Ethiopian pilots (ambitious)👩✈️✈️
Open in Telegram
✈✈We aimed to inspire young students and to provide latest information about aviation✈✈
Show more4 674
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1230 days
Posts Archive
After long waiting here it is
Et sponsored trainee pilot vacancy
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies
@ethiopianpilots
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" የአውሮፕላን ነዳጅ መቆጣጠሪያዎች በጥብቅ ይፈተሹ " - ህንድ
ከአንድ ወር በፊት ህንድ ውስጥ በደረሰ የቦይንግ 787-8 አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ260 ሰዎች ህይወት መቀጠፉ ይታወሳል።
የአደጋው መንስዔ የቦይንግ አውሮፕላኑ ከተነሳ ከሰኮንዶች በኋላ የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ጠፍተው ወደ ሞተሩ የሚደርሰው ነዳጅ መቋረጡ መሆኑን በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የምርመራ ቢሮ (AAIB) ይፋ የተደረገ ቅድመ ሪፖርት አሳይቷል።
አውሮፕላኑ ከተነሳ በሰከንዶች ውስጥ የነዳጅ መቆጣጠሪያ ማብሪያና ማጥፊያዎች ደህነንት ጠፍተው ነዳጅ ተቋርጦ ነበር ተብሏል።
መቆጣጠሪያዎቹ ከመብራት ወደ መጥፋት በመቀየራቸው ወደ ሞተሩ የሚወስደው ነዳጅ መቋረጡ ተመላክቷል። በዚህም አውሮፕላኑ ሊከሰከስ ችሏል።
ሪፖርቱን ተከትሎ ህንድ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ መቆጣጠሪያዎችን በጥብቅ እንዲፈትሹ መመሪያ አወጥታለች።
የአገረቱ ሲቪል አቪዬሽን የህንድ እና አለም አቀፍ አየር መንገዶች በነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ላይ የራሳቸውን ፍተሻ አድርገው ሪፖርት እንዲያቀርቡ መመሪያው እንደወጣ ገልጿል።
አየር መንገዶች የቦይንግ አውሮፕላኖች የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ማብሪያና ማጥፊያዎችን እስከ ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ፈትሸው እንዲያጠናቅቁ ጠይቋል።
" የተቀመጠውን ቀነ ገደብ በጥብቅ መከተል የመብረር ብቃት እና የአፕሬሸኖችን ደህንነት ለማረጋገጥ መሰረታዊ ጉዳይ ነው " ብሏል።
የአሜሪካ የፌደራል አቪዬሽን ባለስልጣን ይፋ የተደረገውን ሪፖርት ተከትሎ " የቦይንግ የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ማብሪያና ማጥፊያዎች ደህንነታቸው የተጠበቀ ነው " ብሏል። መቆጣጠሪያዎቹ በሚቆለፍ መልኩ የተገጠሙ መሆኑን አመልክቷል።
የህንድ አየር መንገድ ፓይለቶች ማህበር ከአደጋው ጋር ተያይዞ በአውሮፕላኑ ፓይለቶች ላይ የሚሰነዘረውን የስም ማጉደፍ ተከላክሎ መግለጫ አውጥቷል።
ማህብሩ " አብራሪዎች በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ማድረግ ያለባቸውን በስልጠናቸው እና በተሰጣቸው ኃላፊነት መሰረት እርምጃ ወስደዋል " ብሏል።
አደጋውን ተከትሎ ከኮክፒት የተገኘ የድምጽ ቅጂ አንደኛው ፓይለት " ለምን አቋረጥከው ? " ሲል የሚሰማ ሲሆን ሌላኛው አብራሪ ደግሞ " አኔ አላቋረጥኩትም " ሲል ይደመጣል።
በህንዱ የአውሮፕላን አደጋ በተአምር ከተረፈው አንድ ሰው በስተቀር ሌሎች ተሳፋሪዎች እና የበረራው አባላት ሁሉ መሞታቸው ይታወሳል።
መረጀው ከቢቢሲ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
+1
#EthiopianAirlines🇪🇹
" አውሮፕላኑ ያለምንም ችግር በሰላም አርፏል። ካረፈ በኋላ ስምንት ተጓዦች የህመም ስሜት ተሰምቷቸው ወዲያውኑ በህክምና ባለሙያዎች ክትትል ተደርጎላቸዋል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን ህንድ ውስጥ በድንገት ለማረፍ መገደዱና በተሳፋሪዎች ህመም ማጋጠሙን " ዘፋይናንሻል ኤክስፕረስ " የተሰኘው የውጪ ሚዲያ ዘግቧል።
ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኑ በሙምባይ ባጋጠመው ችግር " ሰባት ሰዎች መታመማቸው"ን የጠቀሰው ዘገባው፣ ከሰባቱ ሰዎች መካከል "አንዱ በጠና ታሞ ሆስፒታል ገብቷል" ብሏል።
የበረራ ቁጥር ET640 አውሮፕላኑ ክስተቱ ያጋጠመው 33 ሺህ ጫማ ብሎ መጓዝ እንደጀመረ መሆኑ ተመልክቷል። በዚህም " አውሮፕላኑ በድንገት ለማረፍ የተገደደው በአካባቢው በተከሰተው የአየር ፀባይ ነው " ተብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቀ ሲሆን፣ የአየር መንገድ የሕዝብ ግንኙነት ሐና አጥናፉ በሰጡን ቃል፣ " አውሮፕላኑ ወደ ሙምባይ እየበረረ በነበረበት ወቅት የበረራ አባላቱ በካቢን ውስጥ የነበረው ግፊት ቀንሶ አጎኝተውታል " ብለዋል።
" በበረራ ወቅት የበረራ አባላት ባረጋገጡት መረጃ መሰረት ፓይለቱ ደህንነቱ ወደ ተጠበቀ/ለፕሌኑ በሚመች (ከፍታ ቦታ ላይ) በመሄድ አርፏል " ያሉት ሐና፣ " የአደጋ ጊዜ የኦክስጅን ማስኮችን በአግባቡ ተጠቅሟል " ሲሉ ገልጸዋል።
" አውሮፕላኑ ያለምንም ችግር በሰላም አርፏል " በማለት ገልፀው፣ " ካረፈ በኋላ ስምንት ተጓዦች የህመም ስሜት ተሰምቷቸው ወዲያውኑ በህክምና ባለሙያዎች ክትትል ተደርጎላቸዋል" ሲሉም ሁነቱን አስረድተዋል።
" ሰባቱ በዚያው በአየር መንገዱ ህክምና አግኝተዋል። አንዱ ተጎጂ ለተጨማሪ ህክምና ወደ ሆስፒታል ተወስዷል። ነገር ግን ክትትል ከተደረገለት በኋላ ከሆስፒታል ወጥቷል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የአውፕላኑ አብራሪ ሁኔታው ሳይባባስ ፕሮፌሽናል በሆነ መንገድ መቆጣጠሩን ለመረዳት ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Sometimes when things happen unfavourably it is better to say it is for good!
@ethiopianpilots
AI
Guys this thing is going to make us jobless
@ethiopianpilots
What a MIRACLE !
he is a survivor of that tragic 787 crash.
@ethiopianpilots
B787 dreamliner is known for its excellent flight record
@ethiopianpilots
As Dailymail stated Those two britian nationals were one of the victims in this Air india flight
@ethiopianpilots
ቪድዮ ፦ የኤር ኢንዲያ ንብረት የሆነ ቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን (የበረራ ቁጥር 171) ዛሬ የመከስከስ አደጋ አጋጥሞታል።
ከሕንድ አህመዳባድ ከተማ 242 ሰዎችን ጭኖ ወደ ለንደን ለመብረር የተነሳው አውሮፕላን በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በአውሮፕላን ማረፍያው አቅራብያ ተከስክሷል።
በህይወት ሰው ስለመትረፉ ምንም የተባለ ነገር የለም።
Video Credit ፦ Al Arabia
@ethiopianpilots
Repost from 🛫🛫The Pilot's🛬🛬
Yesterday around 8:45 AM, I saw and quickly recorded this Ethiopian Airlines aircraft parked at Toronto Pearson ✈️🇪🇹. The flight came from Addis Ababa, via Rome. I couldn’t get a clear shot because I was driving — but just seeing it there was a proud moment. #EthiopianAirlines #YYZ #ProudMoment #AviationSpotting
Repost from Ethiopian Airlines የኢትዮጵያ አየር መንገድ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ዒድ ሙባረክ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
There are rumors of saying Ethiopian airlines CEO Mesfin Tasew Bekele is about to get retired.
@ethiopianpilots
