Tikvah-Education
Open in Telegram
📚 ይህ የቲክቫህ ኢዱኬሽን ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም ትምህርታዊ መረጃዎች የሚያገኙበት መድረክ ነው ። በዚህ ቻናል ትክክለኛ የትምህርት መረጃዎች እና ወቅታዊ ክስተቶች ይዳሰሱበታል ።
Show more1 916
Subscribers
+724 hours
+417 days
+13330 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+55
in 3 channels
August '26
+148
in 1 channels
Get PRO
July '26
+100
in 1 channels
Get PRO
June '26
+143
in 2 channels
Get PRO
May '26
+66
in 3 channels
Get PRO
April '26
+29
in 0 channels
Get PRO
March '26
+40
in 1 channels
Get PRO
February '26
+39
in 1 channels
Get PRO
January '26
+19
in 0 channels
Get PRO
December '25
+57
in 0 channels
Get PRO
November '25
+69
in 1 channels
Get PRO
October '25
+95
in 0 channels
Get PRO
September '25
+680
in 0 channels
Get PRO
August '25
+8
in 0 channels
Get PRO
July '250
in 0 channels
Get PRO
June '25
+2
in 0 channels
Get PRO
May '25
+2
in 0 channels
Get PRO
April '25
+4
in 0 channels
Get PRO
March '25
+2
in 0 channels
Get PRO
February '25
+1
in 0 channels
Get PRO
January '25
+3
in 0 channels
Get PRO
December '24
+3
in 0 channels
Get PRO
November '24
+30
in 1 channels
Get PRO
October '24
+8
in 0 channels
Get PRO
September '24
+5
in 0 channels
Get PRO
August '24
+12
in 0 channels
Get PRO
July '24
+5
in 0 channels
Get PRO
June '24
+5
in 0 channels
Get PRO
May '24
+1
in 0 channels
Get PRO
April '24
+1
in 0 channels
Get PRO
March '240
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 0 channels
Get PRO
January '240
in 0 channels
Get PRO
December '230
in 0 channels
Get PRO
November '230
in 0 channels
Get PRO
October '230
in 0 channels
Get PRO
September '230
in 0 channels
Get PRO
August '230
in 0 channels
Get PRO
July '230
in 0 channels
Get PRO
June '230
in 0 channels
Get PRO
May '230
in 0 channels
Get PRO
April '230
in 0 channels
Get PRO
March '230
in 0 channels
Get PRO
February '230
in 0 channels
Get PRO
January '230
in 0 channels
Get PRO
December '220
in 0 channels
Get PRO
November '220
in 0 channels
Get PRO
October '220
in 0 channels
Get PRO
September '220
in 0 channels
Get PRO
August '220
in 0 channels
Get PRO
July '220
in 0 channels
Get PRO
June '220
in 0 channels
Get PRO
May '220
in 0 channels
Get PRO
April '22
+4
in 0 channels
Get PRO
March '22
+2
in 0 channels
Get PRO
February '220
in 0 channels
Get PRO
January '22
+5
in 0 channels
Get PRO
December '210
in 0 channels
Get PRO
November '21
+2
in 0 channels
Get PRO
October '21
+3
in 0 channels
Get PRO
September '21
+3
in 0 channels
Get PRO
August '21
+4
in 0 channels
Get PRO
July '21
+7
in 0 channels
Get PRO
June '21
+24
in 0 channels
Get PRO
May '21
+289
in 0 channels
Get PRO
April '21
+1 015
in 0 channels
Get PRO
March '21
+1 148
in 0 channels
Get PRO
February '21
+1 452
in 0 channels
Get PRO
January '21
+1 957
in 0 channels
Get PRO
December '20
+6 331
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | +5 | |||
| 07 September | +7 | |||
| 06 September | +12 | |||
| 05 September | +14 | |||
| 04 September | +3 | |||
| 03 September | +3 | |||
| 02 September | +6 | |||
| 01 September | +5 |
Channel Posts
#ሰበር_ቅምሻ
10 ዓመታት ያለ እንቅልፍ ‼
እንቅልፍ በአይኑ ከዞረ 10 አመታት ማስቆጠሩን የሚናገረው ኢትዮጵያዊው ግለሰብ የዓለም ክብረ ወሰንን ለመስበር ማቀዱ መነጋገሪያ ሆኗል።
በዳውሮ ዞን ነዋሪ የሆነው አቶ ቁምላቸው አሰፋ ከሚያዝያ 18 2008 ዓ.ም ጀምሮ በተፈጠረ አጋጣሚ እንቅልፍ መተኛት እንዳልቻለ ተናግሯል።
በምሽት መኝታው ላይ አረፍ ለማለት ሲፈልግ የሰውነት ሙቀት እንደሚጨምርና ጎኑን ውጋት እንደሚሰማው የገለጸው ግለሰቡ፣ ይህ እንግዳ ጉዳይ የጤና እክል እየፈጠረበት ቢሆንም ለረጅም ጊዜ ያለ እንቅልፍ የመቆየት የዓለም ክብረ ወሰንን ለመስበር ማቀዱን ገልጿል።
ለጉዳዩ መፍትሄ ለማምጣት ከዘመናዊ እስከ ባህላዊ ህክምና እንዲሁም ሀይማኖታዊ መፍትሄዎችን መሞከሩን የገለፁት አቶ ቁምላቸው፣ የእንቅልፍ መድኃኒቶችም ቢሰጡትም እንቅልፍ ሊወስደው እንዳልቻለ ገልጿል።
የጤና ባለሙያዎች አስካሁን አስተያየት ባይሰጡበትም ጉዳዩ መነጋገሪያ ሆኗል ።
@Tikvah_edu
| 2 | "ተማሪዎችን አልመድብም" - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ከማንኛውም ወታደራዊና የትጥቅ እንቅስቃሴ ነፃ እንዲያደርጉ አስጠንቅቋል።
ሚኒስቴሩ ማስጠንቀቂያውን የሰጠው ለመቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ሲሆን፣ በካምፓሶቹ ውስጥ የወታደራዊ አካላት መኖራቸው የተማሪዎችንና የሰራተኞችን ደህንነት አደጋ ላይ እንደሚጥል ገልጾ፤ ዩኒቨርሲቲዎቹ ሙሉ በሙሉ ከወታደራዊ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸው ካልተረጋገጠ አዳዲስ ተማሪዎችን ወደ ተቋማቱ እንደማይመድብ አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ከላይ ባስቀመጠው ዝርዝር ገለፃ መሰረት ይህ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲዎቹ ከሲቪልና ከትምህርታዊ ተልዕኳቸው ውጭ ለወታደራዊ ዓላማ እየዋሉ መሆናቸውን እንደሚያመለክት ገልጿል።
ይህም የተማሪዎችን ሕይወት፣ ደኅንነትና ሰላማዊ የመማር ሁኔታ ሊያሰጋ እንደሚችል አስጠንቅቋል።
ሚኒስትሩ ለዩኒቨርሲቲዎቹ በዋናነት ሦስት መመሪያዎችን ሰጥቷል ፦
● በግቢዎቹ የሚገኙ የጦር ቁስለኞችን በአስቸኳይ ማስወጣት፤
● ሁሉም የዩኒቨርሲቲ ግቢዎች ከማንኛውም ወታደራዊና የትጥቅ እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸውን ማረጋገጥ፤
● የዩኒቨርሲቲ ሀብቶች ለወታደራዊ ዓላማ እንዳይውሉ ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ።
ደብዳቤው ከላይ ተያይዟል !
@Tikvah_edu | 287 |
| 3 | #MekelleUniversity
መቐለ ዩኒቨርሲቲ የነባር የቅድመ-ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት መስከረም 09 እና 10/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
በመሆኑም ነባር ተማሪዎች በተጠቀሱት ቀናት ሪፖርት እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
@tikvahuniversity | 294 |
| 4 | የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አሥራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን መግቢያ እና መመዝገቢያ መስከረም 05 እና 06/2019 ዓ.ም መሆኑን ካምፓሱ ገልጿል።
መስከረም 07 እና 08/2019 ዓ.ም በቅጣት ምዝገባ የሚከናወን ሲሆን፣ መስከረም 11/2019 ዓ.ም ትምህርት ይጀምራል ተብሏል።
@tikvahuniversity | 273 |
| 5 | #DebreBerhanUniversity
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ እና በመሃል-ሜዳ ካምፓስ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ነባር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ መደበኛ እና የኤክስቴንሽን ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም የምዝገባ ጊዜ መስከረም 07 እና 08/2019 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት ብቻ በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ያሳሰበው ዩኒቨርሲቲው፤ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ወደፊት ይገለጻል ብሏል።
@tikvahuniversity | 279 |
| 6 | በኢትዮጵያ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (የ12ኛ ክፍል) ፈተና 50% ውጤት ያስመዘገቡ ተፈታኞች ቁጥር በየዓመቱ መሻሻል እያሳየ እንደሚገኝ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባጋራው አኃዛዊ መረጃ አሳይቷል።
50% እና በላይ ያመጡ ተማሪዎች በ2014 ዓ.ም ከነበረበት 3.32 በመቶ፤ በ2018 ዓ.ም 12.85 በመቶ መድረሱ ተጠቁሟል።
ዘንድሮ የማለፊያ ውጤት ያመጡ የተፈጥሮ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች 16.62 በመቶ የደረሰ ሲሆን የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ገና 8.35 በመቶ ላይ ይገኛል።
@tikvahuniversity | 303 |
| 7 | ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ለተመዘገቡና ለፈተና ለተመረጡ ተማሪዎች ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና መስጠቱ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች፣ ሰኞ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity | 438 |
| 8 | መቱ ዩኒቨርሲቲ የነባር ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ መስከረም 07 እና 08/2019 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።
ትምህርት መስከረም 11/2019 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።
በ2019 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር መቱ ዩኒቨርሲቲ ለምትመደቡ የፍሬሽማን ተማሪዎች እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያገኛችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን በቀጣይ እንደሚገለፅ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
@tikvahuniversity | 390 |
| 9 | #ተጨማሪ
ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (UAT) ለመውሰድ የመፈተኛ ማዕከላችሁን አምቦ ዩኒቨርሲቲ የመረጣችሁ ፈተናው የሚሰጥበት ማዕከል በሀጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ፣ ፈተናው በፖሊ ካምፓስ የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል።
@tikvah_edu | 402 |
| 10 | #ሰበር_ቅምሻ
ከናይጄሪያ የተሰማው አስደንጋጭ ዜና‼️
ናይጄሪያውያን ወጣቶች ኩላሊታቸውን
በ1,100 ዶላር እየሸጡ ነው ።
በናይጄሪያ በተከሰተው የከፋ የኑሮ ውድነትና ድህነት ሳቢያ ወጣቶች ኩላሊታቸውን በ1,100 ዶላር እየሸጡ መሆኑ ተሰምቷል። የቀድሞው የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት አቲኩ አቡበከር ይህን አሳዛኝ ሁኔታ በማንሳት ጥልቅ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የችግሩ መንስኤ እና ወቅታዊ ሁኔታ፡
● የምግብ፣ የትራንስፖርትና የቤት ኪራይ ዋጋዎች እጅግ መናራቸው ለዚህ ችግር ዳርጓቸዋል።
● ፖሊስ ሁለት የህክምና ባለሙያዎችን ጨምሮ በአራት ግለሰቦች ላይ ህገ-ወጥ የሰዎች አካል ዝውውር ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
● ምንም እንኳን ሪፖርቶቹ ሙሉ በሙሉ ባይረጋገጡም፣ የኢኮኖሚ ቀውሱ የሰውን አካል እስከ መሸጥ ማድረሱ ሁኔታውን እጅግ አሳሳቢ አድርጎታል።
የቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት መልእክት ፡ "ወጣቶች መሸጥ የሚገባቸው አካላቸውን ሳይሆን የፈጠራ ሃሳቦቻቸውን ሊሆን ይገባል" ሲሉ አቲኩ አቡበከር አሳስበዋል።
@Tikvah_edu | 431 |
| 11 | #AAU #UAT
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (UAT) ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
ፈተናው በተጠቀሱት ቀናት በሦስት ፈረቃ ማለትም ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ፈረቃ 2: ረፋድ ከ5:30-8:00 ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ8:30-11:00 የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
መርሐግብሩን እዚህ በጥንቃቄ ይመልከቱ። የመፈተኛ ማዕከልዎን የመፈተኛ ሰዓትዎን በደንብ ይመልከቱ።
🔔 ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ አመልካቾች ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የተዘዋወራችሁ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከል የመረጡ ማየት የተሳናቸው አመልካቾችች በሙሉ ዋናው ግቢ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ላብ 1 ማክሰኞ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም በፈረቃ 3 ፈተናቸውን የሚወስዱ መሆኑ ተገልጿል፡፡
@tikvah_edu | 466 |
| 12 | +1 UAT TEST SCHEDULE
👍 @keleme_2013 | 403 |
| 13 | 1_UAT_Test_Taker_Schedule_–_AAU_Test_Site_–_September_7–8,_2026.xlsx | 2 |
| 14 | #update
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ያወጣው የፈተና ፕሮግራም (schedule) ።
@tikvah_edu | 417 |
| 15 | #update
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ያወጣው የፈተና ፕሮግራም (schedule) ።
@tikvah_edu | 1 |
| 16 | #NGATResult
ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።
ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et
ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'NGAT Results' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
@tikvahuniversity | 415 |
| 17 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመሔድ ከላይ በምስሉ የተገለፁትን አራት የትራንስፖርት አቅጣጫ አማራጭ መንገዶች ይጠቀሙ።
@tikvah_edu | 378 |
| 18 | #ጥቆማ
እንግሊዝኛ ቋንቋን ያለምንም ክፍያ በማንኛውም ጊዜ እና በየትኛውም ቦታ ሆነው ይማሩ!
ትምህርት ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የመምህራን እና የተማሪዎችን እንግሊዘኛ ቋንቋን ለማሻሻል የሚያግዝ ፖርታል ይጠቀሙ፡፡
ፖርታሉ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ለሁሉም የክፍል ደረጃዎች የተዘጋጀ ሲሆን፤ በቀላሉ ለመረዳት በሚቻሉ በድምፅ፣ በፅሁፍ እና በምስል በተቀናበሩ ማስተማሪያዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋን ለማሻሻል የሚያስችል ትምህርት ያገኛሉ።
ፖርታሉን ለመጠቀም ኢንተርኔት የሚያስፈልግ ቢሆንም ገንዘብ የማይቆርጥ ሲሆን፤ በስማርት ስልክ፣ ስማርት ቴሌቪዥን፣ በታብሌት እና በኮምፒውተር በማንኛውም የዌብ መፈለጊያ (browser) መጠቀም ይቻላል፡፡
ፖርታሉን ለማግኘት 👇
http://learn-english.moe.gov.et
@tikvah_edu | 394 |
| 19 | #ሰበር_ቅምሻ
ለስራ አጦች ደመወዝ መክፈል ተጀመረ ‼️
አልጀርያ ስራ አጥ ለሆኑ ወጣቶቿ ደምሞዝ መክፈል ጀመረች ። የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር አልጄሪያ ለዜጎቿ የዘረጋችው አስደናቂ የማህበራዊ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመላው አፍሪካ ከፍተኛ አድናቆትን እያተረፈ ይገኛል።
ሀገሪቱ የተፈጥሮ ሀብቷን እና የኢኮኖሚ አቅሟን ቀጥታ የዜጎቿን ህይወት ለማሻሻል በሚያስችሉ ዘመናዊ ውሳኔዎች ላይ በመመደብ በአፍሪካ አዲስ ምሳሌነቷን እያሳየች ነው።
ሀገሪቷ ስራ ለሌላቸው ወጣቶች በወር 96 ዶላር ድጋፍ ታደርጋለች።
ይህ ድጋፍ ወጣቶች ስራ እስኪያገኙ ድረስ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን እንዲሸፍኑ የሚያስችል ሲሆን ከገንዘቡ በተጨማሪ ነፃ የጤና መድህን አገልግሎትም ያካትታል ተብሏል።
በወር ከ 216 ዶላር በታች የሚያገኙ ዜጎች ምንም አይነት የገቢ ግብር እንዳይከፍሉ አድርጋለች።
አነስተኛ የደመወዝ ወለል ወደ 170 ዶላር ከፍ በማድረግ የዜጎችን የመግዛት አቅም እንዲሻሻል አድርጋለች።
ከዚህ በተጨማሪም ለህዝቧ በሙሉ ነፃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት አረጋግጣለች።
አልጄሪያ ግዙፍ የተፈጥሮ ጋዝ እና የሃይል አቅሟን በመጠቀም 100 በመቶ ለሚጠጉ ዜጎቿ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ እና ነፃ የሆነ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማድረስ ችላለች።
ይህም በገጠር እና በከተማ የሚኖሩ ዜጎቿ በእኩል መሰረታዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል ነው የተባለው።
©️ African folder
@Tikvah_edu | 386 |
| 20 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
በ2019 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች የመግቢያ ፈተና ለመፈተን በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።
በመሆኑም ያመለከታችሁ በሙሉ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎቹ አሳውቀዋል።
ተፈታኞች በዕለቱ ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያዎች መገኘት ይጠበቅባችኋል። የሞባይል ስልክ እንዲሁም ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የአድሚሽን ካርድ እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
@tikvah_edu | 388 |
