en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
👉𝚌𝚞𝚕𝚝𝚒𝚟𝚊𝚝𝚎 𝚝𝚑𝚎 Sᴘɪʀɪᴛ ᴏғ ᴡᴀƦ!💪 ᴠɪᴄᴛᴏʀʏ 𝚒𝚜 𝚖𝚘𝚜𝚝𝚕𝚢 𝚊𝚝𝚝𝚊𝚌𝚑𝚎𝚍 𝚝𝚘 𝚝𝚑𝚎 Sᴘɪʀɪᴛ ᴏғ ᴡᴀƦ 𝚝𝚑𝚊𝚗 𝚒
👉𝚌𝚞𝚕𝚝𝚒𝚟𝚊𝚝𝚎 𝚝𝚑𝚎 Sᴘɪʀɪᴛ ᴏғ ᴡᴀƦ!💪 ᴠɪᴄᴛᴏʀʏ 𝚒𝚜 𝚖𝚘𝚜𝚝𝚕𝚢 𝚊𝚝𝚝𝚊𝚌𝚑𝚎𝚍 𝚝𝚘 𝚝𝚑𝚎 Sᴘɪʀɪᴛ ᴏғ ᴡᴀƦ 𝚝𝚑𝚊𝚗 𝚒𝚝'𝚜 𝚝𝚘 𝚠𝚎𝚊𝚙𝚘𝚗𝚜. @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

God will make a way! No matter what Trust In God, He will make a way! Be blessed. 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ያዕቆብ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²² ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ። ²³ ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤ ²⁴ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል።

የእግዚአብሔርን ቃል በጥልቀት ስንረዳ እና የተረዳነው ቃል አድራጊዎች ስንሆን እግዚአብሔር ለእኛ በታርኪ የሰማነው እና ያነበብነው ባለታሪክ መሆኑ ይቀርና ከሰውነታችን በላይ እሁን ከእስትንፋሳችን በላይ ቅርብ ይሆናል። Join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

-Dawit Getachew "አንተ ክብሬ ነህ" ѕιzє 6.4 МВ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በጣም በፍጥነት ብዙ መጽሐፍት ማንበብ ትርፉ ትንሽ ትምህርት እና ብዙ ትዕቢት ነዉ!።😁። -ቻርለስ ስፑርጅዮን @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit
በጣም በፍጥነት ብዙ መጽሐፍት ማንበብ ትርፉ ትንሽ ትምህርት እና ብዙ ትዕቢት ነዉ!።😁። -ቻርለስ ስፑርጅዮን @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ቃሉ በሕይወታችን እንዴት ያፈራል? ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ✍️የእግዚአብሔር ቃል ዘር ነዉ: "ዘሪው ቃሉን ይዘራል።" -ማርቆስ 4:14 ። መቼም ዘር በውስጡ ያለው አቅም ለሁላችንም ግልጽ ነው። ዘር በውስጡ ሕይወት አለው።ለምሳሌ የ ማንጎ ዘር በውስጡ የማንጎ ዛፍ የመሆን እምቅ አቅም በውስጡ አለው። በዚህ አውድ የማንጎን ፍሬ ብቻ በማየት የመንጎ ዛፍ ማየት ይቻላል: ይህ የሚጠይቀው የዘርን ተፈጥሮአዊ አቅም መረዳት ብቻ ነዉ። ነገር ግን ይህ እምቅ ውስጣዊ አቅም ወጥቶ ሕይወቱ ለውጫዊው ዓለም መታየት ካለበት አንድ ማድረግ ያለብን ነገር አለ እርሱም: ዘሩን ትክክለኛው መሬት ለይ መጣል ነዉ። ዘር በውስጡ የማደግ የመለወጥ ዛፍ የመሆን እና የማፍራት አቅም ያለው ቢሆን እንኳ ይህ እሁን እንድሆን መጣል ያለበት ትክክለኛ ቦታ አለ። የቤታችሁ ወለል ለይ ወይም የቤታችሁ መስኮት ጠርዝ ለይ ያስቀመጣችሁት ዘር ለ አንድ ሺህ አመትም ዛፍ አይሆንም! ነገር ግን ለረጅም ጊዜ እንደዛ አይነት ቦታ ለይ ያስቀመጣችሁትን ዘር እንኳ አሁን አንስታችሁ አፈር ውስጥ ብታኖሩት በቀናት ውስጥ ሕይወት ከውስጡ ስወጣ ማየት ትችላላችሁ። ስለዚህ ዘር ማፍራት ካለበት የመጀመሪያው ትክክለኛው መሬት ለይ መውደቅ ይኖርበታል ሌላው ደግሞ ተገቢውን እንክብካቤ መግኘት አለበት። ይህ መርህ በልባችን ማሳ ለይ ለሚዘራው የእግዚአብሔር ቃልም የሚሰራ ነዉ። የእግዚአብሔር ቃል በሕይወታችን እንዲያፈራ የመጀመሪያው እኛ ትክክለኛው መሬት መሆን አለብን። ሌላው ደግሞ በቀጣይነት የተዘራብንን ቃል በቃል በመደገፍ እና በማሰላሰል ነፍሳችን እንድገዛ መፍቀድ አለብን የዚህን ጊዜ በሰውነታችን ለይ መገለጫ መግኘት ይጀምራል። የትክክለኛ መሬት ባሕርይ ጌታችን በዚህ መልኩ ነዉ ያስቀመጠልን "ቃሉን #ሰምቶ #ማስተዋል" .....“በጥሩ መሬት ላይ የተዘራው ዘር ግን ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውለውን ሰው ይመስላል፤ በርግጥም ፍሬ ያፈራል፤ አንዱ መቶ፣ አንዱ ሥልሳ፣ አንዱም ሠላሳ ፍሬ ሰጠ።”” — ማቴዎስ 13፥23 (አዲሱ መ.ት) መስማት ብቻውን በቂ አይደለም ማስተዋል የግድ አስፈላጊ ነዉ። በዚህ አውድ ማስተዋል የሚለውን ቃል (በጥልቀት መረዳት እና አጥብቆ መያዝ) የሚል ትርጉም ወይም ትንታኔ ልንሰጠው እንችላለን። 👉ቃሉን መስማት! 👉የሰሙትን ቃል በጥልቀት መረዳት! 👉በጥልቀት የተረዱትን ቃል በልብ አጥብቆ መያዝ! ✍️ይህንን ማድረግ የምንችል ከሆነ የምንሰማውን የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ፍሬ እንድያፈራ ማድረግ እንችላለን። “እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ እንድት ሄዱና ፍሬ እንድታፈሩ ፍሬያችሁም እንዲኖር ሾምኋችሁ። ስለዚህም አብ በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ ይሰጣችኋል።” — ዮሐንስ 15፥16 (አዲሱ መ.ት) 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

#የዛሬ_ማታ_ጥቅስ የእግዚአብሔር መንግስት ለነማን ናት!? #መንግስት የሚለው ቃል "Kingdom" የሚል የእንግሊዝኛ ቃል ነዉ: ስንፈታው "የንጉሥ ግዛት" /King domine/ ይሆናል። ይህ የዚህ ዘመኑ ትውልድ ከሚያውቀው የ "ዲሞክራሲ" የመምራት ስርዓት የተለየ ነዉ። ስለዚህ እያወራን ያለነው ስለ "ዲሞክራሲ የመምራት ክህሎት" ሰይሆን ስለ ንጉሥ የመግዛት ሃይል ነዉ! 👉የእግዚአብሔር ልጆች የትኛውም "መንግስት" "Kingdom" ማግኘት የሚፈልግ "ንጉሥ" ብዙ ሃይል ያለውና #ግፈኛ መሆን አለበት! "መንግስት" የሚገኘውም በ ዲፕሎማሲ" ሰይሆን "በግፍ" ነዉ!!! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ተወዳጆች ሆይ የእግዚአብሔርን መንግስት እና የእግዚአብሔርን መንግስት ነገሮች በተመለከተ ኢየሱስ በሰራው ሥራ ምክንያት #ይገባኛል የሚል ግፈኛ( በሃይል የሚናጠቅ) መሆን ይጠበቅባችኋል!!!! “ከመጥምቁም ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፥ ግፈኞችም ይናጠቋታል።” — ማቴዎስ 11፥12 ድምጻችሁን አሰምታችሁ ይህንን ደጋግማችሁ አውጁ👉 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ኢየሱስ ክርስቶስ በእኔ ምትክ በመሞቱ እና ከሙታን በመነሳቱ የእግዚአብሔር መንግስት ይገባኛል!!! የእግዚአብሔርን መንግስት በሃይል እናጠቃለሁ! የእግዚአብሔር መንግስት አሁን እና ለዘላለም የምኖረው እውነት ነዉ!!! በእግዚአብሔር መንግስት ሃይል ያለሁበትን ዓለም እገዛለሁ! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ሰላም ደስታ- ፀጋህ ይርዳኝ🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

እግዚአብሔር የሚመልሰው ጸሎት --------------------------------------------- 👉ምድር ለይ ካሉ ሰው ሰራሽና አጋንንታዊ ኃይማኖቶች ስለ ጸሎት የማያስተምር የለም: ኃይማኖት ጸሎት #የምፈልጉትን ነገር ከአምላክ ለምነው የምቀበሉበት ልማድ እንደሆነ ተከታዮቹን ያስተምራል: : ይህ #አስተምህሮ እንኳን አይደለም በጨለማ ላሉት: በብርሃን ላሉ ለቤተክርስቲያን ልጅች እንኳ በአእምሮ እውነት የሚመስል ነዉ። ነገር ግን እውነተኛ የሕይወት መንገድ የሆነው ክርስትና ስለ ጸሎት የሚያስተምረው ትምህርት አለው። ------------- ------------ ---------- ---------- ጸሎት በክርስትና እምነት ውስጥ በጣም ትልቅና ሰፊ ጥቅም ያለው መንፈሳዊ ልምምድ ነዉ። በእውነተኛው ትምህርት መሰረት ጸሎት ከአምላክ የምንፈልገውን ከመለመን ያልፋል። እውነቱን እንነጋገር ከተባለ ክርስትያን( በቃሉ ብርሃን በእምነት የሚሄድ ክርስትያን) ያልተቀበለው ወይም የሚያጣው ስለሌለ(መዝሙር 23) የራሱ ፍላጎት የለውም: #ፍላጎቱ_ሁሉ_የጌታው_ፈቃድ_ነዉ። ስለዚህ በእኛ ሕይወት ጸሎት የምንፈልገውን ከመጠየቅ አልፎ እሱ ጌታችን የሚፈልገውን መጠየቅ ይሆናል። ሐዋርያው ጳውሎስን ጌታ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ደማስቆ በሚወስደው መንገድ ለይ ስያገኘው ጳውሎስ ጌታን ሁለት ጥያቄ ነበር የጠየቀው: የመጀመሪያ "አንተ ማን ነህ?" የሚል ነበር ለዚህ ጥያቄ መልስ እንዳገኘ ቀጥሎ የጠየቀው ጥያቄ "ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?" የሚል ነበር (ሐዋርያት 9) ። ይህ በጣም የሚደንቅ ነዉ: ለበሰሉ ክርስትያኖች ጸሎት ከእንጀራ፣ከልብስ፣ከቤት ያለፈ ነዉ(ማቴዎስ 6:25-33): ምክንያቱም እነዚህ ነገሮች ሁሉ እሱን በማወቅ ውስጥ እና እሱ በሕይወታችን ያለውን ዓለማ በማግኘት ውስጥ ያሉ ናቸዉ: “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።” — ማቴዎስ 6፥33 👉እግዚአብሔር የሚመልሰው ጸሎት እንደፈቃዱ የሚደረግ ጸሎት ነዉ: “በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል።” — 1ኛ ዮሐንስ 5፥14 👉ጸሎታችሁ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማእከል ያደረገ ከሆነ: እንደሰማችሁ እወቁ ከዛም በእምነት እንደተቀበላችሁት ቁጠሩ: “የምንለምነውንም ሁሉ እንዲሰማልን ብናውቅ ከእርሱ የለመነውን ልመና እንደ ተቀበልን እናውቃለን።” — 1ኛ ዮሐንስ 5፥15 👉እናውቀው ዘንድ እና በእርሱም እንድንኖር የእግዚአብሔር ፈቃድ ነዉ። በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚኖር ሰው በእግዚአብሔር ይኖራል: በእግዚአብሔር የሚኖር ደግሞ ያለምንም ጉድለት በሙላት ይኖራል። Join 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Watch "🔴 Jerusalem tonight singing that they are waiting for Messiah" on YouTube http://www.youtube.com/shorts/vV4y9czhVR8 ትናንት ማታ በእስራኤል በኢየሩሳሌም: እስራኤላውያን #መሲሑን እየጠበቁት እንደሆነ በሚናገር መዝሙር ስዘምሩ የሚያሳይ ነዉ። #የተባረከው_ጌታችን_በደጅ_ነዉ_ንቁ!

ሰላም ደስታ - አልደራደርም 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“እርሱም መጥቶ የእግዚአብሔርን ጸጋ ባየ ጊዜ ደስ አለው፥ ሁሉንም #በልባቸው_ፈቃድ በጌታ ጸንተው ይኖሩ ዘንድ መከራቸው፤” — ሐዋርያት 11፥23 በጌታ ጸንተን የምንኖረው በልባችን ፈቃድ ነዉ። እግዚአብሔር ነጻ ፈቃዳችንን ይፈልገዋል። በዚህ ሕይወት ከእግዚአብሔር ለእናንተ እና በእናንተ ምንም ነገር ከመሆኑ በፊት የናንተ የልብ ነጻ ፈቃድ አስፈላጊ ነዉ። ፈቃዳችሁን ከሰጣችሁት እግዚአብሔር ከእናንተ ውስጥ ድንቅን ማውጣት ይችላል። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

From the pages of my heart.... This worship songs bless your soul! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።” — 1ኛ ዮሐንስ 4፥4 @TheDeepThingsOfTheSpirit

ለክብር የሚሆን እቃ - audio - ዮሐንስ ግርማ። “የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።” — መዝሙር 51፥17 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔርን የመናገር ባሕርይ ከመጠራጠር የሰውን የመስማት ችሎታ መፈተሽ የተሻለ ነዉ። መነገር የእግዚአብሔር ባሕርዩ ነዉ: መስማት ግን የሰው ልጅ ሃላፊነት ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ᴄʜɪʟᴅ ᴏғ ɢᴏᴅ sʜᴀʀᴘᴇɴ ʏᴏᴜʀ ᴇᴀʀs. ɢᴏᴅ ɪs ᴀʟᴡᴀʏs sᴘᴇᴀᴋɪɴɢ! -🅥🅞🅘🅒🅔

እግዚአብሔር ሰይናገር በሕይወታችሁ የሆነ አንድም ነገር የለም! እንዴት??? ይህንን መልእከት ስሙ! ለዚህ ቻናል አባላት። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም።” — ኢያሱ 1፥8