en
Feedback
🍃بالقرآن نحي {በቁርአን እንኖራለን

🍃بالقرآن نحي {በቁርአን እንኖራለን

Open in Telegram

የተለያዩ ቁርኣናዊ አስተምህሮ’ዎች፣ ጣፋጭ ቲላዋዎች፣ ቁርኣንን የሚመለከቱና በቁርኣን ዙሪያ የሚሽከረከሩ መልዕክቶች የሚተላለፍበት ቻናል join ይበሉ ! ቁርኣን የወረደው ለሰው ልጅ መመሪያ፣ እንድናስተነትነውና እንድንገሰፅበት ነው። አላህ እንዲህ ይላል፦ (ይህ) ወዳንተ ያወረድነው ብሩክ መጽሐፍ ነው፡፡ አንቀጾቹን እንዲያስተነትኑና የአእምሮዎች ባለቤቶችም እንዲገሰጹ (አወረድነው)፡፡ {Q 38:29}

Show more
877
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-1630 days
Posts Archive
Repost from ABX
የአላህ ሲትር ባይኖርልን እኮ የሚወደንና የሚያከብረን ሰው ሁሉ እንዴት ይሸሸን እንደነበር። ጌታዬ ሆይ ሲትርህን አታንሳብን። https://t.me/MuhammedSeidAbx

ምድር ላይ አንድ ጊዜ እንጂ ሁለቴ የመኖር ዕድል አልተሠጠንም። ይህ ዓለም ወደዚያኛ ዓለም መሸጋገሪያችሁ እንጂ ሌላ አይደለም ተብሎ ቁርጡ ተነግሮን በቁርጥ የመጣን ሕዝቦች ነን። ስለዚህ ፣ በዕድሜያችን አንቀልድም። እስካለን ድረስ ለዲናችን እንኖራለን ። ሕይወታችን እሱ ነው። በሱ ነው። ሌላ ሕይወት የለንም። ጌታዬ ሆይ በዚህም ሆነ በመጨረሻው ዓለም በዲናችን ላይ አጽናን። https://t.me/MuhammedSeidAbx

በማሰብ ድንበር አለፍን ሁሉም ነገር እንደተፃፈ ረስተን ። በመጨናነቅና በማዘን ድንበር አለፍን አላህ ከኛ ጋር መሆኑን ረስተን ። ስለ ወደፊቱ አስበን በጣም ፈራን ሁሉም ነገር በአላህ እጅ መሆኑን ረ
በማሰብ ድንበር አለፍን ሁሉም ነገር እንደተፃፈ ረስተን ። በመጨናነቅና በማዘን ድንበር አለፍን አላህ ከኛ ጋር መሆኑን ረስተን ። ስለ ወደፊቱ አስበን በጣም ፈራን ሁሉም ነገር በአላህ እጅ መሆኑን ረስተን ። በሰወች ፍራቻ ቢዚ ሁነን የሰወች ልጅም ጂኖችም ተሰባስበው ሊጎዱህ ቢፈልጉ አላህ ከፃፈልህ ውጪ እንደማይጎዱን ረሳን ። ያረብ በሁሉም ነገር ከጎናችን ሁን

በጌታዋ ቸርነት እየተመላለሰች በትዕግስቷ ፀንታ ጀግኖቿን የታቀፈች። ከአላህ ብሩህ ተስፋ ሰንቃ ወደፊት የምትራመድ የዘመናችን ልዩ ጌጥ። ➖➖➖➖➖ ጋዛዊቷ እንስት ➖➖➖➖➖ የልቧ ኢማን ፍርስራሹን ያደ
በጌታዋ ቸርነት እየተመላለሰች በትዕግስቷ ፀንታ ጀግኖቿን የታቀፈች። ከአላህ ብሩህ ተስፋ ሰንቃ ወደፊት የምትራመድ የዘመናችን ልዩ ጌጥ። ➖➖➖➖➖ ጋዛዊቷ እንስት ➖➖➖➖➖ የልቧ ኢማን ፍርስራሹን ያደምቃል። ጥንካሬዋ ድንጋዩን ሳይቀር ያበራል። ፅልመቱ ፍፁም በሆነ ትዕግስቷ ይገፈፋል። ➖➖➖➖ ፅናቷ ከምናውቀው ይለያል። አዎ! ምስጢሩን ያልደረስንበት የልብ ውበት፣ ሱጁድ የተደፉ የአር-ረህማን ባርያዎች የተኮሱት የዱዓ ውጤት ነው። ለመንፈሷ ፅናትን፣ ለደከመ ሰውነቷ እረፍት የሚቸራትን ኢማን ታጥቃ የማይበገረውን ጦር ሁሉ አንበርክካለች። ታንኩን ነሚሩን ማርካለች። ከዕንባዋ ጋር የተቀላቀለ መዳፏን ወደ ሰማይ ዘርግታ በጣቶቿ ጫፍ የማይደበዝዝ ብርሃንን ከአላህ ትጠይቃለች። አንደበት በማይገልፀው ጥንካሬዋ ድልን እየጠበቀች በፅናትና በትዕግስቷ እነሆ ዛሬም አለች። ➖➖➖➖➖ እርሷ እራሷ የጋዛዋ እንስት የምዕራባውያንን እብሪተኝነት አሸንፋ፣ ምናባዊ ዲሞክራሲን ተገዳድራ ድል ታደርጋለች። እመኑኝ ታሸንፋለች። እርሷ ናት የእስልምናን ነፃነት ዳግም የምታፈካው። ➖➖➖➖➖➖ Mahi Mahisho ➖➖➖➖➖➖ ቴሌግራም 👇👇👇👇 t.me/yesheh_kalidrashid_daewawoch

አንድ ዐሪፍ ቢላህ ተጠየቁ፦ «ጌታዬን ስጣራ በዝምታ ነው?  ወይስ ድምጼን በማውጣት?» እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ « ጌታህን ከፍ ባለ ዝምታህ ጥራው!» ዝምታ ከድምጽ በላይ ጉልበት አለው፣ ዝምታ ውስጥ ጥልቅ ማሰላሰል አልለ፣ ዝምታ ውስጥ ማሰብና መረጋጋት አልለ፣ በዝምታ ከአላህ ጋር ማውጋት አልለ። ለሊት ዝምታ ይበዛዋል፣ ለሊቱ በቆየ ቁጥር ዝምታውም ይጨምራል። ዝምታው በጨመረበት ውድቅት ለሊት ላይ ባርያም ከወዳጁ ጋር ይገለላል። በዝምታ ለሊት ዝም ባሉ ቃላቶች ወዳጅን ያናግራል። በጊዜ በዝምታ በማረፍ ጣፋጩን የዝምታ ወቅት የለይልን በረከት ለመውሰድ መነየት ያሰፈልጋል። ለኒያው ያልሰሰተ ሰው ለሥራው ይወፈቃል! ሰላም ♥

« በአንድ በጎ ባርያ ላይ የሚሰፍን የአሏህ ውዴታ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ስሜት አለው። እጅግ በጣም ቀዝቃዛ እና ብርድ በሆነ ሌሊት  ሞቅ እንዳለ ብርድ ልብስ ልብህን ያካብባል። ወይም የመለኮታዊ ብርሃን ብልጭታ ነውና ወዳንተ ዘልቆ፣ በደም ስርህ ውስጥ ይጓዛል..…ይቆጣጠርሃል።…ከዚያም ስሙን በምላስህ ማዘወተር፣ጣፋጭ ሱስ ይሆንብሃል! » «በየ ኹሉም የኑሮ ሒደት ውስጥ…በየ ሰዓቱ የምትደጋግመው…ጣፋጭ ስም የርሱ ስም ይሆናል። የስሙ ጥፍጥና የሚሰጥህ ጥልቅ የመደድ መንፈስ የፍቅር ምናኔ ውስጥ ያስገባሃል።ስሙ ቀልብህ ለይ ኢማንን፣ ሩሕ ዘንድ ሰኪናን፣ ጀሰድህ ላይ ደግሞ የኑር ጀማላን ፈገግታን ውበትን…ሞልቶ ያሸበርቅልሃል!» ስሙን ብቻ መጥራት ህያው ኑር ያለብሳል… الله🩵

Repost from ABX
አባቴ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ወደዚያኛው ተሸጋግረዋል። በረሕመትህ ተቀበላቸው የኔ ጌታ። ይህ ክፉ ክስተት በዕድሜዬ እንዳሁኑ ዓይነት ከባድ ምት አሳርፎብኝ አያውቅም። የሞት ዜና ደርሷችሁ ድንጋጤያችሁን ላልተረዳሁላችሁ ሁሉ ይቅርታ እጠይቃለሁ ። ካልደረሰበት ሁሉም ጠንካራ ነው። ሲደርሰበት ሁሉም ደካማ ነው። አባቴ አንበሳ ነው። ደቦል ሆኜ ለማደግና እሱን መስዬ ለመውጣት በዘመኔ ሁሉ ብዙ ታገልኩ። ግና አልቻልኩም። ከፍፍፍ ያለ ሰው ነበር። እዚህ የመጣሁት ዱዓችሁን ፈልጌ ነው። በኔ ላይ ትንሽ እንኳ ኸይር ነገር ካያችሁ መነሻው አባቴ ነውና ለሱ ዱዓ አርጉለት። ዱንያ ዕድሜዋ ትንሽ ነው። እንዲያም ሆኖ የምንወዳቸው ትንሽም ቢሆን ቢቆዩልን እንዴት በወደድን። አላህ ይዘንልህ። ማረፊያህ ይመር የኔ ጀግና።

[…አንተ የኔ አሏህ 1…] ፍቅርህ ብርሓናማ ነው! በ’ኛ አድማስ ላይ የተጋረደው ድቅድቅ ፅልምት ባሻገር ኃያል፣አሸናፊው፣እና ንጉሱ የሆንከው አሏሃችን ያንተ ህያው ብርኃን አለ።ወደ’ኛ የሚወነጨፈው ፍ
[…አንተ የኔ አሏህ 1…] ፍቅርህ ብርሓናማ ነው! በ’ኛ አድማስ ላይ የተጋረደው ድቅድቅ ፅልምት ባሻገር ኃያል፣አሸናፊው፣እና ንጉሱ የሆንከው አሏሃችን ያንተ ህያው ብርኃን አለ።ወደ’ኛ የሚወነጨፈው ፍቅርህ በሩሓችን ላይ ደማቅ መንፈሳዊ ሕያው ብርሓንን ያኖራል። የኑር ብራቅህን ወደ ባዶው እኛነታችን ሰንዝረህ እንድናስብህ አደልከን። መድረስ ወዳንተው ነው፣ ማድረስም ያንተ ነው።አላህዬ☺️ እኛም…አሰብንህና ደግሞ…ካንተ ውጪ ላለ ለሁሉም ነገር ምንም ግድ አጣን የወደቅንበትን፣የባዘንንበትን የስቃይ አረንቋ ዘንግተን ፍካት በልባችን ተሞላ።አንተን በማሰብ ውስጥ ተጠመድን። እኛማ በምን አቅማችን…! አንተው አሰብኸን ኣሳሰብኸንም፣ እንድናስብህ ኣደረግኸን። ልታድነን ስትፈልግ።ከዚያ በኃላ…አንተ ፈቅደህ፣በኛ ላይ እንዲሆን የሻኸው ሁሉ እንዲጣፍጠን ሆነ። በሁሉም መከራ ውስጥ ጥበብህ…ፍቅር ውዴታህ አዛኝነትህ ይታየን ጀመር።እናም ያኔ ስለ ሁሉም ነገር ግድ የለንም። ግድ የሚሰጠን "አሏህ…አሏህ" ማለት ሆነ! الله…!💚

በርካቶቻችን በቀልብ ድርቀት ፈተና ውስጥ ወድቀን በጭካኔ ህመም እየተሰቃየን ይሆናል። አንዳንድ ሰዎች ግን ፈተናቸው ተቃራኒ ነው። በቀልብ ልስላሴና በቀልብ ቅጥነት ስር ወድቀው የሚሰቃዩ አሉ። የነርሱ ስቃይ ከባድ ነው! : መከረኛ በሆነው በዚህ ዓለም ውስጥ ቀልበ ቀጭን መሆን ከባድ ነው። የሰብዓዊው ፍጡር እንግልት በጠናበት በዚህ ዓለም እዚህም እዚያም ለሚወድቀው ነፍስ ማዘን መራር ነው። ፀሀይ ወጥታ እስከምትጠልቅ ስንት ዓይነት የሰዎችን ስቃይና ሰቆቃ እናያለን? ቀልበ ቀጭኖች የሌሎችን ስቃይ እንደራሳቸው ስቃይ ይመለከታሉ። በሰው ሃሳብ ይብሰለሰላሉ። በጭንቀታቸው ይብሰከሰካሉ። በሰዎች ህመም ይታመማሉ። ከምላሳቸውና ከኪሳቸው እምባቸው ይቀድማል። ሩኅሩኅ ናቸው። ለሰዎች መልካምን ይመኛሉ። በሰው ላይ በሚደርስ ክፉ ነገር ይጨነቃሉ። ሰዎች በእጦት ከተረበሹ እነርሱም ያላቸውን ሰጥተው በእጦት ከሚሰቃዩት ጋር ራሳቸውን ይቦድናሉ። የሚሰጡት ካጡም መለገስ ባለመቻላቸው በመቆጨት በለቅሶ ይመለሳሉ። : እነዚህ ሰዎች ጥቂቶች ናቸው። በህይወቴ ከሦስት የማይበልጡ ሰዎች ከነዚህ እንደሚመደቡ እመሰክርላቸዋለሁ። ምቾትን አያውቋትም። በእርግጥ በዓለሙ ስቃይ ይሰቃያሉ። ነገርግን ስቃያቸው ቢበረታም የጀነት ናቸው። እንደውም ያለ ሂሳብ ጀነት ከሚገቡት የበሯ ከፋቾች ናቸው! በክብር የሚገቡበት የግል በርም ሳይኖራቸው አይቀርም! የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ልባቸው እንደ ወፍ ልብ የሆኑ ሰዎች ጀነት ይገባሉ!» በዚህ ሐዲስ ላይ «የወፍ ልብ ያላቸው» የተባሉት ሩኅሩኅ ሰዎች ናቸው ተብሏል በአንድ ተፍሲር። አላህ ርኅራኄን ይስጠን! https://t.me/fiqshafiyamh

#ሑስነዘን_ቢላህ «በአላህ ላይ ያለህ ጥርጣሬ እውነተኛ ቢኾን የከለከለህ ነገር ከለገሰህ ነገር ጋር አንድ እንደሆነ ታውቅ ነበር።» ኢብን ዓጣእ አስሰከንደሪይ (ቁዲሰ ሲረሁ) ብዙ ጊዜ አላህን የበለጠ የምንቃረበው ተከልክለናል ብለን ባሰብን ጊዜ ነው። የተለገስንና ጊዜ ያለን እውነተኛ ባሕርይ ይገለጥና ሰዎች ሲመቸን ባሕርያችን የተቀየ ይመስላቸዋል። የጸጋዎች እኛ ላይ መስፋት ያለንን ትክክለኛ ባሕርይ እንደሚገልጥ አይታወሰንም። በተቃራኒው የነገሮች እኛ ላይ መጥበብና መያዝ እንዲሁም መከልከል በርካታ ያሉብንን ነውሮች ከመደበቅ በላይ እኛን (ነፍስን) በሚገባ ይሰራልናል። በደንብ ራሳችን ላይ ለመስራት ከፈለግን በችግራችን ጊዜ በደንብ ራሳችን ላይ እንልፋ ነገ ሲያልፍ አጸያፊ ባሕርያት አብረው ይወድቃሉና። አንድ ታማኝ ሸይኽ ዘንድ የመጣ የቸገረው ሰው ሪዝቄ ተይዞብኛል የኾነ ዱዓ ያድርጉልኝ አላቸው። እርሳቸው ትንሽ ታገስ ግማሽ አመት ወይም አንድ አመት ከዚያ ያልፋል ይህ አሉት። ሰውዬውም ተጣድፎና ደስ ብሎት ከዚያስ በኋላ አላቸው፦ " ከዚያ በኋላማ ችግርህን በደንብ ትላመደዋለህ።" አሉት ይባላል። በ "ከራማ" ከችግር ለመላቀቅ ከመሞከር በላይ የሚበልጠው በችግር ጊዜ ነፍሲያን ማረቅ ነው። አቦ የማያልቅበት አላህ ከሁሉም ጸጋ ያቃምሰን፤ ከሚበልጠው መረዳት ይለግሰን! አሚይንን!

ከተወዳጁ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] በስተቀር ማንም ሰው በዱንያ ያንተ ቅርብ ወዳጅ ቢሆን እንኳን በቂያማ ቀን ስላንተ ሊጨነቅና ሊያስብ አይችልም። እርሳቸው ግን በቂያማ ቀን የፍጥረት ሁሉ መሸሸጊያ፣ የኡመታቸው መጠጊያ ናቸው። #ፊዳሁ አቢ ወኡሚ

የሰው ልጅ ሥራ ባገኝ ደስታን አገኛለሁ ብሎ ያስባል፣ ሲያገኝ ዱንያ ያው ናት፡፡ ቀጥሎም አግብቼ ከዚህ የብቸኝነት ሕይወት ብወጣ እኮ ደስታን እጎናፀፋለሁ ብሎ ያስባል፤ ሲያገባ ዱንያ አሁንም ያው ናት፡፡ ቀጥሎም ልጅ ባገኝ ይላል፤ ያገኛል፡፡ ዱንያ ያው ናት፡፡ በትምህርት፣ በገንዘብ ከፍ ቢልም ዱንያ አትሞላም፡፡ እሷ ያው ናት። የሰው ልጅ እንዲሁ እንዳለ እና እንደተመኘ ወደፊት አገኛታለሁ ብሎ ለደስታ እንደቀጠረ በመጨረሻም ቀብር ይገባል፡፡ ወዳጄ! ደስታህ ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው፤ ፈገግታህን ለነገ አትቅጠር፡፡ ለመሳቅ በይደር አታቆይ፡፡ ዛሬ ባለው ትንሽ ነገር ያልተደሠተ ነገ ብዙ ቢያገኝም አይደሠትም፡፡ ደስታ በሀብት መብዛት ውስጥ ሳይሆን በመብቃቃት ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ አላህን ጤና፣ እርጋታን፣ ሰላምን፣ እርካታን ለምኑት፡፡ ወዳጄዋ! ካልገቱት ምኞት አያረጅም፣ ካልገደቡት ፍላጎት አይቆምም። ዱንያ እንደየባህርውሃ ጨዋማ ናት፤ ከሷ በጠጡ ቁጥር ጥሟ ይበረታል፡፡ ግና የታቀበን አላህ ያቅበዋል፡፡ አላህ መብቃቃትን ይለግሰን። ቲስበሑ ዐላ ኸይር https://t.me/MuhammedSeidAbx

💡ለብቻህ ስትሆን የምትፈፅማቸው አምልኮዎች በዲን ላይ ለመፅናት ወሳኝ ናቸው!! ረሱል (📿) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿صلاةُ الرجلِ تطوُّعًا حيثُ لا يراهُ الناسُ تَعدِلُ صل
💡ለብቻህ ስትሆን የምትፈፅማቸው አምልኮዎች በዲን ላይ ለመፅናት ወሳኝ ናቸው!! ረሱል (📿) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿صلاةُ الرجلِ تطوُّعًا حيثُ لا يراهُ الناسُ تَعدِلُ صلاتَهُ على أعينِ الناسِ خمسًا وعشرينَ.﴾ “ሰውዬው ሰዎች ሳያዩት የሚሰግደው ትርፍ (የሱና ሰላት) ሰዎች አይተውት ከሚሰግደው ሰላት በሃያ አምስት ደረጃ ትስተካከላለች (ብልጫ አለው)።” 📚 ሶሂህ አልጃሚ: 3821 ▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️ ☑ በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦ 💬፦ https://bit.ly/4ayf0xJ 💬፦ https://bit.ly/486xnrS 💬፦ https://bit.ly/41zEZkk 📷፦ https://bit.ly/4arMbTx 💬፦ https://bit.ly/41tIUPv 📺፦ https://bit.ly/3UTTSwh

ሐጃ ሲኖርህ እጅህን ወደ ላይ በማንሳት ብቻ አይደለም አላህ የሚለመነው፡፡ ለአላህ ብቻ ብለን በምናደርጋቸው መልካም ነገሮችም ጭምር አላህ ይለመናል፡፡ የበደለንን ዐፉ በማለት፣ ለወላጆቻችን መልካም በመዋል፣ ሶደቃ በመስጠት፣ የቲምን በማስታወስ፣  የተቸገረን በመርዳት፣ ሰውን ወደ መልካም ነገር በመጥራት፣ ከመጥፎ ነገር በመከልከል፣  ግራ ለገባው መፍትሄ በመስጠት፣ ቁርኣን በመቅራት፣ ሰዎችን ከጭንቅ በመገላገል፣ በሰዎች ነፍስ ውስጥ ደስታን በመዝራት፣ ለሌላ ሰው ዱዓ በማድረግ፣ ስለ አላህ ባሮች በመጨነቅ እና በመሣሠሉት ደጋግ ሥራዎች ሁሉ ወደ አላህ በመቃረብ አላህ ይለመናል፡፡ ወዳጆቼ! ችግር ሲገጥማችሁ፣ መከራ ሲያገኛችሁ፣ ስትታመሙ፣ ግራ ሲገባችሁ፣ የሆነ ነገር ሲያሳስባችሁ … አላህን በልባችሁ አውሩት፤ መልካም ሥራዎችን በመሥራት ለምኑት፡፡ መልካም ቃል ሶደቃ ናት፣ ድብቅ ሶደቃ የአላህን ቁጣ ታበርዳለች፣ የታመመን ትፈውሳለች፣ መልካም ሥራ ከክፉ ኻቲማ ይጠብቃል፡፡ እናም ለልጁም፣ ለሀብቱም፣ ለኢማኑም፣ ለትዳሩም … ዱዓ ማድረግ ብቻ ሳይሆን ደጋግ ሥራዎችንም አብዙ፡፡ በየትኛው መልካም ሥራችሁ ሀሳባችሁ ሊሳካ እንደሚችል፣ ጭንቀታችሁ እንደሚወገድ አታውቁምና፡፡ መሳአል ኸይር MuhammedSeidAbx

ለሁሉም ካቅም በለይ ለሆኑብን ሁሉ ትእግስት'ና ተስፍን የመሰለ ድል የለም። ኢንሻ አላህ  እንታገሳለን። https://t.me/bilQURANnehyaa

للهم صل وسلم وبارك عليه، عدد خلقك.. ورضا نفسك، وزنة عرشك، ومداد كلماتك، اللهم صل وسلم وبارك عليه عدد ما خلقت، وعدد ما رزقت، وعدد ما أحييت، وعدد ما أمت. اللهم صل وسلم وبارك عليه في كل وقت وحين، وفي كل ملة ودين، وفي العالمين إلى يوم الدين . اللهم صل وسلم وبارك عليه كلما ذكرك الذاكرون، وكلما غفل عن ذكرك الغافلون، و عدد من صلى عليه ، وعدد من لم يصل عليه، وعدد أوراق الأشجار، وعدد مياه البحار، وعدد ما أظلم عليه الليل وما أضاء عليه النهار.