en
Feedback
TheDeepThingsOfGod

TheDeepThingsOfGod

Open in Telegram

Glorious Church the bride of Christ. Rapture ready!

Show more
1 810
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
“አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።” — መዝሙር 51፥10

የእግዚአብሔር ልጆች በማንኛውም አይነት ሁኔታ ውስጥ እያለፋችሁ ብሆን ሁሉን የሚችል አምላክ ከእናንተ ጋር መሆኑን አትርሱ! በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ አታልፉም የሚል ተስፋ አልሰጠንም ነገርግን በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ከእኛ ጋር እንደሚሆን የጸና ተስፋ ሰጥቶናል! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ኤፌሶን 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴-¹⁵ ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ ¹⁶-¹⁷ በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ¹⁸-¹⁹ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ።

✅ ከአንተ/ች የቀደመ የእግዚአብሔር ዓላማ❕ ኤርምያስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴ የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። ⁵ በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ። እግዚአብሔር ከምናስበው በለይ አዋቂ አምላክ ነዉ! ምንም ነገር ከመስራቱ በፊት ለመስራት በቂ ምክንያት ያበጃል: እንኳን አይደለም እግዚአብሔር ልባም ሰዎችም ከማሰባቸው ከመናገራቸው እና ከማድረጋቸው በፊት ምክንያት ይኖራቸዋል። አሁን የምትጠቀሙበትን ስልክ ወይም ኮምፒውተር እንኳ የሰሩ ሰዎች ከመስራታቸው በፊት ለምን? የሚለውን ጥያቄ ቀድመው መልሰውታል። ለምን? ለሚለው ጥያቄ ያገኙት መልስም ነዉ ለመስራት ያነሳሳቸው። ሰዎች በዚህ ደረጃ ዓላማ መር ከሆኑ ከሰዎች ይልቅ እግዚአብሔር እንዴት ይሆን?? እግዚአብሔር የለ ዓላማ የሚሰራው አንድም ነገር የለም!!! አንተን/ችን ከመስራቱ በፊት: ለመስራት ያነሳሳው ምክንያት በዘላለማዊ ምክሩ ውስጥ ነበረው! ከአንተ/ች የቀደመ የእግዚአብሔር ዓላማ አለ! በፍጹም የለዓላማ አልተፈጠርክም/ አልተፈጠርሽም። አንዳንዶች እንደሚመስላችሁ የአጋጣሚ ውጤት አይደላችሁም! ወይም ሰዎች እንዳሏችሁ የሴት ስህተት ወይም የወንድ ስህተት ውጤት አይደላችሁም! የእግዚአብሔር የእጅ ስራዎች እንጂ! “ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን።” — ኤፌሶን 2፥10 (አዲሱ መ.ት) ከመጣችሁበት መንገድ በላይ የመጣችሁበት ምክንያት እንድቆጣጠራችሁ አድርጉ!!! ከእናንተ የቀደመው የእግዚአብሔር ዓላማ በሕይወታችሁ የሰላም እንጂ የክፉ አይደለም! ፍጻሜው ያማረ እና ተስፋን የሚሰጥ እንጂ የሚጎዳችሁ አይደለም! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።” — ሐዋርያት 1፥8 አገልጋይነት በመንፈስ ቅዱስ ሃይል የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር የምትሆኑበት ሕይወት ነዉ! ዝና እና ስም ማትረፊያ ወይም ሃብት መሰብሰቢያ መንገድ አይደለም! ስማችንም ዝናችንም ሃብታችንም ያለው በኢየሱስ ውስጥ ነዉ! ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወታችሁ እና የአገልግሎታችሁ ማእከል ከሆነ መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ሃይሉን የማይገልጥበት ምንም ምክንያት የለም። መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችሁ ኢየሱስን ያክብረው!!!! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

Bless the LORD, O my soul: and all that is within me, bless his holy name.” @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔር ልጆች ሰይጣን በሽንገላው ያላችሁበት እንዲያስቀራችሁ አትፍቀዱለት ውስጣችሁ ዓለምን መለወጥ የሚችል የመንፈስ ቅዱስ ሃይል አለ! በዚህ ሃይል ዓለማችሁን ለወጡት ተነሱና ተከናወኑ። @TheDeepThingsOfTheSpirit

ለምቡዳ በ 1920 ለመጀመሪያ ጊዜ የወንጌል ሚሽነሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንደመጡ ያረፉበት ተራራ ለይ ተገኝቼ በመጸለዬ ደስ ብሎኛል! ይህ ቦታ ወንጌልን የተቀበሉት የመጀመርያው ሰውም የሚጸልዩበት ቦታ
ለምቡዳ በ 1920 ለመጀመሪያ ጊዜ የወንጌል ሚሽነሪዎች ወደ ኢትዮጵያ እንደመጡ ያረፉበት ተራራ ለይ ተገኝቼ በመጸለዬ ደስ ብሎኛል! ይህ ቦታ ወንጌልን የተቀበሉት የመጀመርያው ሰውም የሚጸልዩበት ቦታ እንደነበር ስምቻለሁ! @TheDeepThingsOfTheSpirit

🦋🦋🦋🦋ለ እህቶች🦋🦋🦋🦋🦋 በክርስቶስ ውድ እህቶቼ የሆናችሁ ይህን ቃል ስትመለከቱ ጌታ ልትሰሩ የመደበላችሁን ሥራ እንድትሰሩ የክርስቶስ መንፈስ በእናንተ ውስጥ እንዲያልፍ እንድትፈቅዱለት ጉልበት እንድሆናችሁ እጸልያለሁ። ብርሃናችሁ እንዲበራ በውስጣችሁ የተደበቀውና ታፍኖ የሚገኘው የተቀበላችሁት ተስጥኦችሁ ወጥቶ ለእግዚአብሔር ክብር እንድታውሉት፣በእጃችሁ ሁሉ የተሰጣችሁን ሥራ እግዚአብሔርን በመታመን በጥንካሬ እንድታከናውኑ፣አልተውሽም፣አልጥልሽም ያለውን ጌታን በማሰብ ድካማችሁን ሳይሆን እግዚአብሔር የዓለምን ጥበበኞች ሊያሳፍር ደካማውን እንደመረጠ እንድታስተውሉ ላበረታታችሁ እወዳለሁ። እኛ የታላቁ እግዚአብሔር ወንዶችና ሴቶች ልጆች ነን። በጨለማና በሞት ጥላ ስር ያሉትን ለመታደግ ለእግዚአብሔር ጥሪ ክብር ልንሰጥ እንዴት አቃተን? ሙሴን ፣አሮንና ማርያምን ሕዝቡን እንድመሩ አልላከምን? ባራቅ ዲቦራን አንቺ ከእኔ ጋር ካልሄድሽ ወደ ጠላት መንደር አልወጣም አላለምን? (መሳፍንት 4:8) እግዚአብሔር ራሱ የመረጣቸውን ወንዶችና ሴቶች ልጆቹን ሐና፣ሕልዳና ማርያም በሚል ስም የተጠቀሱትንና በእግዚአብሔር ቃል ከጳውሎስ ጋር ይተባበሩ የነበሩ እህቶች ለሥራው አስነስቷል። ለእግዚአብሔር መንግስት ሥራ ያለዕረፍት ለመሰጠት ሴት መሆኔ የበለጠ ያተጋኛል ብዬ አምናለሁ። እናት ማርያ ውድወርዝ ኢተር : ለእህቶች የሰጠችው ምክር ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

አይዳ አብራሃም : እንዴት ያለ ፍቅር ነዉ.. @TheDeepThingsOfTheSpirit

ደግም ልደት ******* ዮሐንስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹² ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ ¹³ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም። ደግም ለደት በጌታ በኢየሱስ የተፈጸመ ስራ ያገኘነው ፀጋ ነዉ። በደግም ልደት ከእግዚአብሔር በእምነት ተወልደናል ፤ የእግዚአብሔር ዘር በውስጣችን ነዉ። ደግም መወለድ ግን የጉዞው መጨረሻ አይደለም! መጀመርያ ብቻ እንጂ መጽሐፍ በእግዚአብሔር ሕይወት እንድናድግ እና እንድንጠነክር ያስተምረናል ከዛም በላይ ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልክተን ከፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግስት መሮጥ እንዳለብን ያስጠነቅቀናል። የተወደዳችሁ በዚህ ጉዞ ውስጥ ለአሸናፊነት የሚያበቃችሁ ሁሉ ተሰጥቷችኃል! መጽሐፍ “የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።” — 2ኛ ጴጥሮስ 1፥2-3 ይላልና። በዚህ የድል ጉዞ ውስጥ ለሕይወት እና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚያስፈልጋችሁ ሁሉ በእናንተ ውስጥ ነዉ! ነገር ግን ይህ የሚሰራው #በማወቅ ነዉ! እውነተኛ አምላክ የሆነዉን እግዚአብሔርን እና ያላከውን ኢየሱስ ክርስቶስን በጥልቀት በማወቅ ነዉ። የእግዚአብሔርን እውነት ለማወቅ በርቱ ሕይወታችሁ ነዉና!!! የጀመራችሁት የክርስትያን ጉዞ የፈጣራችሁን ራሱን ለመምሰል የጀመራችሁት ነዉ!!! መጽሐፍ “የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤” — ቆላስይስ 3፥10 እንደምለው ነዉ። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

የእግዚአብሔር ሕይወት ለእናንተ ሆኗል!!!

ተወዳጆች ዛሬ በነበረኝ የጸሎት ጊዜ ስለ ሁላችንም ስጸልይ ነበር። እግዚአብሔር የሚያዩ አይኖች የሚሰሙ ጆሮዎች እና የሚያስተውል ልብ እንድሰጠን ይህ የጥበብና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጠን የልብ አይኖቻችንም እንዲበሩ የሁልጊዜ ጸሎቴ ነዉ። እግዚአብሔር በጌታ የጠራንን ተስፋ በውስጣችን ያስቀመጠውን የርስት ክብር ባለጠግነት እና ኢየሱስን ከሙታን ያስነሳውን በእኛም የሚሰራውን ታላቁን የእግዚአብሔርን ሃይል እንድናውቅ እና በዚህ ብርሃን እንድንመላለስ ያለማቋረጥ እጸልያለሁ! ከዚህ በኃላ ቤተክርስቲያን በዚህ እውቀት እንድትሞላ ያለኝ ተስፋ ብዙ ነዉ! ተወዳጆች ሆይ ይህንን የእግዚአብሔር ፈቃድ እንድናደርግ ሃይል አለን! @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

ዛሬ እስከ እኩለ ቀን በሚኖረኝ የጸሎት ጊዜ በኃለኛው ዝናብ እንቅስቃሴ ውስጥ አካል እንድትሆኑ እጸልያለሁ! እግዚአብሔር ተመልካች ብቻ ከመሆን እንዲያድናችሁ ተስፋዬ ነዉ። እናንተም ከቻላችሁ እስከ እኩለ ቀን ጸልዩ! ተባረኩ።

ፍጹም ለውጥ በቤተክርስቲያን ውስጥ በሚኖረን የጊዜ ርዝመት የሚፈጠር ተዓምራት ሰይሆን በጊዜ ህደት ፍጹም ቁርጠኛ በሆነ የለውጥ መንፈስ ከእግዚአብሔር መንፈስ እና ቃል ጋር በሚደረግ የማያቋርጥ ህብረት የሚፈጸም እውነት ነዉ! 🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋🦋 @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

🦋 ስኬት🦋 ዓለም ስኬትን የምታብራራበት የራሷ መንገድ አለ እኛ ያለንበት የእግዚአብሔር መንግስት ደግሞ ስለ ስኬት የራሱ የሆነ ትርጉም አለዉ። በዓለም ያሉ ብዙ ሰዎች እንደሚያስቡት ስኬት ገንዘብ መሰብሰብ እና ቅንጡ ኑሮ መኖሮ ወይም በዚህ ምድር መመዘኛ ብዙ መማር እና ስምን ማትረፍ ወይም ዝናን ማትረፍ አይደለም ፤ ብዙ ወዳጆች ማትረፍም አይደለም። ምክንያቱም እጅግ በገንዘብ የበለጸጉ ነገር ግን በየሳምንቱ ለህክምና ህንድና ባንኮክ የሚመላለሱ ሰዎች አሉ ፤ በዙ ለብሰው የማይሞቃቸው በሰዎች ተከበው ዋስትና የማይሰማቸው እና ሕይወታቸውን በፍርሃት የሚኖሩ ሰዎች ብዙ ናቸዉ! የዓለምን ጥብብ በጥልቀት የተማሩ ፕሮፌሰር ወይም ዶክተር የሚል የማእረግ ስም ያላቸው ነገር ግን ሕይወታቸዉ በሁሉም እረገድ የተሰበረ እና በሕይወት ድሃ የሆኑ ሰዎችም አሉ። እንግዲያውስ ስኬት የእግዚአብሔርን ምክር ማወቅ እና የምክሩም አካላዊነት መሆን ነዉ። ይህ ማለት እግዚአብሔር አንተን/አንቺን ከመፍጠሩ በፊት በልብ አንቺን/አንተስ ለመፍጠር ያነሳሳውን ምክንያት ማግኘት እና ያንኑ የእግዚአብሔር ፈቃድ በምድር ለይ መፈጸም ማለት ነዉ። ስኬት ይህ ነዉ። እውነተኛ ደስታና ሰላም ሙሉነትም የሚገኘው የእግዚአብሔርን ፈቃድ በመኖር ውስጥ ነዉ። ጻድቅ(በእግዚአብሔር ፈቃድ ውስጥ የሚኖር) እንዳ አንበሳ ያለፍርሃት ይኖራል ተብሎ እንደተጻፈው ነዉ። ተወዳጆች ሆይ የእናንተ ባልሆነ ነገር ለይ ትርፍ ለማግኘት ስትደክሙ ዘመናችሁን እንዳትጨርሱ ዛሬ ንቁ! በእግዚአብሔር ሃሳብ ውስጥ ስትኖሩ የምታጡት አንድም ነገር የለም! ምክንያቱም በመንገዱ ለሚሄዱ እግዚአብሔር እረኛቸው ነዉ። እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ያለውን ዓላማ አግኙ፤ ዓለም ሁሉ ብቃወማችሁ እንኳ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ስለሆነ ብቻችሁን ለመሄድ ወስኑ! ያኔ ስኬት ምን ማለት እንደሆነ በሕይወት ይገባችኋል። @TheDeepThingsOfTheSpirit @TheDeepThingsOfTheSpirit

በዚህኛው ሕይወት ለኢየሱስ ምንም ቦታ የሌላቸው ነገር ግን በሚመጣው ዓለም አብረውት ለመኖር ተስፋ የሚያደርጉ እጅግ ብዙዎች ናቸዉ።እውነታው ግን አሁን ቦታ ያልሰጠሀው ኢየሱስ በሚመጣው ዓለም ቦታ አይ
በዚህኛው ሕይወት ለኢየሱስ ምንም ቦታ የሌላቸው ነገር ግን በሚመጣው ዓለም አብረውት ለመኖር ተስፋ የሚያደርጉ እጅግ ብዙዎች ናቸዉ።እውነታው ግን አሁን ቦታ ያልሰጠሀው ኢየሱስ በሚመጣው ዓለም ቦታ አይሰጥህም! “በሰውም ፊት የሚክደኝ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ይካዳል።” — ሉቃስ 12፥9 @TheDeepThingsOfTheSpirit

“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።” — ኤርምያስ 29፥11 እግዚአብሔር ለአንተ ያለው ሃሳብ አንተ ለራስህ ካለህ የተሻለ ነዉ! በሕይወትህ የእግዚአብሔርን ሃሳብ አግኝ።