Tikvah-Education
الذهاب إلى القناة على Telegram
📚 ይህ የቲክቫህ ኢዱኬሽን ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም ትምህርታዊ መረጃዎች የሚያገኙበት መድረክ ነው ። በዚህ ቻናል ትክክለኛ የትምህርት መረጃዎች እና ወቅታዊ ክስተቶች ይዳሰሱበታል ።
إظهار المزيد1 903
المشتركون
+1324 ساعات
+257 أيام
+11430 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
سبتمبر '26
سبتمبر '26
+41
في 3 قنوات
أغسطس '26
+148
في 1 قنوات
Get PRO
يوليو '26
+100
في 1 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+143
في 2 قنوات
Get PRO
مايو '26
+66
في 3 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+29
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+40
في 1 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+39
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '26
+19
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+57
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+69
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+95
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+680
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+8
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '250
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+2
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+2
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+2
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+1
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+3
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+3
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+30
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+8
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+5
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+12
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+5
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+5
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+1
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+1
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '240
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '240
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '240
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '230
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '230
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '230
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '230
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '230
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '230
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '230
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '230
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '230
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '220
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '220
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '220
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '220
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '220
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '220
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '220
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '220
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+2
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '220
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+5
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '210
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+2
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+3
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+3
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+4
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+7
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+24
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+289
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+1 015
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+1 148
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+1 452
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+1 957
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+6 331
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 06 سبتمبر | +10 | |||
| 05 سبتمبر | +14 | |||
| 04 سبتمبر | +3 | |||
| 03 سبتمبر | +3 | |||
| 02 سبتمبر | +6 | |||
| 01 سبتمبر | +5 |
منشورات القناة
ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 የትምህርት ዘመን በፌዴራል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር ለተመዘገቡና ለፈተና ለተመረጡ ተማሪዎች ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና መስጠቱ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ ለፈተና ተመርጣችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተና ያልተፈተናችሁ ተማሪዎች፣ ሰኞ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፈተና መስጫ ማዕከል በመገኘት መፈተን የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በድጋሜ መፈተን የማይቻል መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
| 2 | መቱ ዩኒቨርሲቲ የነባር ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ መስከረም 07 እና 08/2019 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።
ትምህርት መስከረም 11/2019 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።
በ2019 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር መቱ ዩኒቨርሲቲ ለምትመደቡ የፍሬሽማን ተማሪዎች እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያገኛችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን በቀጣይ እንደሚገለፅ ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
@tikvahuniversity | 179 |
| 3 | #ተጨማሪ
ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (UAT) ለመውሰድ የመፈተኛ ማዕከላችሁን አምቦ ዩኒቨርሲቲ የመረጣችሁ ፈተናው የሚሰጥበት ማዕከል በሀጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ፣ ፈተናው በፖሊ ካምፓስ የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል።
@tikvah_edu | 300 |
| 4 | #ሰበር_ቅምሻ
ከናይጄሪያ የተሰማው አስደንጋጭ ዜና‼️
ናይጄሪያውያን ወጣቶች ኩላሊታቸውን
በ1,100 ዶላር እየሸጡ ነው ።
በናይጄሪያ በተከሰተው የከፋ የኑሮ ውድነትና ድህነት ሳቢያ ወጣቶች ኩላሊታቸውን በ1,100 ዶላር እየሸጡ መሆኑ ተሰምቷል። የቀድሞው የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዚዳንት አቲኩ አቡበከር ይህን አሳዛኝ ሁኔታ በማንሳት ጥልቅ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የችግሩ መንስኤ እና ወቅታዊ ሁኔታ፡
● የምግብ፣ የትራንስፖርትና የቤት ኪራይ ዋጋዎች እጅግ መናራቸው ለዚህ ችግር ዳርጓቸዋል።
● ፖሊስ ሁለት የህክምና ባለሙያዎችን ጨምሮ በአራት ግለሰቦች ላይ ህገ-ወጥ የሰዎች አካል ዝውውር ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
● ምንም እንኳን ሪፖርቶቹ ሙሉ በሙሉ ባይረጋገጡም፣ የኢኮኖሚ ቀውሱ የሰውን አካል እስከ መሸጥ ማድረሱ ሁኔታውን እጅግ አሳሳቢ አድርጎታል።
የቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት መልእክት ፡ "ወጣቶች መሸጥ የሚገባቸው አካላቸውን ሳይሆን የፈጠራ ሃሳቦቻቸውን ሊሆን ይገባል" ሲሉ አቲኩ አቡበከር አሳስበዋል።
@Tikvah_edu | 315 |
| 5 | #AAU #UAT
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (UAT) ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
ፈተናው በተጠቀሱት ቀናት በሦስት ፈረቃ ማለትም ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ፈረቃ 2: ረፋድ ከ5:30-8:00 ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ8:30-11:00 የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
መርሐግብሩን እዚህ በጥንቃቄ ይመልከቱ። የመፈተኛ ማዕከልዎን የመፈተኛ ሰዓትዎን በደንብ ይመልከቱ።
🔔 ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ አመልካቾች ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የተዘዋወራችሁ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከል የመረጡ ማየት የተሳናቸው አመልካቾችች በሙሉ ዋናው ግቢ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ላብ 1 ማክሰኞ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም በፈረቃ 3 ፈተናቸውን የሚወስዱ መሆኑ ተገልጿል፡፡
@tikvah_edu | 364 |
| 6 | +1 UAT TEST SCHEDULE
👍 @keleme_2013 | 333 |
| 7 | 1_UAT_Test_Taker_Schedule_–_AAU_Test_Site_–_September_7–8,_2026.xlsx | 2 |
| 8 | #update
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ያወጣው የፈተና ፕሮግራም (schedule) ።
@tikvah_edu | 339 |
| 9 | #update
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ያወጣው የፈተና ፕሮግራም (schedule) ።
@tikvah_edu | 1 |
| 10 | #NGATResult
ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።
ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et
ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'NGAT Results' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
@tikvahuniversity | 350 |
| 11 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመሔድ ከላይ በምስሉ የተገለፁትን አራት የትራንስፖርት አቅጣጫ አማራጭ መንገዶች ይጠቀሙ።
@tikvah_edu | 318 |
| 12 | #ጥቆማ
እንግሊዝኛ ቋንቋን ያለምንም ክፍያ በማንኛውም ጊዜ እና በየትኛውም ቦታ ሆነው ይማሩ!
ትምህርት ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የመምህራን እና የተማሪዎችን እንግሊዘኛ ቋንቋን ለማሻሻል የሚያግዝ ፖርታል ይጠቀሙ፡፡
ፖርታሉ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ ለሁሉም የክፍል ደረጃዎች የተዘጋጀ ሲሆን፤ በቀላሉ ለመረዳት በሚቻሉ በድምፅ፣ በፅሁፍ እና በምስል በተቀናበሩ ማስተማሪያዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋን ለማሻሻል የሚያስችል ትምህርት ያገኛሉ።
ፖርታሉን ለመጠቀም ኢንተርኔት የሚያስፈልግ ቢሆንም ገንዘብ የማይቆርጥ ሲሆን፤ በስማርት ስልክ፣ ስማርት ቴሌቪዥን፣ በታብሌት እና በኮምፒውተር በማንኛውም የዌብ መፈለጊያ (browser) መጠቀም ይቻላል፡፡
ፖርታሉን ለማግኘት 👇
http://learn-english.moe.gov.et
@tikvah_edu | 334 |
| 13 | #ሰበር_ቅምሻ
ለስራ አጦች ደመወዝ መክፈል ተጀመረ ‼️
አልጀርያ ስራ አጥ ለሆኑ ወጣቶቿ ደምሞዝ መክፈል ጀመረች ። የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር አልጄሪያ ለዜጎቿ የዘረጋችው አስደናቂ የማህበራዊ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመላው አፍሪካ ከፍተኛ አድናቆትን እያተረፈ ይገኛል።
ሀገሪቱ የተፈጥሮ ሀብቷን እና የኢኮኖሚ አቅሟን ቀጥታ የዜጎቿን ህይወት ለማሻሻል በሚያስችሉ ዘመናዊ ውሳኔዎች ላይ በመመደብ በአፍሪካ አዲስ ምሳሌነቷን እያሳየች ነው።
ሀገሪቷ ስራ ለሌላቸው ወጣቶች በወር 96 ዶላር ድጋፍ ታደርጋለች።
ይህ ድጋፍ ወጣቶች ስራ እስኪያገኙ ድረስ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን እንዲሸፍኑ የሚያስችል ሲሆን ከገንዘቡ በተጨማሪ ነፃ የጤና መድህን አገልግሎትም ያካትታል ተብሏል።
በወር ከ 216 ዶላር በታች የሚያገኙ ዜጎች ምንም አይነት የገቢ ግብር እንዳይከፍሉ አድርጋለች።
አነስተኛ የደመወዝ ወለል ወደ 170 ዶላር ከፍ በማድረግ የዜጎችን የመግዛት አቅም እንዲሻሻል አድርጋለች።
ከዚህ በተጨማሪም ለህዝቧ በሙሉ ነፃ የኤሌክትሪክ አቅርቦት አረጋግጣለች።
አልጄሪያ ግዙፍ የተፈጥሮ ጋዝ እና የሃይል አቅሟን በመጠቀም 100 በመቶ ለሚጠጉ ዜጎቿ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ እና ነፃ የሆነ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማድረስ ችላለች።
ይህም በገጠር እና በከተማ የሚኖሩ ዜጎቿ በእኩል መሰረታዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል ነው የተባለው።
©️ African folder
@Tikvah_edu | 335 |
| 14 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
በ2019 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች የመግቢያ ፈተና ለመፈተን በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።
በመሆኑም ያመለከታችሁ በሙሉ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎቹ አሳውቀዋል።
ተፈታኞች በዕለቱ ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያዎች መገኘት ይጠበቅባችኋል። የሞባይል ስልክ እንዲሁም ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የአድሚሽን ካርድ እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
@tikvah_edu | 337 |
| 15 | ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሰባት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤታቸው በስህተት Disqualified እንደተባለባቸው በመግለፅ፣ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ጽ/ቤት ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁን ገልጿል።
ሰባቱም ተማሪዎች ለአገልግሎቱ ማመልከት ስለሚገባቸው፣ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ መረጃው እንዲደርሳቸው ጠይቋል፡፡
ተማሪዎቹ (3 የማኅበራዊ ሳይንስ እና 4 የተፈጥሮ ሳይንስ) ፈተናቸውን በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የወሰዱ ናቸው።
(ጥር 11, 2022 የተከፈተና 18,853 ተከታዮች ያሉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር የቴሌግራም ገጽ ትናንት ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ያጋራው መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናቸውን የወሰዱና ውጤታቸው Disqualified የተባለባቸው እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ። በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተገለፀው አይነት መሠል ግድፈት ሊኖር ስለሚችል ዩኒቨርሲቲዎች በድጋሜ የሪሚዲያል ተፈታኞችን ውጤት እንዲያዩ ይጠየቃሉ።
@tikvahuniversity | 387 |
| 16 | የመውጫ ፈተና አፈጻጸም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
መንግሥት በመውጫ ፈተና ምክንያት ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወጪ መጋራት በሁለት ዓመት ብቻ 8 ቢሊዮን ብር ማጣቱን አንድ ጥናት አሳየ፡፡
የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀውና የመውጫ ፈተና ወስደው ያላለፉና ሰርተፍኬት ባለማግኘታቸው ምክንያት በኮንትራትም ሆነ በቋሚ መቀጠር ካልቻሉ ተማሪዎች፣ መንግሥት በሁለት ዓመት ብቻ ያገኝ የነበረውን ስምንት ቢሊዮን ብር እንዳጣ አንድ ጥናት አረጋገጠ፡፡
መንግሥት የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ እንዳጣ የተገለፀው፤ ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ዩኒቨርሲቲ እና ከሽያሾኔ ተቋም ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አውደ ጥናት ላይ ነው፡፡
የመውጫ ፈተና በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ውስጥ ያለው አፈጻጸም፣ የታዩ ችግሮች እና የወደፊት መፍትሔ ምን ሊሆን እንደሚገባ ትኩረት ያደረገ ጥናት በመድረኩ ላይ ቀርቧል፡፡
ጥናቱን ያደረገው ቡድን ከአዲስ አበባ፣ ከሐዋሳ እና ከጅማ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም ከትምህርት ሚኒስቴር የተውጣጡ አባላት ያሉት መሆኑን፣ ጥናቱን ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ማዕከል አባል አብርሃም ቱሉ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡
በ2016 እና 2017 ዓ.ም. የመውጫ ፈተና ከሰጡ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከ128,000 በላይ ተማሪዎች መውደቃቸውንና ከተፈተኑት ውስጥ ከ52.7 ከመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ማለፋቸው በጥናቱ ተመላክቷል፡፡
የግል የትምህርት ተቋማት ደግሞ 14.8 በመቶ ብቻ ተማሪዎች ማለፋቸውን፣ በዚህም ትልቁ የመውደቅ ምጣኔ የተመዘገበው በግል የትምህርት ተቋማት መሆኑን ጥናቱ አሳይቷል፡፡ ሦስት የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በምንም ዓይነት የትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎችን አለማሳለፋቸው በመረጃ መረጋገጡን የጥናቱ አቅራቢ ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ በሁለት ዓመታት ውስጥ የተመዘገበው የማለፍ ምጣኔ 33.1 በመቶ ሲሆን፣ 66.9 በመቶ የሚሆነው ደግሞ የመውደቅ ምጣኔ መሆኑን በጥናቱ ግኝት መካተቱ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም የመውጫ ፈተና አልፈው ተቀጥረው ቢሆን በሁለት ዓመት ውስጥ በትንሹ መንግሥት ከወጪ መጋራት ያገኝ የነበረው ከስምንት ቢሊዮን ብር በላይ መመለስ እንዳልቻሉ ተገልጿል፡፡
ተማሪዎቹ የሚማሩት ትምህርት በመጀመሪያ ምርጫቸው ከሆነ የማለፍ ምጣኔያቸው ከፍተኛ መሆኑን ለአብነትም የጤና፣ የኢንጅነሪንግና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ከፍተኛ እንደሆነ፣ በተቃራኒው የማኅበራዊ ሳይንስ፣ የቢዝነስና የትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ዝቅተኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
64 በመቶ የሚሆኑት የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች ሰርተፍኬት ስለሌላቸው በጊዜያዊነትም ሆነ በቋሚነት መቀጠር እንዳልቻሉ፣ በዚህ ምክንያት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መግባት በቤተሰብ፣ በአካባቢና በጓደኛ የማሸማቀቅ ሁኔታ በልጆቹ ላይ እንደሚደርስ፣ ከ94 በመቶ በላይ የሚሆኑት ደግሞ በቤተሰብ ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ጥናቱ በተመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች በአብዛኛው ምንም ዓይነት የመውጫ ፈተና በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች የመስጠት ሁኔታ እንደማይታይና ከዚያ ይልቅ በተመረጡ ፕሮግራሞች ላይ ብቻ ተግባራዊ አንደሚደረግ አቅራቢው አስረድተዋል፡፡
በመሆኑም ኢትዮጵያ ብቻ በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የመውጫ ፈተና ተግባራዊ ማድረግ የጀመረች አገር መሆኗንና፣ ትምህርት ሚኒስቴርም ወደ እዚህ ሁኔታ የገባው ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች ለሥራ ቅጥር ብቁ ባለመሆናቸው፣ ይህን ያስከተለውን የትምህርት ጥራት ለማሻሻል ኃላፊነቱን በመውሰዱን ነው ብለዋል፡፡
6,ዐ3ዐ ተማሪዎች በጥናቱ መሳተፋቸውንና ከእነዚህ ውስጥ 1,38ዐ የሚሆኑት ከአንድ እስከ አምስት ጊዜ የወደቁ መሆናቸውን እንዲሁም 78 የመንግሥት እና የግል ተቋማት፣ 13 የመንግሥት እና ሰባት የግል፣ በአጠቃላይ 20 ዩኒቨርሲቲዎች በጥናቱ መካተታቸው ተገልጿል፡፡ #ሪፖርተር
@tikvahuniversity | 809 |
| 17 | لا يوجد نص... | 756 |
| 18 | What do you think your result will be ❔ | 375 |
| 19 | በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ይፋ መደረጉ ይታወሳል ።
ዘንድሮ የሚገቡ ተማሪዎችም ቁጥር በመንግሥትም ሆነ በግል የዩንቨርሲቲ ተቋም ከ 130,000 እንደሚያንስ ተገልጿል ።
በመንግሥት ዩኒቨርስቲ የሪሜዲያል ፕሮግራም እድል የሚያገኙት ደግሞ ከ 50,000 በታች እንደሚሆኑ ይጠበቃል ።
መግቢያ ነጥቡ ከ38% (224/600) በላይ እንደሚሆንም ፍንጭ ተሰጥቷል ።
ከዚህ በፊት በነበረው የሪሜዲያል ፕሮግራም ለተማሩ በማዕከል ከ70 በመቶ እንዲሁም በተቋማት ከ30 በመቶ በተሰጡ ምዘናዎች 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች የፍሬሽማን ኮርስ እንዲማሩ እና የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያላስመዘገቡ ግን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች ለመከታተል የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ ይፋ መደረጉ ይታወሳል ፡፡
በ2018 ዓ.ም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት እና የዩንቨርስቲ ምደባ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ።
@Tikvah_edu | 359 |
| 20 | የተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምደባ - አዲስ ስርዓት ማሻሻያ እቅድ !
ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን ለማዘመን ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ እንደገለፁት፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስብጥር ብዝሃነትን ባካተተ፣ መቻቻልንና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪዎች ምደባና ዝውውር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚዘረጋ ገልፀዋል።
ከበጀት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደበላቸውን በጀት ለታቀደለት ዓላማ ብቻ በቁጠባና በተጠያቂነት መንፈስ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረህይወት (ፕ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርስቲዎቹ በስምምነት ተማሪዎችን ሲያዘዋውሩ ለትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
@tikvah_edu | 477 |
