en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 913 subscribers, ranking 5 777 in the Religion & Spirituality category and 2 265 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 913 subscribers.

According to the latest data from 17 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 644 over the last 30 days and by 24 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 41.62%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.42% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 6 198 views. Within the first day, a publication typically gains 2 296 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 29.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 913
Subscribers
+2424 hours
+2167 days
+64430 days
Posts Archive
በጅማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጠ። በጅማ ሀገረ ስብከት በተለይም በጅማ
+3
በጅማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጠ። በጅማ ሀገረ ስብከት በተለይም በጅማ ከተማ በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓት ትምህርት ዘንድሮ ሁለተኛ የትግበራ ዓመቱ ሲሆን የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ተሰጥቷል። በሀገረ ስብከቱ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በከተማው ከሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በተጨማሪ በተወሰኑ ወረዳዎችም መጀመሩን የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት አስታውቋል። መረጃው የጅማ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

መጻጉዕ 4ኛ ሳምንት "ጌታ ኢየሱስ :- ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬወወ ዳነ። አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" ዮሐ 5:8-9 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የ
መጻጉዕ 4ኛ ሳምንት "ጌታ ኢየሱስ :- ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬወወ ዳነ። አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" ዮሐ 5:8-9 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስታወቀ፡፡ የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርት ክፍል ሐላፊዎች፣ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ አስተባባሪዎችና የአንድነቱ ሥራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመጀመሪያ ወሰነ ትምህርት አተገባበር ላይ ያተኮረ ግምገማ በዛሬው ዕለት አካሄዷል፡፡ የከተማ አስተዳደር ቤተ ክህነቱ የስብከተ ወንጌልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መ/ር ቡሩክ ተስፋዬ “ዛሬ ላይ በሕፃናትና ወጣቶች ላይ የሚሠራ ሥራ የነገን ቤተክርስቲያን ቀጣይነት ያረጋግጣል” የሚል መሪ መልእክት መነሻ አድርገው ንግግር ያደረጉ ሲሆን አድባራት ከቁሳዊ ልማት ባሻገር ለሰው ኃይል ልማት ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መ/ር ቡሩክ አክለውም በከተማ አስተዳደሩ አድባራት ከተመዘገቡት 13 ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል በአሥሩ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው የሰበካ ጉባኤያት ትኩረት አናሳ መሆን፣ የግንዛቤ ክፍተትና የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ወጥ አለመሆን ከገጠሟቸው ችግሮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተገኘ መረጃና በአካል በተደረገ ክትትል የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ሰንበት ትምህርት ቤቶች ቢኖሩም በመረጃ ክፍተት ምክንያት በትግበራው ላይ ውስንነት ያለባቸው እንዲያሻሽሉ አጫጭር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮችና የኹሉም አድባራት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አስፈጻሚ አባላት በተገኙበት መርሐ ግብሩ ተካሂዷል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና
+7
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና አሰጠ፡፡ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወረዳው ስር ባሉ 26 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ላይ በሀገረ አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በወጣ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በ23/06/2017 ከ1ኛ -5ኛ ክፍል እና በ30/06/2017 ዓ.ም ከ6ኛ - 9ኛ ክፍል ያሉ አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበሩ ባሉ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ምዘና አሰጥቷል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት የናሙና ምዘና ሰጠ። እንደሚታወቀው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ወጥ ሥርዓተ ትምህርት ቀር
+5
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት የናሙና ምዘና ሰጠ። እንደሚታወቀው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ወጥ ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ ማስተግበር ከጀመረ ዓመታት አስቆጥሯል። በዚህም መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ከ90% በላይ ሰንበት ት/ቤቶች እየተገበሩት ይገኛሉ። በዚህም መሠረት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት 4 እርከኖች ያሉት ሲሆን ተማሪዎች ከአንዱ እርከን ወደ ሌላው እርከን ሲዘዋወሩ በሀገረ ስብከት ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል ። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነትም ይህን ምዘና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል። በዚህ ዓመትም ሥርዓተ ትምህርቱን እየተገበሩ ከሚገኙ 4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል እያስተማሩ ለሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 22 እና 23 / 2017 ዓ.ም ከ130 በላይ በሚሆኑ ሰንበት ት/ቤቶች ላይ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ምዘና ሰጥቷል ። በቀጣይም በዚህ ዓመት የማጠቃለያ ምዘናውን የሚዉስዱና ወደ ቀጣዩ እርከን (ክፍል ) መዛወር የሚችሉት እነዚህ ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን ተገልጿል። መረጃው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ2017 ዓ.ም የት/ት ዓመት የመጀመሪያውን ወሰነ ት/ት የማጠቃለያ
+6
የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ2017 ዓ.ም የት/ት ዓመት የመጀመሪያውን ወሰነ ት/ት የማጠቃለያ ምዘና አሰጠ። የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከት ደረጃ 38 ሰንበት ትምህርት ቤቶች በ23/06/2017 ዓ/ም የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ምዘና ከ1-8 ክፍል ያሉ  አዲሱን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እያስተገበሩ የሚገኙትን ማጠቃለያ ምዘና አሰጥቷል። በዚህም ዓመት የ4ኛ እና 8ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አቀፍ ሞዴል ምዘና እና ማጠቃለያ ምዘና በሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ለማሰጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል። ዘገባውን ያደረሰን የባህር ዳር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰ
+3
በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2016 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በሀገረ ስብከት ዓቀፍ ደረጃ ሲተገበር የቆየው የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ስርዓተ ትምህርት ትግበራ በተሳካ ሁኔታ ለሁለት ቀን ማለትም በቀን 22 እና 23/06/2017 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው የመጀመሪያ ወሰነ ትምህርት ፈተና ተጠናቀቀ። በትግበራውም በሀገረ ስብከቱ ስር የሚገኙ 12 አጥቢያዎች የተሳተፉ ሲሆን በቁጥር 414 የ4ኛ ክፍል 330 የሚሆኑ የ8ኛ ክፍል በጥቅሉ ከ744 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ መቻላቸው ተገልጿል። በመጨረሻም የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መ/ሃ/ዘላለም በተመረጡ አጥቢያዎች የፈተና አሰጣጡን ሁኔታ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህ ሥራ ላይ ለተሳተፉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላት መምህራን እና አስተባባሪዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። መረጃው የአንድነቱ ትምህርት ክፍል ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
+2
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ  ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል። ዘገባው የኢ/ኦ/ተ/ቤ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ሰንበት ትምህርትቤቶችን በማጠናከር ግብረገብ የተላበሰ ትውልድ ማፍራት እንደሚገባ ተገለጸ። በሰሜን ወሎ ሀገረስብከት የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ከየካቲት 20 እስከ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በወረ
+2
ሰንበት ትምህርትቤቶችን በማጠናከር ግብረገብ የተላበሰ ትውልድ ማፍራት እንደሚገባ ተገለጸ። በሰሜን ወሎ ሀገረስብከት የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ከየካቲት 20 እስከ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በወረዳው ከሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ላይ ትኩረት ያደረገ ሥልጠና ሰጥቷል። በሥልጠናው መርሐ ግብር ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ወኃቤ ሀብታት መምህር ፍስሐ አለሙ እንዱሉት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማጠናከር ግብረ ገብ የተላበሰ ትውልድ ማፍራት ይገባል ብለዋል። ሥራ አሰኪያጁ አክለውም የሥልጠናው ተሳታፊዎች በሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት  ሐላፊነት በተሞላበት አኳሀን ተግባራዊ እንዳያደርጉ አሳስበዋል። ሥልጠናውን የሰጡት  የመቄት ወረዳ ቤተ ክህነት ሒሳብ ሹም መምህር ቀለመ ወርቅ በበኩላቸው ቤተክርስቲያናችን ዕድሜና የክፍል ደረጃን መሠረት ያደረገ ሥርዓተ ትምህርት ቀርጻ ወደ ሥራ የገባች በመሆኑ ወጣቶችን በእዚህ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በማስተማር መሠረተ እምነታቸውን እንዲያውቁ ማድረግ ይገባል ብለዋል። በሥልጠናው  የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ሠራተኞች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አንድነት ሥራ አስፈጻሚዎች፣  ከአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተወከሉ ሰንበት ተማሪዎች ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ፍላቂት ወረዳ ማዕከል ተወካዮች፣ የፍላቂት ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል የሐዲስ ኪዳን ጉባኤ ቤት ደቀ መዛሙርትን ጨምሮ ከ50 በላይ ሰልጣኞች ተሳታፊ ሁነዋል። ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ወልድያ ማእከል ሚዲያ አገልግሎት ዋና ክፍል ነው። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አን
እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥ የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።" መዝ 43(44)-7 መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥ የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።" መዝ 43(44)-7 መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች!" ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጾም ፤ ዓቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙን የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነ
"ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች!" ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጾም ፤ ዓቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙን የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ!" መዝ 88፡3 እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን (ኪዳነ ምሕረት) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ሰናይ ሌሊ
"ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ!" መዝ 88፡3 እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን (ኪዳነ ምሕረት) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok