en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 356 subscribers, ranking 6 146 in the Religion & Spirituality category and 2 357 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 356 subscribers.

According to the latest data from 23 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 507 over the last 30 days and by 14 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.68%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 13.08% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 681 views. Within the first day, a publication typically gains 1 875 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 28.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 356
Subscribers
+1424 hours
+1027 days
+50730 days
Posts Archive
በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ ወደ ትግበራ ስለገባው ወጥ የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትና መዋቅር የመመሪያ አቅጣጫ እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ተካሔደ ። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ነሐሴ 20 /12/2016 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ ወደ ትግበራ ስለገባው ወጥ የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትና መዋቅር የመመሪያ አቅጣጫ እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ፤ ሀገር አቀፍየሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው፤ የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ ና የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ዛሬ ነሐሴ 20 በዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሒዷል። የግንዛቤ ማስጨበጫው የተሠጠው በአ.አ ውስጥ ለሚገኙ አቢያተ ክርስቲያናትና ገዳማት አስተዳዳሪ ፣ ጸሐፊ ፣ የሰበካ ጉባኤ ም/ሊቀ መናብርት ፣ የስብከተ ወንጌል ሓላፊዎችና ለሰንበት ት/ቤት ሰብሳቢዎች ነው። በመርሐ ግብሩም የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ ከመንበረ ፖትርያሪክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤት ድረስ ያለውን መዋቅር ፤ የሰንበት ት/ቤቶች ጠቅላላ ጉባኤ በበዓለ ጰራቅሊጦስ እንደሚካሔድ በዚያ የሚተላለፉ መመሪያዎች ተግባራዊ እንደሚሆኑ፤ የሰንበት ት/ቤቶች የውስጥ ደንብ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጸድቆ ወደታች እንደሚወርድ እንዲሁም የሰንበት ት/ቤቶች የምርጫ ጊዜ በተመሣሣይ ወቅት እንደሚሆን ለተሣታፊዎች ገለፃ አድርገዋል። በመቀጠልም የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው ስለ ሥርዓተ ት/ት ገለፃ ሲያደርጉ ሥርዓተ ትምህርቱ የዕድሜ ደረጃቸውን ያማከለ እንደሆነና ከ1ኛ-12ኛ ክፍል በ6 ክፍላተ ትምህርትና 1 አጋዥ ክፍለ ትምህርት የተከፋፈለና እንደሆነ አስረድተዋል። ከ1ኛ-4ኛ ክፍል ያሉት 23 መጽሐፍት በ4 ጥራዝ በ13ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ማስመረቁ ይታወሳል። በቀጣይም የቀሩትን መጻሕፍት ለማሳተም ዕቅድ መያዙን እንዲሁም ከሊቃውንት ጉባኤ ጋር የአርትዖ ሥራ እየተደረገባቸው እንደሆነ አስረድተዋል። አያይዘውም የመማሪያ ቦታ ፣ መምህራን ና መጽሐፍቱ ለሥርዓተ ትምህርቱ ትግበራ ጉልህ ድርሻ እንዳላቸውና ይሄንን ማሟላት የሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዎል። በመጨረሻም የዐዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስቅዱስ" ሰንበት ት/ቤት የቤተ ክርስቲያን ናትና የሰንበት ት/ቤት ዓባላትም ቤተክርስቲያኒቱን በሓላፊነት መምራትና መቆጣጠር ይገባቸዋል ፤ የሰበካ ጉባኤ ዓባላትም ከሰ/ት/ቤቶች ጋር በመመካከር መሥራት ይኖርባቸዋል።" ብለዋል አያይዘውም " የአጥቢያው ሰበካ ጉባኤ ከ1-4 ኛ ክፍል ያሉትን መጽሐፍት ከየአንዳንዱ ስድስት ስድስት መጽሐፍት ለሰንበት ት/ቤቶቹ እንዲገዙ" መመሪያ አስተላልፈዋል። ከተሣታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም መልስ ተሰጥቶባቸው ጉባኤው ተጠናቋል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የ12ኛ ክፍል ምዘና በጉራጌ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅና ልዩ ልዩ የመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተሰጠ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ነሐሴ 19/12/2016 ዓ.ም በሀገር
+6
የ12ኛ ክፍል ምዘና በጉራጌ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅና ልዩ ልዩ የመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተሰጠ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ነሐሴ 19/12/2016 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት 12ኛ ክፍል የደረሱ አጥቢያዎች ዛሬ ነሐሴ 19 የማጠቃለያ ፈተና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህም ተፈታኝ አጥቢያዎች መካከል በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የወልቂጤ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት አንዱ ነው። በፈተና ጣቢያው በመገኘት አባታዊ መልእክትና ቡራኬ የሰጡት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ሰንበት ትምህርት ቤቱ በሥርዓተ ትምህርት ትግበራ እያሳየ ያለውን እምርታ አድንቀው ከትምህርቱ ጋር ምዘና መኖሩ ተማሪዎች ምን ያህል ከመምህሮቻቸው የሚያገኙትን ትምህርት ማወቃቸውን ያሳያል ብለዋል። በመጨረሻም እግዚአብሔር ምስጢሩን ይገልጥ ዘንድ ፀሎትን አድርገው በይፋ የፈተና መርሐ ግብሩን አስጀምረዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የአሥራ ሁለተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና በአዲስ አበባ እና በጉራጌ ሀገረ ስብከት በ5
+9
በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የአሥራ ሁለተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ምዘና በአዲስ አበባ እና በጉራጌ ሀገረ ስብከት በ5 የምዘና ጣቢያዎች እየተሰጠ ይገኛል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።" መዝ 131(132):8 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል! የሰንበት
"አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።" መዝ 131(132):8 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የትንሣኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook �
እንኳን ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok