en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 479 subscribers, ranking 6 043 in the Religion & Spirituality category and 2 334 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 479 subscribers.

According to the latest data from 30 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 530 over the last 30 days and by 23 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 39.14%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 10.20% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 666 views. Within the first day, a publication typically gains 1 477 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 33.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 01 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 479
Subscribers
+2324 hours
+1447 days
+53030 days
Posts Archive
Watch "ፈለገ ጥበብ Wisdom Spring ወራዙት ዓምድ እኛ እና አባቶቻችን ከመምህር ቢተወደድ ወርቁ ጋር የአባቶቻችን ማኅበራዊ መስተጋብር" on YouTube https://youtu.be/lKHltFHCmwA

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የ፮ኛ ቀን ዋና ዋና ዜናዎች ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ (ጥቅምት 19 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) 6ኛ ቀኑን በያዘው የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ከሰዓት በፊት በነበረው ውይይት የተለያዩ ውሳኔዎችን ጉባኤው መወሰኑን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ገልጸዋል። ሦስቱ ዋና ዋና ውሳኔዎችም የሠራተኞች መተዳደሪያ ደንብን ፣የመጋቤ ብሉይ አእመረ አሸብር የይቅርታ ጉዳይን እና የባሕርዳር ጽርሐ ጽዮን መንፈሳዊ ኮሌጅ ጥያቄን የተመለከቱ ሲሆኑ በሚከተለው መልኩ ቀርበዋል። • ቅዱስ ሲኖዶስ በትናንትው ዕለት በንባብ ሲሰማ የዋለውን የሠራተኞች መተዳዳሪያ ደንብ ከማስተካከያዎቹ ጋር በሙሉ ድምጽ መጽደቁን ገልጸው ደንቡ የሠራተኞችን መብትና ግዴታ እንዲሁም የአገልጋዮችን ትንሹን የአገልግሎት ዕድሜና የጡረታ ዕድሜ ጣሪያ ያስቀመጠ መሆኑን አብራርተዋል። •በሌላ በኩል በምንፍቅና ምክንያት ጥቅምት ፳፻፲፩ ዓ/ም በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው ተለይተው የነበሩትና ይቅርታም ከጠየቁ በኋላም በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት በቀኖናና በጽሑፍና በቃል ያሳቱትና ያሳቱትን በሚዲያ ቀርበው ይቅርታ ሲጠይቁና ሲያስተምሩ እንደነበሩ ገልጾ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት በመምህር አእመረ ላይ ከዚህ ቀደም ያስተላለፈበቸውን ውግዘት በማንሳት ይቅርታቸውን ተቀብሏቸዋል ብለዋል ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊው ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) በሰጡት መግለጫ። • በተጨማሪም በዛሬው ከሰዓት በፊት ውሎው የመንፈሳዊ ኮሌጆች ይቋቋምልን ጥያቄዎች አጀንዳ መነሳቱን ጠቅሰው በዚህም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ያቀረበውን የባሕርዳር ጽርሐ ጽዮን መንፈሳዊ ኮሌጅ መስፈርቱን በሟሟላቱ እንዲቋቋም ጉባኤ ውስኗል ብለዋል፣ የሌሎች ጥያቄዎችን ከሰኞ ጀምሮ መታየታቸው እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል። በመጨረሻም ጉባኤው ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ በዕድሜ የገፉ ብፁዓን አባቶች ትጋትና ጸሎት የቀጠለ መሆኑን ጠቅሰው ሊቃውንት ምዕመናንና ምዕመናት በጸሎት ጉባኤውን እንዲያስቡ ተማጽነዋል ሲል EOTC TV ዘግቧል።

ቅዱስ ሲኖዶስ በሦስተኛ ቀን ጉባኤ ውሎው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ ሰነድ ተወያይቶ ማጽደቁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ገለጹ። ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐ
ቅዱስ ሲኖዶስ በሦስተኛ ቀን ጉባኤ ውሎው ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ ሰነድ ተወያይቶ ማጽደቁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ገለጹ። ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጴጥሮስ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 16 ቀን 2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሦስተኛ ቀንን ውሎ በተመለከተ ዕለታዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ብፁዕነታቸው በሰጡት ገለጻ ትላንት በንባብ የተሰማውና ብዙ ውይይት የተደረገበት አጀንዳ የሕገ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እንደነበረ ገልጸው ምልዓተ ጉባኤው እያንዳንዱን ሐሳብ በተናጠል ካየና ከመረመረ በኋላ ማስተካከያ በማድረግ ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለሦስተኛ ጊዜ መጽደቁ ተገልጿል። ከ80ሺ በላይ መንፈሳዊ ማኅበራት በቤተ ክርስቲያናችን እንዳሉ የሚነገር መሆኑን የጠቀሱት ብፁዕነታቸው ለአሠራር እንዲመች የማኅበራት ማደራጃና ማስተባበሪያ መምሪያ የሚል አዲስ መዋቅር ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ምልዓተ ጉባኤው ስምምነት ላይ መደረሱንም አብራርተዋል። በሌላ በኩል በሊቀ ጳጳስ የበላይነት የሚመሩና በመንበረ ፓትርያርክ ሥር የሚገኙ ድርጅቶችና ዩኒቨርሲቲ ሒሳባቸውን በራሳቸው ፊርማ እንዲያንቀሳቅሱ ፤ በየሦስት ወሩም ለዋና መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት እንደሚያደርጉና እንደያሳውቁም መወሰኑን ገልጸዋል። አያይዘውም በነገው ዕለት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ደንብ ፣ የማኅበራት ማደራጃ ደንብ እና የመንፈሳዊ ፍርድ ቤት ደንብ የሚታዩና ይሁንታም ሲያገኙ የሚጸድቁ ይሆናል ብለዋል። የሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በየዕለቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሎን እየገለጹ መሆኑ ከዘገባው ተጠቁሟል። ዘገባው የኢኦተቤ ቴቪ ነው፡፡

ዛሬ ማታ 2፡00 በEOTC Tv ይጠብቁን!
ዛሬ ማታ 2፡00 በEOTC Tv ይጠብቁን!

ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ******* ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም """"""""""""""""""""""""""""""" አዲስአበባ -ኢትዮጵያ ****** የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚያካሂድ ይታወሳል፡፡ይኸውም በወርኃ ጥቅምትና ግንቦት ነው፡፡ በእነዚህ ወራት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ምልዓተ ጉባኤውን በማካሔድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁለንታዊ ጉዳዩች ወይም መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶች ላይ በመምከር ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን እንደሚያስተላልፍ ይታወቃል። ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያካሒዳቸው እነዚህ ጉባኤያት በተረጋጋ፣ በሰከነና በተሳካ መልኩ መካሔድ ይችላሉ ዘንድ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ማድረግ ይኖርባቸዋል። በተለይም በተለምዶ ጉባኤው በሚካሔድበት ወቅት ልዩ ልዩ አቤቱታዎችን ሕጋዊውን አሠራር ባልጠበቀ መልኩ በግልና በቡድን በመሆን በቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትና በብፁዓን አባቶች ማረፊያ ቤት በመገኘት ማቅረብ ሕጋዊነት የሌለው ተግባር ከመሆኑም በላይ የቅዱስ ሲኖዶስን ጉባኤን የሚያውክ ነው፡፡ በዚህም የተነሣ ፍጹም ተቀባይነትን የሌለው ተግባር መሆኑን ሁሉም ሊያውቀው ይገባል፡፡ አቤቱታና ጥያቄዎች ካሉም በሕጋዊው የቤተ ክርስቲያናችን አሠራር መሠረት መዋቅራዊ አሠራርን በጠበቀ መልኩ ማቅረብ ተቀባይነት ያለውና ሕጋዊ አሠራር ነው፡፡ በመሆኑም ማንኛውም ሕጋዊ አቤቱታና ጥያቄ ያለው ግለስብም ይሁን ተቋም ይህንን አሠራር መሠረት በማድረግ ጥያቄና አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል። ይህም የሚሆነው ግን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ የሚካሔድበትን ወቅት ጠብቆ መሆን የለበትም። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጉባኤውን በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የሚያካሒደው በቀኖና ቤተ ክርስቲያንና በሕጋዊው አሠራር በተቀረጹ አጀንዳዎች መሠረት መሆኑ ይታወቃል፡፡ቅዱስ ሲኖዶሱ የመወያያ ነጥቦች ብሎ በሚያጸድቃቸው የስብሰባ አጀንዳዎች ላይ ብቻ መሆኑን መረዳትም ያስፈልጋል፡፡ እናም መላው ሕዝበ ክርስቲያን በሕግና በሥርዓት የሚካሔደውን ጉባኤ ሊያውክ ከሚችል ተግባራት ራሱን በማራቅ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በተሳካ መልኩ እንዲከናወን በጸሎት ፈጣሬ ዓለማትን በመለመን ሊተጋ ይገባዋል። ይህንን መሠረት በማድረግም የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ሰኞ ጥቅምት ፲፬ ቀን ፳፻ ፲ ወ ፭ ዓ.ም መካሔድ የሚጀምረውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን ተከትሎ የሚከተሉትን መመሪያዎች አውጥቷል። ፩ኛ. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚካሔድባቸው ቀናቶች ሁሉ ማንኛውም አቤቱታ አቀርባለሁ የሚል አካል ልዩ ልዩ ጽሑፎችን፣ በግልና በቡድን ሆኖ ማቅረብ የማይቻል መሆኑን ተገንዝቦ የምናቀርበው አቤቱታ አለን የሚል አካልም ደረጃውን ጠብቆ ለሚመለከተው አካል እንዲያቀርብ። ፪ኛ. ማንኛውም ሰው በአቤቱታ ሽፋን ለአድማ የተዘጋጁ ጽሑፎችና ማመልከቻዎችን ይዞ በቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትም ሆነ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው። ፫ኛ. አቤቱታ እናቀርባለን በሚል ሰበብ ልዩ ልዩ ጽሑፎችን ይዞ በግልም ሆነ በቡድን ብፁዓን አባቶች ቤት በመገኘት ወረቀቶችን መበተን በበር ሥር ማስገባትና አላስፈላጊ ቅስቀሳ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ከመሆኑም በላይ የቅዱስ ሲኖዶስን ጉባኤ የሚያውክ ተግባር በመሆኑ ይህን ድርጊት የሚፈጽሙ ሁሉ ከአድራጎታቸው እንዲታቀቡ ከወዲሁ እናሳስባለን። ፬ኛ. ጉባኤው በሚካሔድበት ወቅት ለሥራ ጉዳይ እንዲንቀሳቀሱ ከተፈቀደላቸው የሥራ ኃላፊዎች ውጪ ያለምንም ሥራ በጉባኤው አዳራሽና አካባቢው እንዲሁም ብፁዓን አባቶት ለእረፍት በሚወጡበት ጊዜ ብፁዓን አባቶችን ተከታትሎ ማረፊያ ቤታቸው መሄድና ማወክ የተከለከለ ነው። ፭ኛ. የጉባኤው ውሎን በተመለከተ አንዳንድ የመገኛኛ ብዙኀን ተቋማት መሠረተ ቢስ መረጃዎችን በመዘገብ ሕዝበ ክርስቲያኑን ከማደናገር እንዲቆጠቡ እያሳሰብን፤ የጉባኤውን ውሎ በማስመልከት አስፈላጊ በሆነ ጊዜ ሁሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊ አማካኝነት በቤተ ክርስቲያናችን መገናኛ ብዙኀን የሚገለጽ ስለሆነ ትክክለኛውን መረጃ ከቤተ ክርስቲያናችን መገናኛ ብዙኀን ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን። ፭ኛ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሰከነና በተረጋጋ መልኩ ተከናውኖ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መላው ኦርቶዶክሳዊ ተዋሕዶ ምዕመናን በጸሎት በመትጋት ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ጥሪውን ያስተላልፋል ። በመጨረሻም ይህ የቤተ ክርስቲያናችንን መንፈሳዊ ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስኬቶችና ቀጣይ መከናወን የሚገባቸውን ተቋማዊ ጉዳዩችን በመመልከት ውሳኔ የሚተላለፍበት ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ መከናወን ይችል ዘንድ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ መላው ሕዝበ ክርስቲያንና ወጣቶች በጸሎት ከምታደርጉት ትጋት በተጨማሪ ለጉባኤው መሳካትና ውጤታማነት እንዲሁም ለዚህ መመሪያ መከበር የሚጠበቅባችሁን ሁሉ እንድታበረክቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት መልእክቱን ዳግም ያስተላልፋል። "ልዑል እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክልን፤" አሜን የኢ /ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ጥቅምት ፲፩ቀን ፳፻፲ወ፭ዓ.ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

ነገ ከቀኑ 10 ሰአት በኢኦተቤ ቴቪ ላይ ይጠብቁን፡፡ ልዩ የተሰጥኦ መርሃግብር ይዘንላችሁ እንቀርባለን፡፡

Watch "የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ክፍል አራት" on YouTube https://youtu.be/Mf4t35sHB40

ዛሬ ምሽት 2፡00 EOTC tv ላይ
ዛሬ ምሽት 2፡00 EOTC tv ላይ

"ድንግል ሆይ ከእርሱ ጋር ከሀገር ስትሸሺ ካንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ" ቅዳሴ ማርያም                                               ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                             ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

" እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በሰቆቃወ ድንግል" ✍️ በሰቆቃወ ድንግል ድርሰት ውስጥ ያሉ አርኬዎችን ለመረመረ እጅግ ግሩም የሆነ ትምህርትን ያገኛል፡፡ የዚህ ጽሑፍ መልክኡ ባሉት ፶፯( 57) አርኬዎች ውስጥ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዴት ባለ ሁኔታ በጸሐፊው አንደበት እንደተገለጠች እና ምክንያቱንም ጭምር ጥቂቶቹን በጥቂቱ ማብራራትና ማፍታታት ነው፡፡ ➊ እምዕያማ ማርያም (ማርያም እንቦሳ) ፀሐፊው በአራተኛው አርኬ ላይ ሲጀምር እርሷን በለቅሶ ይከተላት ዘንድ ዜናዋን እንዲነግሩት መንገዷንም እንዲያሳዩት በልመና ቃል የገሊላ ሰዎችን እንዲህ እያለ ይጠይቃል፦ " አይቴ ኅለፈት እምዕያማ ማርያም ጣዕዋ..." ( የገሊላ ሰዎች ሆይ ማርያም እንቦሳ ልጅዋን ይዛ ከማደርያዋ ወዴት ሄደች?) ✍️ ጸሐፊው እመቤታችንን እና ልጇን እንቦሳ ማለቱ እመቤታችን ከመጽነሷ በፊት እያቄምና ሀና በሕልም ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትገባ፣ ስትወጣም እንቦሳይቱ እንቦሳ ስትወልድ አይተው ነበርና ድንግል ማርያምንና ልጇን በእንቦሳ መሰላቸው፡፡ ➋ ወለተ ደክታመ (ደሃ አደግ) በአምስተኛው አርኬም እንዲሁ ጸሐፊው አጥብቆ ሕማምን ስላልለመደች ኃያል የተሰኘ ኢየሱስን ስለተሸከመች ድንግል ማርያምን ማወቅ ሽቶ አሁንም የገሊላ ሰዎችን፦ " ርኢክሙ ወለተ ደክታመ ሐዚላ ሕፃን እንዘ ትጎይይ ገዳመ..."(ልጇን አዝላ ወደ በረሀ ስትሸሽ ደሃ አደግ የሆነች ድንግል ማርያምን አይታችኀልን?) ሲል ይጠይቃል፡፡ ✍️ እዚህም ጋር ጸሐፊው እመቤታችንን ደሃ አደግ ማለቱ በትንሽነቷ ከወላጆችዋ ተለይታ በቤተ መቅደስ ማደጓን ሲያይ ነው፡፡ ሕማምንም ያልለመድሽ ማለቱ ደግሞ እመቤታችን ልዑለ ባሕርይ ኢየሱስ ክርስቶስን በማሕፀኗ ስትሸከም ድካም አላገኛትም ነበርና ማለት በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ስትወልድ ከወለደችም በኋላ የሴቶች ልማድ አላገኛትምና ይህን ሲናገር ሕማምን ያልለመድሽ አላት፡፡ ➌ ነአስ መርዐት (ትንሽ ሙሽራ) አሁንም ጸሐፊው ፍለጋውን እስከሚሞት ድረስ እንደሚቀጥል በመናገር ጥያቄውን በመቀጠል፦ " ርኢክሙኑ ነአስ መርዐተ ሐዚላ ሕፃና እንዘ ተሐውር ፍኖተ..." (ልጇን አዝላ መንገድ ስትሄድ ትንሽ ሙሽራን አይታችኀልን? )ይላል፡፡ ✍️ እመቤታችንን ትንሽ ሙሽራ ማለቱ አካሏን ቢያይ ነው፡፡ ማለትም እመቤታችን በቁመት በስፋት እንደማንኛውም ሰው ናት በክብር ግን ከመላእክት ትበልጣለች፡፡ ይህንን ነገር ሲያጠናክር አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ላይ "እንዘ ነንስቲት አባል አንቲ፣ እንዘ ንስቲት መርዓት አንቲ" (በሦስት ክንድ ከስንዝር ቁመት የተወሰንሽ የ፲፭(15) ዓመት ቆንጆ ስትሆኚ ዙፋኑ እሳት የሆነ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ እንዴት በማሕፀንሽ ወሰንሽ? ለዚህም ክብር አንክሮ ይገባል ) ሲል ተናግሯል፡፡ ➍ ወለተ ብርሃን ( የብርሃን ልጅ ማርያም) ✍️ በዚህ በ፲፫(13)ኛ አርኬ ላይ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን የብርሃን ልጅ ብሎ መጥራቱ ☞ አማናዊው ብርሃን ኢየሱስ ፈጣሪዋ ነውና እርሷም ለዚህ ብርሃን አገልጋዩ ናትና በጨለማ ይኖር የነበረ ዓለም ብርሃን ያየ የዓለም ብርሃን የሆነው ክርስቶስ ከእርሷ ከተወለደ በኋላ ነውና የብርሃን ልጅ አላት፡፡ (ሉቃ ፩÷፵፮-፷ ኢሳ ፱÷፪ ማቴ ፬÷፲፭) ➎ ማርያም ዋኖስ (ሽመላ) ✍️ ጸሐፊው በ፲፱(19)ኛ አርኬው ስለልጇ እያሰበች በማልቀሷ እመቤታችንን በዋኖስ ይመስላታል፡፡ ስለምን ቢሉ፦ ዋኖስ ኑሮዋ በበረሃ ነው ሽመላም ከሀገር ወደ ሀገር ርቆ ሄዶ ሄዶ ምግቡን የሚፈልግ የአዕዋፍ ዘር ነው፡፡ እመቤታችንም ወደ ሩቅ አገርና ወደ በረሃ መሰደድዋን ሲያይ ነው፡፡ ➏ ወለተ ካህናት (የካህናት ልጅ) ✍️ ፳፩(21)ኛ አርኬው እመቤታችን የካህናት ልጅ ስለመሰኘቷ " በቤተ መቅደስ ዘልሕቀት ወለተ ካህናት እንዘ ትሴሰይ ስሩዐ.." (የተመረጠ የሰማይ ምግብን እየተመገበች ፍፁም የሆነ የጽዋ ወይንንም እየጠጣች በቤተመቅደስ ያደገች የካህናት ልጅ ድንግል ማርያም..) ይላታል፡፡ ስለምን እንዲህ አለ ቢሉ ከቤተ ክህነት ተወልዳለችና አንድም በተወለደች በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተ እግዚአብሔር ስትገባ ብዙ ካህናት በክብር ተቀብለው ካህናት በሚያገለግሉበት ቤተመቅደስ አድጋለችና የካህናት ልጅ አላት፡፡ ➐ ንግሥተ ይሁዳ ወሌዊ (የይሁዳና የሌዊ ንግሥት) ✍️ በ፳፰(28)ኛ አርኬው ንግሥተ ይሁዳ ወሌዊ ማለቱ እመቤታችን ከቤተ ክህነት ከነገደ ሌዊ ከቤተ መንግሥትም ከነገደ ይሁዳ በእናትና አባቷ በኩል መወለዷን ሲናገር ነው፡፡ በዚሁ አያይዞም በ፵፰(48)ኛ አርኬ ክብርተ ዘመድ (በዘመድ የከበርሽ) ይላታል፡፡ እንዲህም ማለቱ ከቤተ ክህነት ከቤተ መንግሥት መወለዷን መናገሩ ሲሆን የመላእክት እህት የነብያት ትንቢት የሐዋርያት ስብከት የጻድቃን የሰማዕታት እናት ተብላ ትመሰገናለችና በዘመድ የከበርሽ አላት፡፡ ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ያካፍለን፡፡ ✍️ ሚኪያስ ግዛቸው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

Watch "የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ክፍል ሁለት" on YouTube https://youtu.be/26LCrR8Fds4

"ድንግል ሆይ ከእርሱ ጋር ከሀገር ስትሸሺ ካንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ" ቅዳሴ ማርያም ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
"ድንግል ሆይ ከእርሱ ጋር ከሀገር ስትሸሺ ካንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ" ቅዳሴ ማርያም                                               ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                             ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/