en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 479 subscribers, ranking 6 043 in the Religion & Spirituality category and 2 334 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 479 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 530 over the last 30 days and by 23 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 39.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.20% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 666 views. Within the first day, a publication typically gains 1 477 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 33.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 479
Subscribers
+2324 hours
+1447 days
+53030 days
Posts Archive
ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC tv ይጠብቁን!
ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC tv ይጠብቁን!

✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram
✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                              ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

🔔🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!   " ኅየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ "    {"በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ" }  (መዝ 44:16)      በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ በ2014 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን  ተከታትለው  ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ  በአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነትምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ  #የ4ኛ , #የ6ኛ እና #የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች የዕውቅና መስጠት መርሐ ግብር !!! #ታኅሣሥ_8_2015_ዓ_ም  #ከቀኑ_6_30_ሰዓት_ጀምሮ  #በአዲስ_አበባ_ሚሊኒየም_አዳራሽ        #በዕለቱ_የሚኖሩ_ሌሎች_መርሐግብሮች 👇 👉 በ2014 ዓ.ም በክረምት መርሐግብር  በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የተማሩ የተተኪ መምህራን ምርቃት ፤ 👉  በሰንበት ት/ቤቶች  አንድነት ለሥርዓተ ትምህርቱ ማስተማሪያ የተዘጋጁ መጻሕፍት ምርቃት ፤ 👉 በ2015 ዓ.ም የመስቀል ደመራ  በዓል ላይ ትርዒት እና መዝሙር ላቀረቡ የየሰንበት ት/ቤቱ አባላት እና ባለድርሻ አካላት የዕውቅና መርሐ ግብር  ፤  በተጨማሪም የተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች ተሰናድተዋል። #በመርሐግብሩ_ላይ_ይገኛሉ_ተብለው_የሚጠበቁ 👇 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤ ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመሪያው ኃላፊዎች ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና የክፍለ ከተማ ቤተክህነት  የየክፍሉ ኃላፊዎች ፤ የደብራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፤ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አባቶች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግሥት ባለስልጣኖች ፤ የየሰንበት  ት/ቤቱ አባላቶች እንዲሁም ምዕመናን/ት ይገኛሉ። እርስዎም በዚህ ልዩ መርሐግብር ላይ ታኅሣሥ 8/2015 ከቀኑ 6:30 ሰዓት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ ተገኝተው የመርሐግብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!!!            #የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት 🔔🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔

ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC TV ይከታተሉን
ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC TV ይከታተሉን

ዛሬ ማታ 2፡00 ላይ EOTC TV ላይ ይጠብቁ!
ዛሬ ማታ 2፡00 ላይ EOTC TV ላይ ይጠብቁ!

15. በየአህጉረ ስብከቱ ያለውን መንፈሳዊና ማህበራዊ አገልግሎት ክንውን የገመገመው ምልዓተ ጉባኤ ለአብያተ ክርስቲያናት መልካም አስተዳደር ዕድገትና ለሰላም መስፈን ትኩረት በመስጠት በአንዳንድ አህጉረ ስብከት የብፁዓን አባቶች ዝውውርና ምደባ አድርጓል፡፡  16. በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኙት የሶሪያ አንጾኪያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የግብጽ አሌክሳንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የቂልቅያ ሊባኖስ መንበር የሆኑት እነዚህ ሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት በግብፅ ሀገር ከጥቅምት 8-10 በአውሮፓውያን አቆጣጠር ከኦክቶበር 18 እስከ 20 ድረስ ባካሄዱት የመሪዎች ጉባኤ በሰጡት መግለጫ በቅድሰት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ገዳም ይዞታችን አስመልክቶ የሰጡት አሳዛኝ መግለጫ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በትኩረት ተመልክቶታል፡፡ እነዚሁ አብያተ ክርስቲያናት በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የቤተ ክርስቲያናችን በሆነ የይዞታ ላይ የሰጡት የተሳሳተ መግለጫ የቤተ ክርስቲያናችንና የአገራችንን ኢትዮጵያ ክብር የሚነካ ስለሆነ ጉባኤው በእጅጉ ተቃውሞታል፡፡ አብያተ ክርስቲያናቱም የሰጡትን መግለጫ መልሰው እንዲያጤኑትና የማረሚያ መግለጫ እንዲሰጡ የኢፌዲሪ መንግሥትም በጉዳዩ ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግበት ጉባኤው ጥሪውን ቅርቧል፡፡    17. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከጥቅምት 21-27/2015 ዓ.ም. ድረስ ለሰባት ዕለታት ለምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ማስፈጸሚያ ባዘጋጀው የአንድ ሱባዔ የጸሎት ሳምንት፡- -       ለአገራችንና ብሎም ለአለማችን ፍጹም ሰላም፣ -       ለሕዝቦች አንድነትና ሰላማዊ ኑሮ መገኘት፣ -       በጦርነት ምክንያት ከቄያቸው ለተፈናቀሉና -       በልዩ ልዩ ወረርሽኝ በሽታ ለተያዙ ምሕረትና ጤና እንዲያገኙ፣  እንዲሁም በጦርነትና በማንኛውም አጋጣሚ ውድ ሕይወታቸው ያጡ ወገኖቻችን እረፍተ ነፍስን እንዲሰጣቸው ሁሉን ቻይ ወደሆነው እግዚአብሔር በሱባኤ የሰነበተ ሲሆን በቀጣይም ለአገራችንና ለሕዝባችን ፍጹም ሰላም መገኘት መላው ካህናትና ምእመናን በጸሎት እንዲተጉ ጉባኤው አሳስቧል፡፡ በመጨረሻም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በስብሰባ በሰነበተባቸው ዕለታት በቤተ ክርስቲያናችን የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ላይ በስፋት በመነጋገር መንፈሳዊ አገልግሎቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልማታዊው ተግባር ትኩረት ተሰጥቶት እንዲከናወን ለህብረተሰቡ ሊደረግ የሚገባው ማህበራዊ ጉዳዮች አስፈላጊው ክትትል እንዳይለያቸው በተለይም በአገራዊ ሰላምና አንድነት ላይ በሁሉም አካባቢዎች የተጠናከረ ሥራ እንዲሠራ በማስገንዘብ ከጥቅምት 11 ቀን 2015 እስከ ጥቅምት 25 ድረስ ሲያካሂድ የቆየውን ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት ዘግቷል፡፡                                             እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር !!! አሜን፡፡ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥቅምት ፳፭ ቀን 2015 ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ ኢትዮጵያ                                                                 ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                              ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ ከጥቅምት 11 ቀን 2015 እስከ ጥቅምት 25 ድረስ ሲያካሂድ የቆየውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት ዘግቷል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ቅዱስ ሲኖዶስ በርዕሰ መንበሩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አማካይነት ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠ ሲሆን የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ይቀርባል። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !!! ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ ፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የመክፈቻውን ሥርዓተ ጸሎት ከፈጸመበት ከጥቅምት 11 ቀን 2015ዓ.ም. ጀምሮ የተለመደውን ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡ ምልዓተ ጉባኤው ለቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ዕድገት ለአገራችን ማህበራዊና ልማታዊ ክንውን እንዲሁም ለመላው ሕዝባችን ሰላምና አንድነት ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡             በዚሁ መሠረት፡- 1.የዚሁ የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መከፈቱን በማስመልከት የተደመጠው የመክፈቻ ንግግር 2.የሕዝባችንና የቤተ ክርስቲያናችን ሰላም ተጠብቆ እንዲኖር ማድረግ እንዲቻል ፣ 3.በአገራችን በሰሜኑ ክልል በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ከቀያቸው ስለተፈናቀሉና በአጠቃላይ በችግር ላይ ስለሚገኙ ወገኖቻችን መደረግ ስለሚገባው እገዛ፣ 4.በቀጣይም የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ዕድገት ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ ምልዓተ ጉባኤው በዚሁ ላይ በስፋት ተነጋግሮ ለተግባራዊነቱ የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን እንዲወጡ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ 5.የ2015ዓ.ም. የመንበረ ፓትርያርክ አለም አቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ያሳለፈውን የጋራ መግለጫ በመመርመርና አስፈላጊ ማሻሻያዎችን በማድረግ የበጀት ዓመቱ የሥራ መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው አጽድቋል፡፡ 6.የ2015ዓ.ም. የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ የዓመቱን በጀት ድልድል አስመልክቶ ጉባኤው በስፋት ከተነጋገረ በኋላ የቀረበውን በጀት በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡  7.ከ200 7ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ላይ የነበረውን ሕገ ቤተክርስቲያን ወቅቱን በዋጀ መልኩ በማስጠናት መልካም አስተዳደርን ሊያሰፍን በሚችል ሁኔታ ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ ላይ በመነጋገር ማሻሻያዎችን በማድረግ ረቂቅ ደንቡን አጽድቋል፡፡ በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡                              8.የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ካህናትና ምእመናን የሚያጋጥሟቸው ችግሮች ቀኖና ቤተክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ በመንፈሳዊ ዳኝነት መታየትና ፍትሕ ማግኘት እንዲችሉ ለማስቻል በባለሙያ ተዘጋጅቶ የቀረበው የመንፈሳዊ ፍ/ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ በምልዓተ ጉባኤ ጸድቋል፡፡ ከዚሁ ጋር ለቤተ ክርስቲያኒቱ ማህበራዊና መንፈሳዊ የሥራ ሂደት ጠቃሚ የሆኑ ልዩ ልዩ ረቂቅ ደንቦችን መርምሮ በማጽደቅ በሥራ ላይ እንዲውሉ ወስኗል፡፡ 8.በቤተ ክርስቲያናችን ሕጻናትና አስተዳደግ ድርጅት አገልግሎት የሚገኘው ምግባረ ሠናይ ሆስፒታል በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል የማሻሻያ ሥራ እንዲሠራ በተጨማሪም በቤተ ክርስቲያናችን በምሥራቅ አፍሪካ ውስጥ የመጀመሪያ የሆነ ታላቅ ሆስፒታል እንዲገነባ የቀረበውን ጥናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አጽድቋል፡፡ 9.በአገራዊ ሰላምና አንድነት ላይ የተነጋገረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሰላም ለአገራችን ሕዝቦች አንድነትና ለቀጣይ በልማታዊ እድገት የበለፀገች ኢትዮጵያን ለማየት መሠረት መሆኑን ሁሉም ተገንዝቦ አገራዊ እርቀ ሰላም እንዲወርድ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን አቅርቧል፡፡ ከዚሁም ጋር አገራዊ ሉአላዊነትን በሚዳፈር መልኩ እየታየ ያለውን የውጭ መንግሥታት ጣልቃ ገብነት እንዲቆም ጉባኤው አሳስቧል፡፡ 10.በሰሜኑ አገራችንም ሆነ በውጭው ዓለም አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት የቤተ ክርስቲያናችን ማዕከላዊ አሠራር ላይ እያሳዩት ያለው አካሄድ ለቤተ ክርስቲያናችንም ሆነ ለአገራዊ አንድነታችን መጠበቅ ሲባል እንደገና በሰከነ መንፈስ ታይቶ ወደነባሩ ማዕከላዊ አስተዳደርና አሠራር እንዲመለሱ ጉባኤው ጥሪውን ያቀርባል፡፡  በቤተ ክርስቲያናችን ስብከተ ወንጌል እንዲስፋፋ መልካም አስተዳደር በሁሉም አቅጣጫ እንዲሰፍን አገራዊ አንድነትና ሰላም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አህጉረ ስብከት ከምንግዜውም በላይ ተጠናክረው እንዲሠሩ ለማስቻል ምልዓተ ጉባኤው በሰፊው መክሮ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ 10.የቤተ ክርስቲያኒቱ አእምሮአዊ ሀብት ንብረትና የቱሪዝም ቅርሶቻችንን አስመልክቶ በቀረበው የባለሙያ ጥናት ላይ የተነጋገረው ምልዓተ ጉባኤ ጥናቱን በማጽደቅ በተግባር እንዲተረጐም ወስኗል፡: 11. አገራችንን በልማት አሳድጐ ሕዝባችንን ከረሀብና ከድህነት ለማላቀቅ በማሰብ ግንባታው ከዓመታት በፊት ተጀምሮ በአሁኑ ጊዜ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ሕዝባችን እየተረባረበ ያለበት የዓባይ ግድብ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እስከሚደርስ በቤተ ክርስቲያናችንም ሆነ በሁሉም ዘንድ አስፈላጊው ድጋፍና ትብብር እንዲቀጥል ምልዓተ ጉባኤው ጥሪ አቅርቧል፡፡ 12.እስከአሁን ድረስ በቤተ ክርስቲያናችን የሚገኙ መንፈሳዊ ኮሌጆች ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑን በመገንዘብና ለትምህርት አስፈላጊው ትኩረት እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ባስቀመጠው አቅጣጫ ተጨማሪ ከሦስት ያላነሱ መንፈሳዊ ኮሌጆች መጨመራቸው ሥራም መጀመራቸውን ጉባኤው ተመልክቶ ኮሌጆቹ በቀጣይም በእቅድና የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮ በጠበቀ መልኩ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስገንዝቧል፡፡ 13. ልማት ለቤተ ክርስቲያናችን ብሎም ለአገራችን እድገት ለሕዝባችን የኑሮ መሻሻል በእጅጉ አስተዋጽኦው የጐላ መሆኑን በመገንዘብ በቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓመታዊ በዓላትን ለማክበር ለሚገኙ ምዕመናን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሠረታዊ ልማት ለመተግበር እንዲቻል ጉባኤው ተነጋግሮ ለተግባራዊነቱ የወደፊት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡ 14.   ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው ጦርነት አገራችንና ሕዝባችን ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ቤተ ክርስቲያናችንም የዚህ ችግር ገፈት ቀማሽ ሆና ካህናቶቿና ምእመናን ተከታዮቿ ለሞትና ለስደት መዳረጋቸው አብያተ ክርስቲያናት መፍረሳቸውና መቃጠላቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ሆኖም በአሁኑ ጊዜ ይኸው ጦርነት እንዲያበቃ አገራዊ ሰላምና አንድነት እንዲጠበቅ ትኩረት ባደረገ መልኩ በደቡብ አፍሪካ የተደረሰውን ስምምነት ቤተ ክርስቲያናችን በእጅጉ የምትደግፈውና በተደረሰው ስምምነት መሠረት ሰላሙ ፍጻሜ እንዲያገኝ የበኩሏን አስተዋጽኦ የምታበረክት ሲሆን ሁሉም አካል ለሰላሙ መገኘት በትኩረት እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ በኦጽንኦት ያስገነዝባል፡፡ ይህ በቅዱስ ሲኖዶሱ ሁልጊዜም በጉጉት ሲጠበቅ፣ ጸሎት ሲጸለይበትና የሰላም ጥረት ሲደረግበት የቆየ በመሆኑ አሁንም በየአቅጣጫው አገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 መልካን ምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው? (ሮሜ.10:15)። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
+1
ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 መልካን ምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው? (ሮሜ.10:15)። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በወቅታዊ ጉዳይ አባታዊ የደስታ መልእክት አስተላለፉ።

ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 መልካን ምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው? (ሮሜ.10:15)። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በወቅታዊ ጉዳይ አባታዊ የደስታ መልእክት አስተላለፉ።

[ Album ] "ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 መልካን ምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው? (ሮሜ.10:15)። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በወቅታዊ ጉዳይ አባታዊ የደስታ መልእክት አስተላለፉ።

"ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 መልካን ምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው? (ሮሜ.10:15)። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏�
+1
"ሠናይ እገሪሆሙ ለእለ ይዜንዉ ሠናየ ዜና" 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 መልካን ምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው? (ሮሜ.10:15)። 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በወቅታዊ ጉዳይ አባታዊ የደስታ መልእክት አስተላለፉ።

"በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ" ጠቢቡ ሰለሞን ለወጣቶች በሙሉ ዘላለማዊ መመሪያ የሚሆን የሕይወት ቃል ታናግሯል፡፡ ቃሉም " የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ " የሚል ነው፡፡ /መክ ፲፪፥፩/ "በጉብዝህ ወራት" ያለው ወጣቶችን ለመጥቀስ ፈልጎ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ወጣቶች "ጎበዞች" ይባላሉ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በመልእክቱ "ጎበዞች ሆይ ብርቱዎች ስለሆናችሁ የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር ክፉውንም ስላሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ፡፡" ብሎ በጻፈ ጊዜም ወጣቶች "ጎበዞች" እንደሚባሉ ማጠናከሪያ ሰጥቷል፡፡ ፩ዮሐ፫፥፲፬ "ክፉውንም ስላሸነፋችሁ ማለቱም ' ክፉ' የሚባለው የወጣትነት ምኞት ስላሸነፋችሁ ማለቱ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ሽሽ " በማለት የክርስትና ልጁ ጢማቴዎስን እንደመከረው የወጣትነት ምኞት ክፉ ይባላልና። ወጣቶች ፈጣሪያቸውን ማሰብ እንደሚኖርባቸው ተለይተው የተጠቀሱት ለምንድን ነው? ፈጣሪን ማሰብ ማለትስ እንዴት ነው? በመሠረቱ ፈጣሪን ማሰብ የሚኖርባቸው ወጣቶች ብቻ አይደሉም፡፡ ልጆችም ሆኑ አረጋውያን ፈጣሪን ማሰብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጠቢቡ ሰለሞን ግን ወጣቶችን ለይቶ ፈጣሪን ማሰብ እንዳለባቸው የተናገረበት ምክንያት አለው ይኸውም ከልጆች ከአረጋውያን ይልቅ ወጣቶች እግዚአብሔርን እዲረሱ የሚያደርጋቸው ብዙ ነገር ስላለ ነው፡፡ 👉 እግዚአብሔርን ማሰብ ማለት ሕጉንና ትእዛዙ በቤት ሲቀመጡ፣ በመንገድ ሲሄዱ፣ ሲተኙና ሲነሱም መጫወት ማለት ነው፡፡ /ዘዳ ፮፥፬-፱/ በተጨማሪም ቃሉን በልቡና መያዝና በፍጹም ልብና በፍጹም ነፍስ እግዚአብሔርን መውደድ ማለት ነው፡፡ በዚህም መልኩ ፈጣሪን ማሰብ ይገባል፡፡ ለምን ቢባል? ነቢዩ ዳዊት "እግዚአብሔርን የሚረሱ ይጠፋሉ" ብሏልና፡፡ 👉 ፈጣሪን ማሰብ ማለት "ሕጉን በቀንና ሌሊት ያስባል" በማለት ቅዱስ ዳዊት እንደተናገረው የእግዚአብሔርን ሕግ በደስታ ማሰብ ማለት ነው፡፡ /መዝ ፩፥፪/ ተግባር የተለየው ማሰብ ብቻውን ምግባር የተለየው እምነት ሆነ ማለት ነው፡፡ ምግባር የተለየው እምነት ደግሞ ነፍስ እንደተለየው ሥጋ የሞተ መሆኑ በግልጽ ተነግሯል፡፡ /ያዕ ፩፥፳፮/ 👉 እግዚአብሔርን ማሰብ ማለት በሥራ በሚገለጥ ነገር እግዚአብሔርን ማክበር ማለት ነው እንጂ በቃልና በአንደበት ብቻ አይደለም፡፡ እግዚአብሔርን አስበዋለሁ ማለት በሥራ ካልተገለጠ ምንም አይጠቅምም፡፡ ሚስት ለባሏ "ሁል ጊዜ እስብሃለሁ እፈቅሃለሁ ከራሴ አብልጬ እወድሃለሁ" ብትለው ነገር ግን ባሏ የሚወደውን እንዱንም ባትሠራ "እወድሃለሁ" ማለቷ ብቻ ባሏን ሊያስደስተው ይችላልን? ፈጣሪንም ብዙ ትእዛዛቱን ወደ ኋላ ጥሎ "አስብሃሉ " ማለት ብቻ ምንም አያስደስተውም፡፡ ሩቅ ሀገር ያለ ወዳጃችንን በደስታው ጊዜ እንኳን ደስ ያለህ በኀዘኑ ጊዜ እግዚአብሔር ያበርታህ ለማለት ካልጣርን የሚያስፈልገውን ሁሉ የማንረዳው ከሆነ "ሁል ጊዜ አስብሃለሁ" ማለት ብቻ ምን ይጠቅመዋል? በዚህ መልኩ መራራቅ የሞት ያህል ነውና ያረሳሳል፡፡ ፍቅርን ያጠፋል እንጂ መተሳሰብን አይገባም፡፡ ፈጣሪንም ቢሆን ጠዋት ማታ ካልጸለዩ፣ ካላመሰገኑት፣ ካልለመኑት፣ ሕጉን ካላከበሩ "አስብሃለሁ" ቢሉት ጨርሶ በዚህ አይደሰትም፡፡ የያዕቆብ ልጅ ዮሴፍ የጠጅ አሳላፊዎቹን አለቃ "ነገር ግን በጎ ነገር በተደረገልህ ጊዜ እኔን አስበኝ" ሲል ምን ማለቱ ነበር? "ምሕረትን አድርግልኝ፤ የእኔን ነገር ለፈርዖን ነግረህ ከዚህ ቤት አውጣኝ" በማለት በግፍ ከተጣለበት ወኅኒ እንዲያስወጣው መናገሩ አልነበረም? /ዘፍ፵፥፲፬/ ስለዚህ "በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ" ማለትም አንድ ተገቢ ነገር ሥራ ማለት ነው እንጂ በሕሊናህ ፈጣሪህን አሰላስለው ማለት ብቻ እንዳልሆነ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ ከጌታችን ከመድኃታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቀኝ ተሰቅሎ የነበረው ሽፍታ "አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ" ሲል ምን ማለቱ ነበር? ጌታ የማያውቀው ሆኖ ራሱን ማስተዋወቁ ነበርን? ወይስ ፈጣሪ በመጣ ጊዜ "አስበኝ ብለኸኝ ነበር" እንዲለው ብቻ ነበርን? ይቅርታ እንዲያደርግለትና መንግሥቱን እንዲያወርሰው መለመኑ እንደነበር አያጠራጥርም፡፡/ሉቃ፳፫፥፵፪-፵፫/ ታዲያ የ"ማሰብ" ትርጓሜ እንዲህ ከሆነ "በጉብዝህ ወራት ፈጣሪህን አስብ" ሲባልም ሕጉን ጠብቅ፣ ጸልይ፣ አመስግን ማለት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "አቤቱ በመንግስትህ በመጣህ ጊዜ አስብኝ" በማለት ለለመነው ወንበዴ "እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ" ብሎ የመለሰለት መልስ "ማሰብ" የሚለውን ቃል በሌላ መልኩ እንድናየው ግድ ይለናል፡፡ "አስበኝ" ላለው ወንበዴ "ከእኔ ጋር ትኖራለህ" ካለው "ማሰብ" ማለት ከራስ ጋር አብሮ ማኖር የሚል ትርጓሜ እዳለው ያስረዳል፡፡ ፊያታዊ ዘየማንም /በቀኝ የተሰቀለው ሽፍታም/ "አስበኝ" ሲል "ከራስህ ጋር አኑረኝ" ማለቱ እንደበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "ከእኔ ጋር ትኖራለህ" በማለት ከመለሰለት መልስ እንገነዘባለን፡፡ ከላይ በተሰጠው ሐተታ መሠረት "ማሰብ" ማለት "ከራስ ጋር አብሮ ማኖር" ማለት ከሆነ "በጉብዝህ ወራት ፈጣሪህን አስብ" ማለት ምን ማለት ሊሆን ይችላል? ፈጣሪ ካንተ የማይለይበትን ሥራ አድርግ ማለት ነው፡፡ ማለትም ሰው ከፈጣሪው የሚለየው ኃጢአት ነውና ከኃጢአት ሽሽ! /ኢሳ ፶፱፥፪/ በአንጻሩ ደግሞ መልካም ሥራን ሁሉ አድርግ፡፡ በደልህን ሁሉ አምነህ ንስሐ ግባና ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀበል፡፡ በዚህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ይሆናል ማለት ነው፡፡ /ዮሐ ፮፥፶፮/ ይህ ሁሉ አድርገህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ሲሆን "በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ" የሚለውን ትእዛዝ በእውነት የፈጸምክ ትሆናለህ፡፡ ከዲያቆን በፍቃዱ ከመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ወቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ኆኅተ መንግስተ ሰማያት ሰ/ት/ቤት

ለ፫ተኛ ጊዜ ቅብዓ ሜሮን የማፍላት ሥርዓተ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ እየተከናወነ ይገኛል። ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ቤተክርስቲያናችን ለሚጠመቁ ምዕመናንን በቅብዓ ሜሮን አማካኝነት ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ታሳድራለች። ተጠማቂው ቅብዓተ ሜሮን በመቀባት መንፈስ ቅዱስ ያድርበታል። የቃል ኪዳኑ ታቦት (ፅላት) ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በመንበረ ክብሩ ላይ በመቀመጥ አገልግሎት እንዲሰጥ አስቀድሞ በዚህ በተቀደሰ ቅብዓ ሜሮን ተባርኮ መሰየም አለበት ። ቤተ ክርስቲያን ከታነጸ በኋላ ፤ በውስጡ ሙሉ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከመስጠቱ በፊት በቅብዓተ ሜሮን መባረክ አለበት። በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት መሪነት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅብዓ ሜሮን የማፍላት የጸሎት መርሐ ግብር እየተካሄደ ይገኛል። ቀድሞ ከግብፅ ተዘጋጅቶ ይመጣ የነበረው ቅብዓ ሜሮን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲዘጋጅ ይህ ለ፫ ተኛ ጊዜ ነው። ዛሬ ከሌሊቱ ፲ ሰዓት በተጀመረው ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ምእመናንና ካህናት ለ፯ ተከታታይ ቀናት በጸሎት እንዲተባበሩ ቀደም ብሎ በቅዱስነታቸው ጥሪ ቀርቧል። ይህንኑ አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፣ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ባስተላለፉት መልዕክት ቅብዓ ሜሮን ዝግጅቱን ተከትሎ በሀገራችን እየደረሰ ላለው መከራ እንዲያበቃ የጸሎት አዋጅ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ መታወጁን ገልጠዋል። ገዳማትና አድባራቱ በሙሉ በጸሎት እንዲተባበሩም ጥሪ አቅርበዋል። ሥርዓቱ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት ከጥቅምት ፳፩ እስከ ፳፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ድረስ ይከናወናል። EOTC TV

ኃሢሠ አእምሮ ማክሰኞ 22/02/2014 ዓ.ም ምሽት 2፡00 EOTC Tv ላይ በ፯ ክፍል ተማሪዎች መካከል የሚደረገውን ውድድር ይከታተሉ:: ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/
ኃሢሠ አእምሮ ማክሰኞ 22/02/2014 ዓ.ም ምሽት 2፡00 EOTC Tv ላይ በ፯ ክፍል ተማሪዎች መካከል የሚደረገውን ውድድር ይከታተሉ:: ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/