fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 309 مشترک است و جایگاه 6 161 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 365 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 309 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 21 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 502 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 48.88% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.10% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 0 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 875 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 22 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 309
مشترکین
+1624 ساعت
+1117 روز
+50230 روز
آرشیو پست ها
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት የናሙና ምዘና ሰጠ። እንደሚታወቀው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ወጥ ሥርዓተ ትምህርት ቀር
+5
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የመጀመሪያውን መንፈቅ ዓመት የናሙና ምዘና ሰጠ። እንደሚታወቀው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ወጥ ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ ማስተግበር ከጀመረ ዓመታት አስቆጥሯል። በዚህም መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ከ90% በላይ ሰንበት ት/ቤቶች እየተገበሩት ይገኛሉ። በዚህም መሠረት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት 4 እርከኖች ያሉት ሲሆን ተማሪዎች ከአንዱ እርከን ወደ ሌላው እርከን ሲዘዋወሩ በሀገረ ስብከት ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል ። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነትም ይህን ምዘና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል። በዚህ ዓመትም ሥርዓተ ትምህርቱን እየተገበሩ ከሚገኙ 4ኛ ፣ 8ኛ እና 10ኛ ክፍል እያስተማሩ ለሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 22 እና 23 / 2017 ዓ.ም ከ130 በላይ በሚሆኑ ሰንበት ት/ቤቶች ላይ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ምዘና ሰጥቷል ። በቀጣይም በዚህ ዓመት የማጠቃለያ ምዘናውን የሚዉስዱና ወደ ቀጣዩ እርከን (ክፍል ) መዛወር የሚችሉት እነዚህ ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን ተገልጿል። መረጃው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ2017 ዓ.ም የት/ት ዓመት የመጀመሪያውን ወሰነ ት/ት የማጠቃለያ
+6
የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ2017 ዓ.ም የት/ት ዓመት የመጀመሪያውን ወሰነ ት/ት የማጠቃለያ ምዘና አሰጠ። የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በሀገረ ስብከት ደረጃ 38 ሰንበት ትምህርት ቤቶች በ23/06/2017 ዓ/ም የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ምዘና ከ1-8 ክፍል ያሉ  አዲሱን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እያስተገበሩ የሚገኙትን ማጠቃለያ ምዘና አሰጥቷል። በዚህም ዓመት የ4ኛ እና 8ኛ ክፍል ሀገረ ስብከት አቀፍ ሞዴል ምዘና እና ማጠቃለያ ምዘና በሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ለማሰጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል። ዘገባውን ያደረሰን የባህር ዳር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰ
+3
በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2016 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በሀገረ ስብከት ዓቀፍ ደረጃ ሲተገበር የቆየው የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ስርዓተ ትምህርት ትግበራ በተሳካ ሁኔታ ለሁለት ቀን ማለትም በቀን 22 እና 23/06/2017 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው የመጀመሪያ ወሰነ ትምህርት ፈተና ተጠናቀቀ። በትግበራውም በሀገረ ስብከቱ ስር የሚገኙ 12 አጥቢያዎች የተሳተፉ ሲሆን በቁጥር 414 የ4ኛ ክፍል 330 የሚሆኑ የ8ኛ ክፍል በጥቅሉ ከ744 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ መቻላቸው ተገልጿል። በመጨረሻም የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መ/ሃ/ዘላለም በተመረጡ አጥቢያዎች የፈተና አሰጣጡን ሁኔታ ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህ ሥራ ላይ ለተሳተፉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላት መምህራን እና አስተባባሪዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። መረጃው የአንድነቱ ትምህርት ክፍል ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል
+2
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ  ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል። ዘገባው የኢ/ኦ/ተ/ቤ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ሰንበት ትምህርትቤቶችን በማጠናከር ግብረገብ የተላበሰ ትውልድ ማፍራት እንደሚገባ ተገለጸ። በሰሜን ወሎ ሀገረስብከት የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ከየካቲት 20 እስከ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በወረ
+2
ሰንበት ትምህርትቤቶችን በማጠናከር ግብረገብ የተላበሰ ትውልድ ማፍራት እንደሚገባ ተገለጸ። በሰሜን ወሎ ሀገረስብከት የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ከየካቲት 20 እስከ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በወረዳው ከሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር ላይ ትኩረት ያደረገ ሥልጠና ሰጥቷል። በሥልጠናው መርሐ ግብር ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ወኃቤ ሀብታት መምህር ፍስሐ አለሙ እንዱሉት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማጠናከር ግብረ ገብ የተላበሰ ትውልድ ማፍራት ይገባል ብለዋል። ሥራ አሰኪያጁ አክለውም የሥልጠናው ተሳታፊዎች በሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት  ሐላፊነት በተሞላበት አኳሀን ተግባራዊ እንዳያደርጉ አሳስበዋል። ሥልጠናውን የሰጡት  የመቄት ወረዳ ቤተ ክህነት ሒሳብ ሹም መምህር ቀለመ ወርቅ በበኩላቸው ቤተክርስቲያናችን ዕድሜና የክፍል ደረጃን መሠረት ያደረገ ሥርዓተ ትምህርት ቀርጻ ወደ ሥራ የገባች በመሆኑ ወጣቶችን በእዚህ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በማስተማር መሠረተ እምነታቸውን እንዲያውቁ ማድረግ ይገባል ብለዋል። በሥልጠናው  የመቄት ወረዳ ቤተክህነት ሠራተኞች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አንድነት ሥራ አስፈጻሚዎች፣  ከአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የተወከሉ ሰንበት ተማሪዎች ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ፍላቂት ወረዳ ማዕከል ተወካዮች፣ የፍላቂት ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል የሐዲስ ኪዳን ጉባኤ ቤት ደቀ መዛሙርትን ጨምሮ ከ50 በላይ ሰልጣኞች ተሳታፊ ሁነዋል። ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ወልድያ ማእከል ሚዲያ አገልግሎት ዋና ክፍል ነው። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አን
እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥ የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።" መዝ 43(44)-7 መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! "በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥ የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።" መዝ 43(44)-7 መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች!" ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጾም ፤ ዓቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙን የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነ
"ጾም የነፍስን ቁስል ታድናለች!" ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጾም ፤ ዓቢይ ጾም በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙን የበረከት ያድርግልን! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ!" መዝ 88፡3 እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን (ኪዳነ ምሕረት) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ሰናይ ሌሊ
"ከመረጥኳቸው ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ!" መዝ 88፡3 እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ቀን (ኪዳነ ምሕረት) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ (ዐቢይ ጾምን) አስመልክቶ የቅዱስ ፓትርያርኩ መልዕክት:: በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ ፤ የዲያብሎስን የፈተና ወጥመዶች በጣጥሶ በድል ኣድራጊነት የተገለጠው ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ አደረሰን አደረሳችሁ! “አኮ በኅብስት ክመ ዘየሓዩ ሰብእ አላ በኵሉ ቃል ዘይወፅእ እምኣፉሁ ለእግዚአብሔር፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” (ማቴ.፬÷፬) ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውነ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡ በአርባዎቹ ቀናት ሁሉ በቀንም ሆነ በሌሊት ምንም አልበላም ነበር፣ ካርባ ቀንም በኋላ ተራበ፤ በመብል ስውን ከእግዚአብሔር ጋር ማጣላት ልማዱ የሆነ ዲያብሎስም መራቡን ኣይቶ ለምን ትራባለህ? እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ ይሁነ ብለህ እዘዝና ብላ፧ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለህምን? ይህንን ማድረግ ኣያቅትህም ብሎ በመብል ምክንያት የሱ ታዛዥ እንዲሆን ፈተነው:: በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም” የሚል ነበረ፤ ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆነን ኣሳየ፣ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፣ ግን አልተሳካለትም፤ በመጨረሻም ጌታ “ሑር እምድኅሬየ ሰይጣን፣ ሰይጣን ከኋላዬ ወግድ" ብሎ እኩይ ተግባሩን ውድቅ ኣድርጎበታል፣ እሱም ተስፋ ቆርጦና በጌታችን መንፈሳዊ ልዕልና ተሸንፎ ሂዶአል:: የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ከጌታችን ጾም የምንወስደው ብዙ ትምህርት አለ፣ ከሁሉ በፊት ሰው በሕይወት መኖርየሚችለው በእንጀራ ብቻ ኣይደለም ብሎናል፣ ይህ ኣባባል በሕይወት ለመኖር እንጀራ አያስፈልግም ማለት ኣይደለም ፧ ሕይወትን ማኖር የሚቻለው በእንጀራ ብቻ እንደ ሆነ አድርገን እንዳናስብ ግን ቃሉ ያስተምራል ይህም በዓለማችን በየዕለቱ የምናውቀው ሓቅ ነው፤ ብዙ ሰዎች እንጀራን ሳያጡ በየዕለቱ ሕይወትን ያጣሉ፤ ምክንያቱም በሕይወት ለመኖር የእግዚአብሔር ቃልም እንጂ እንጀራ ብቻው በቂ አይደለምና ነው:: ዓለማት ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል ሁነ ተብለው በቃሉ እንደተፈጠሩ፣ በቃሉም ጸንተው እንደሚኖሩ ኋላም በቃሉ እንደሚያልፉ ሁሉ የስው ሕይወትም በዚህ ቃል ይወሰናል፤ እንጀራ ኖረም አልኖረ ቃሉ በቃ ካለ ያበቃል፣ ኑር ካለ ደግሞ እንጀራ ባይኖርም ይኖራል፤ ስለዚህ በሕይወታችን ወሳኝ ሥልጣን ያለው የእግዚአብሔር ቃል እንጂ፣ እንጀራ ብቻ አለመሆነ ጌታችን በዚህ አስተምሮናል:: ከዚህም ሌላ የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባርኣሳይቶናል፣ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፣ አለመሆነንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ ልዕልና ነው ማለት ነው:: ይህም ማለት በእግዚአብሔር የተከለከሉትን ግብረ ኃጣውእ እንድንፈጽም ዲያብሎስ ኅሊናችንን ሲገፋፋው፣ ያን ጊዜ ዲያብሎስ ሊፈትነን እየከጀለ እንደሆነ መንቃት ያስፈልገናል:: ጌታችን እንዳሳየንም ለክፉው ግብረ ኃጢኣት የእሺታ መልስ ሳይሆን የእንቢታ ግብረ መልስ መስጠት ይገባናል ማለት ነው፤ ይህንን ኣቅዋም የሕይወታችን ቀዋሚ መርሕ ካደረግን፣ ዲያብሎስ እየተሸነፈ፣ እኛም እያሸነፍን እንኖራለን፣ ይህንን ስንለማመድ ሓሳባችን ወይም መንፈሳችን ከዲያብሎስ በላይ የላቀና የተራቀቀ ይሆናል ! ዲያብሎስ ረቂቅ ነው፤ የሚጣላንም ረቂቁን አእምሮኣችን በመጠቀም ነው: እኛም እሱን መዋጋትና ማሸነፍ የምንችለው ረቂቁ ኣእምሮኣችን ከሱ የላቀና የረቀቀ ኣድርገን በመጠቀም መሆኑን መገንዘብ ይገባል ይህን ካደረግን እሱ በኛ ላይ አቅም ኣይኖረውም:: • የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ጾመ ኢየሱስ እያልን በየዓመቱ የምንጾመው የታላቱ ጾማችን ዓላማ ዲያብሎስን ለማሸነፍ ነው፤ የዲያብሎስ ማሸነፊያ ስልት የመልካም ጎሊና ልዕልና ነው! ሰውነታችን በመብልና በመጠጥ ሊደነድን መልካም ኅሊና በውስጣችን ዓቅም ያጥረዋል፣ መልካም ኅሊና ሲያጥረን ዲያብሎስ ዘው ብሎ ይገባና ወደ ክፉ ኅሊና፣ ከዚያም ወደ ግብረ ኃጢኣት ይወስደናል፣ በዚህ ጊዜ እኛ ተሸናፊዎች እሱ ኣሸናፊ ይሆናል፣ በአንጻሩ ደግሞ ስውነታችን ከመብልና ከመጠጥ ሊለይ መልካም ኅሊና፤ ቍጥብነት፣ ማስተዋልና ማመዛዘን በውስጣችን ትልቅ ጉልበት ያገኛሉ : እነሱ ጕለበቱ ማለት ዲያብሎስ መግቢያ አጣ ማለት ነው፤ እሱ ካልገባ ግብረ ኃጢኣት አንፈጽምም፣ በዚህ ጊዜ ዲያብሎስ ተሸናፊ እኛ ኣሽናፊዎች እንሆናለን፤ ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው:: ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን፣ እንግዲህ በወርኃ ጾም ከመልካም ኅሊና የሚመነጭ መልካም ስራ ማከናወን ግድ ይለናል። ምክንያቱም ጾምን የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፤ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርት፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፣ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፤ ጥላቻ፤ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀርልናደርግ ነው! በዚህ መንፈስ ጾሙን ከጾምን ጾማችን ግቡን መትቶአል፤ ዲያብሎስም ተሸንፎአል ማለት ነው፤ ስለሆነም በዚህ መንፈስ ጾሙን ልንጾም ይገባል፡። በመጨረሻም- ወርኅ ጾሙን የተራበውን በመመገብ የተራቈተውን በማልበስ በኃላፊነት ያለን የኅብረተሰብ መሪዎችም ፍትሕንና እኩልነትን በማስፈንና ከነገሮች ሁሉ በፊት ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ በመስጠት ጾሙን እንድናሳልፍ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን:: መልካም ወርኀ ጾም ያድርግልን። እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም

የግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት  የአገልጋይ እጦት እንደገጠመው ተገለጸ። የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት የሚገኙ አባላት የልማት ተነሺዎች መሆናቸው አገልግሎቱን እንዳሰተጓጎለውም ተጠቁሟል።  አቶ ዘውዱ ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሰብሳቢ ከማኀበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው የሚኖር ሰውና ምእመን በመቀነሱ ሳምንታዊ ፕሮግራሞችን ወደ ወርሀዊ የመቀየር፣ሕጻናት ባሉበት ሆነው እንዲማሩ ዕድሉን እንዲያገኙ የማመቻቸት እና የኦላይን ትምህርቶችን ለመስጠት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብለዋል፡፡  የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላቱ በኢኮኖሚያዊ፣በማኅበራዊ ጉዳዮች በተለይም በሃይማኖታዊ አንጻር ቃለ እግዚአብሔር እንዳይሰሙ ጫና እንደደረሰባቸው የሰንበት ትምህርት ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዘነበ ክፍሉ ተናግረዋል። በአገልጋይ እጦት ምክንያት አንዳንድ ክፍሎች መታጣፋቸውን የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባል የሆኑት መቅደላዊት ተሾመ የተናገሩ ሲሆን ያሉትም ጥቂት አባላቶች ክፍሎችን ደርበው እንዲያገለግሉ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ችግሩን ለማቃለል በገዳሙ ውስጥ የሚገኙ አባቶችን በመጠቀም የሰንበት ትምህርት ቤት አባላቱ እንዲመጡ ቅስቀሳ የማካሄድ እና በወር አንድ ጊዜ ጉባኤ በማዘጋጀት እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን አባሏ አንስተዋል፡፡ ዘገባው የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የኢትዮ ሶማሌ ሀገረ ስብከት የጅጅጋ ምስራቅ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል መንበረ ጵጵስና ፈለገ ያሬድ ሰንበት ት/ቤት  በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ልጆቹን ማስተማር ከጀመረ 3 (ሦስት) ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን በ2017 ዓ.ም ከጥቅምት ወር አንሰቶ ያስተማራቸውን ተማሪዎች የመጀመሪያ መንፈቅ አመት ማጠቃለያ ፈተና የካቲት 8 እና 9 የሀገረ ስብከቱ ዋና ቁጥጥር ክፍል ሐላፊ መጋቤ ሠናያት የኔነህ ደበሌ ፤ የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ክፍል ሐላፊ መጋቤ ስዩማን ቀሲስ ክፍሌ ሞቱማ ፤ እንዲሁም የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መልአክ ሕይወት ቀሲስ መሠረት አዳነ ፤ የማኅበረ ቅዱሳን ጅግጅጋ ማእከል ዋና ጸሐፊ ዲ/ን  መንግስቱ ፤  የደብሩ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አባላት እና የሰንበት ተማሪ ወላጆች በተገኙበት የምዘና መርሐ ግብር አካሂዷል። የፈለገ ያሬድ ሰንበት ት/ቤት አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ሦስተኛ፣ አራተኛ፣ ስድስተኛ፣ እና ሰባተኛ ክፍል በአመቱ መጀመሪያ መንፈቅ ዓመት የሚሰጡ መሠረተ ሃይማኖት፣ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር፣ እና ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ኮርሶችን አስተምሮ በአጠቃላይ 223 ተማሪዎችን ፈትኗል። በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ክፍል ኃላፊ መጋቢ ስዩማን ክፍሌ ሞቱማ እንዳስተላለፉት ሰንበት ት/ቤቶች አሁን ላይ እየተሰራ ያለው ሥራ እንደ አጀማመር ጥሩ ቢሆንም ከዚህ በኋላ ግን በተላይ በዚህ ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው እና ተማሪዎችም በዚህ ትምህርት ራሳቸውን አንጸው የነገ የቤተክርስቲያን ተረካቢ እንዲሆኑ አሳስበዋል። መረጃው የጅጅጋ ምስራቅ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ፈለገ ያሬድ ሰንበት ት/ቤት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙና የሰንበት ት/ቤቶችን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ባደረጉ ሰንበት ት/ቤቶች በመጀመሪያው ወሰን ዓመት ሲሰጡ የነበሩ የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ትምህርቶች የማጠቃለያ
+5
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙና የሰንበት ት/ቤቶችን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ባደረጉ ሰንበት ት/ቤቶች በመጀመሪያው ወሰን ዓመት ሲሰጡ የነበሩ የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል ትምህርቶች የማጠቃለያ ፈተና የካቲት 09 ቀን 2017 ዓ.ም ተከናውኗል። በደብረ ብርሃን ከተማ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥር ለሚገኙ የሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች የ4ኛ እና የ8ኛ ክፍል 843 ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በደብረ ጽባሕ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ተሰጥቷል። መረጃው የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok