሚናገርባቸው መንገዶች ናቸዉ። (As i said before depending on your spiritual maturity God speaks to you):- መንፈሳዊ ብስላታችሁ የሚወስነው መንገዱን ብቻ ሰይሆን የንግግሩም ይዘት ጭምር ነዉ። 👉👉ስለዚህ እግዚአብሔርን ሁሌ የመስማት ትልቅ ፍላጎት ካላችሁ ሁሉንም መንገዶች ማወቅ እና ለእግዚአብሔር ንግግር ( sensitive) የሆነ አእምሮ እና መንፈስ ባለቤት መሆን ይኖርባችኋል። የኔ ምክር የሁሉም ነገር መጀመሪያ ከሆነው እና የተመዘገበው የእግዚአብሔር ንግግር ከሆነው 1➤ከእግዚአብሔር ቃል(መጽሐፍ ቅዱስ) ጀምሩ። የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት የመመርመር ባህል አሳድጉ። እንደዚህ ስታደርጉ ሌሎቹን በቀላሉ መለማመድ እና ማስተዋል ትችላላችሁ! .... ➤በእግዚአብሔር ቃል ለይ ተመስረቱ!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።” — ማቴዎስ 24፥14

🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 መቼም በየትኛውም ሁኔታና ጊዜ ከየትኛውም አይነት የሰይጣን ሀይል ጋር መጋፈጥ ስኖርባችሁ መርሳት የሌለባችሁ መሰረታዊ እውነት : ኢየሱስ በሞቱ እና በትንሳኤው በሰይጣን ለይ ፍጹም ፣ ዘላቂ ፣ የመጨረሻ እና የማይቀለበስ ድል መቀዳጀቱን ነዉ። ይህንን እውነት ለመለወጥ ሰይጣን ሊያደርግ የሚችለው ምንም ነገር የለም። ይህንን እውነት በመንፈሳችሁ መረዳት ከቻላችሁ በሰይጣን ለይ ፍጹም ድል በዘመናችሁ ሁሉ አላችሁ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheMysteriesOfGod

🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ➤Jesus through his death and resurrection has administered to Satan a TOTAL, PERMANENT, FINAL and IRREVERSIBLE defeat! Hallelujah Glory to the lamb! ➤There is nothing that Satan can do that can change the truth! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheMysteriesOfGod

4_5848060356798187120.m4a6.41 KB

RAPTURE SOON, BUT BEFORE THAT REVIVAL VERY SOON!

Group Join በማድረግ ጥያቄ መጠየቅ ሃሳብ መስጠጥ ሌሎችም መንፈሳዊ መልእክቶች ማካፈል ትችላላችሁ። ThingsOfGod~Group @TheMysteriesOfGod

The Bible is a speaking book. If you can only develop ears which can hear. -Voice

የእግዚአብሔር ቃል Vs የእግዚአብሔር ድምጽ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

photo content

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ከሁለት ቀን በኃላ ተመልሶ መምጣት በእስራኤላውያን የምድረበዳ ታሪክ ውስጥ: ➤ቅዱሳት መጽሐፍት በግልጽ እንደሚያስተምሩን "መጽሐፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚናገሩ ምስክሮች ናቸዉ" ይህንን የተናገረው ጌታችን ነዉ። “እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤” — ዮሐንስ 5፥39 ➤ከዚህ በፊት በጻፍኳቸው ጽሁፎች ቀናት ዓመታትን የመግለጽ ተግባር እንዳላቸው አይታችኋል። በሆሴዕ መጽሐፍ የተነገረው ትንቢት( የእስራኤል መጠገን /ብሔራዊ መዳን/ ) በሁለተኛው ቀን መጀመሪያ አከባቢ (በ 1948) መፈጸም እንደጀመረ ግልጽ ሆኗል። ➤በሆሴዕ ትንቢት መሰረት በሶስተኛው ቀን ጀምሮ (ከ 2000 ዓመት በኃላ ያለው ጊዜ) እስራኤላውያን በእግዚአብሔር ፊት በሕይወት ይኖራሉ። ይህ ማለት ወደ ብሔራዊ ንስሃ መድረስ እና ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን የሚቀበሉ መሆኑን ያሳያል። ይህንኑ ተመሳሳይ ስዕል በእስራኤላውያን የምድረበዳ ታሪክ ውስጥ ማየት እንችላለን! ዘጸአት 19 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ ወደ ሕዝቡ ሂድ፥ ዛሬና ነገም ቀድሳቸው፥ ልብሳቸውንም ይጠቡ፤ ¹¹ በሦስተኛው ቀን ሕዝቡ ሁሉ ሲያዩ እግዚአብሔር በሲና ተራራ ላይ ይወርዳልና ለሦስተኛው ቀን ይዘጋጁ። ➤"ዛሬና ነገ ቀድሳቸው በሦስተኛውም ቀን ሕዝቡ ሁሉ ሲያዩ እግዚአብሔር በሲና ተራራ ለይ ይወርዳል ለሦስተኛው ቀን ይዘጋጁ"። ይህንን ንባብ አይኖቼ ስያዩት በከፊል የደነገጥኩ ብሆንም "ቤዛዬ" በደጅ እንደሆነ በማወቄ ደስታ ሞልቶኛል!!!! ➤ይህ እግዚአብሔር ሙሴን ህዝቡ ለ "ሁለት ቀን" መንጻት ፣ ልብሳቸውን ማጠብ እና መዘጋጀት እንዳለባቸው ነግሮት "በሦስተኛው ቀን" ሕዝቡ ሁሉ እያዩት እግዚአብሔር ከሰማይ እንደሚወርድ ጠቁሞታል!!! ይህ ግልጽ መልእክት ነዉ። የእግዚአብሔር ህዝብ (ቤተክርስቲያን) በሁለት ቀን(2000 ዓመት) ውስጥ መንጻት ልብሷን በበጉ ደም ማጠብ እና ውብ ሆና መዘጋጀት እንዳለበት በሚስጥር የሚናገር ስዕል ነዉ። ተመልከቱ አድስ ኪዳን ምን እንደምል“የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሚስቱም ራስዋን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን ሐሤትም እናድርግ ክብርንም ለእርሱ እናቅርብ።” — ራእይ 19፥7 ➤ጌታችን ከምታስቡት በላይ በደጅ ቀርቧል!!! ብዙ ሰይረፍድ ከእግዚአብሔር ጋር ተስማሙ። እግዚአብሔራዊ ያልሆነን ነገር ሁሉ ከሕይወታችሁ አሽቀንጥራችሁ ጣሉ። ሦስተኛው ቀን ከፊታችን ነዉ። Share በማድረግ ሌሎችንም እናንቃ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

👉ስለ ጌታችን ተመልሶ መምጣት ስናወራ ስለ ኃለኛው ዝናብ ማውራት የግድ ነዉ። የእግዚአብሔር መንፈስ ከመንፈሴ ጋር ሆኖ በተደጋጋሚ ያረጋግጥልኛል። ቤተክርስቲያን በ እውነተኛ ማንነቷ እና ክብሯ በምድር ለይ የምትታይበት ጊዜው እነሆ ከፍታችን ነዉ። “መንፈስህን ትልካለህ ይፈጠራሉም፥ የምድርንም ፊት ታድሳለህ።” — መዝሙር 104፥30 #➤የእግዚአብሔር ወንድና ሴት ልጆች በተሰበረ መንፈስ የእግዚአብሔርን ፊት እና ሃይል ፈልጉ!!!!

ቤዛችን በደጅ ነዉ *********** 👉ከ 2000 ዓመት በፊት በ 30 ዓ.ም እስራኤላውያን መሲሑን (ኢየሱስ ክርስቶስን) በአመፀኞች እጅ ለሞት አሳልፈው ሰጡት። በነብዩ ዘካርያስ “ሰይፍ ሆይ፥ ባልንጀራዬ በሆነው ሰው በእረኛዬ ላይ ንቃ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ እረኛውን ምታ፥ በጎቹም ይበተናሉ፤ እጄንም በታናናሾች ላይ እመልሳለሁ።” — ዘካርያስ 13፥7.....ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጸመ። እስራኤላውያን(በጎቹ) እረኛቸውን(ክርስቶስን) በመምታታቸው ፣ ከ 30 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም ሁሉ መበተን ጀመሩ። በ 70 ዓ.ም ክብራቸው ኢየሩሳሌም ሙሉ በሙሉ በሮም ሀይል በመፍረሷ ይህ የበጎቹን ሁሉ መበታተን ወሰነ። ሁሉም ሰዉ እንደሚያውቀው እ.እ.አ በ 1948, May 14, እግዚአብሔር በሰጣቸው ተስፋ መሰረት ወደ እናት ሃገራቸው ሰበሰባቸው። ይህ የሆነው ከ 1918 ዓመታት በኃላ ነበር። ይህ ከጌታ መምጣት ጋር ምን ያገናኘዋል? የበለስቱ ማቆጥቆጥ(የእስራኤል እንደገና መቆም) የዘመን መጨረሻ ምልክት እንደሆነ ጌታ በግልጽ ተናግሯል። ሉቃስ 21 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁹ ምሳሌንም ነገራቸው እንዲህ ሲል፦ በለስንና ዛፎችን ሁሉ እዩ፤ ³⁰ ሲያቈጠቍጡ ተመልክታችሁ በጋ አሁን እንደ ቀረበ ራሳችሁ ታውቃላችሁ። ³¹ እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህ ሁሉ መሆኑን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች እወቁ። ***************************** ➤ የእስራኤል መቆም ከ ሁለት ቀን በኃላ (2000 ዓመት በኃላ )*እንደምሆን የተነገረ ትንቢት: #➤በመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ውስጥ ቀናት አመታትን የመወከል ተግባር አላቸዉ። ስለዝህ ሁለት ቀን ማለት ሁለት ሺ አመት የሚሆንበት አግባብ አሉ። “እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ሆነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 3፥8 ➤ነብዩ ሆሴዕ የእስራኤል እንደገና መቆም የሚሆነው ከ ሁለት ቀን በኃላ እንደሆነ ተናግሯል። ይህ ማለት ከ ሁለት ሺ ዓመት በኃላ ማለት ነዉ። “ከሁለት ቀን በኋላ ያድነናል፤ በሦስተኛውም ቀን ያስነሣናል፥ በፊቱም በሕይወት እንኖራለን።” — ሆሴዕ 6፥2 #➤በነብዩ በተነገረው ትንቢት መሰረት እስራኤላውያን በ 30 ዓ.ም ተሰብረው በ 1948 , ከ 1918 ዓመታት በኃላ መዳን(ይህ መዳን ብሔራዊ መዳን ነዉ) ጀምረዋል። በእኔ እምነት በሔራዊ መዳናቸው እ.እ.አ በ 2030 ይፈጸማል። በ 2030 እየሩሳሌም ያለምንም ጥርጥር ሙሉ በሙሉ የእስራኤላውያን ትሆናለች። ይህ ህደት ባለፈው አመት የአሜሪካው መሪ ዶናልድ ትረምፕ "እየሩሳሌም ዘላለማዊ የእስራኤል መዲና ነት" ባሉት መሰረት ግልጽ ሆኗል። ➤እስከ 2030 ድረስ እስራኤላውያን እየሩሳሌምን ብሎም ቤተመቅደሱ የሚሰራበትን ተራራ የራሳቸው ማድረግ የሚችሉ ከሆነ ሁሉም ነገር ብዙ ሰይቆይ የሚያበቃ ይሆናል። በ ሆሴዕ ትንቢት መሰረት በ ሦስተኛው ቀን እስራኤላውያን በእግዚአብሔር ፊት ይኖራሉ( ይህ ማለት በመሲሑ ያምናሉ) ። ...2ኛ ጴጥሮስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ በመጨረሻው ዘመን እንደ ራሳቸው ምኞት የሚመላለሱ ዘባቾች በመዘበት እንዲመጡ ይህን በፊት እወቁ፤ ⁴ እርሱም፦ የመምጣቱ የተስፋ ቃል ወዴት ነው? አባቶች ከሞቱባት ጊዜ፥ ከፍጥረት መጀመሪያ ይዞ ሁሉ እንዳለ ይኖራልና ይላሉ። … ⁸ እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ሆነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ። ⁹ ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit