en
Feedback
የንባብ ዓለም /Philosophy/

የንባብ ዓለም /Philosophy/

Open in Telegram

ፍልስፍና እውነትን በመፈለግ- ሀሳዊ እምነቶችን በማጋለጥ እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል። በዚ ቻናል መፅሐፍቶችን እንጋብዛለን፣ ዓለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች፤ ርዕዮት ዓለሞች፤ ሃይማኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃ ይዳሰሳሉ። ሀሳብ አስተያየት discussion group (https://t.me/yenbabalem111) ወይም @kaallua11 ላይ ያስቀምጡልን።

Show more
5 382
Subscribers
+1024 hours
+507 days
+9930 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+98
in 2 channels
August '26
+184
in 1 channels
Get PRO
July '26
+126
in 0 channels
Get PRO
June '26
+133
in 1 channels
Get PRO
May '26
+127
in 0 channels
Get PRO
April '26
+108
in 0 channels
Get PRO
March '26
+149
in 0 channels
Get PRO
February '26
+111
in 2 channels
Get PRO
January '26
+126
in 0 channels
Get PRO
December '25
+198
in 1 channels
Get PRO
November '25
+219
in 0 channels
Get PRO
October '25
+166
in 0 channels
Get PRO
September '25
+164
in 1 channels
Get PRO
August '25
+92
in 1 channels
Get PRO
July '25
+155
in 5 channels
Get PRO
June '25
+103
in 1 channels
Get PRO
May '25
+190
in 3 channels
Get PRO
April '25
+108
in 0 channels
Get PRO
March '25
+124
in 1 channels
Get PRO
February '25
+241
in 2 channels
Get PRO
January '25
+389
in 1 channels
Get PRO
December '24
+337
in 1 channels
Get PRO
November '24
+232
in 0 channels
Get PRO
October '24
+340
in 0 channels
Get PRO
September '24
+252
in 1 channels
Get PRO
August '24
+328
in 0 channels
Get PRO
July '24
+134
in 1 channels
Get PRO
June '24
+186
in 0 channels
Get PRO
May '24
+201
in 0 channels
Get PRO
April '24
+394
in 1 channels
Get PRO
March '24
+720
in 1 channels
Get PRO
February '24
+220
in 0 channels
Get PRO
January '24
+91
in 0 channels
Get PRO
December '23
+185
in 2 channels
Get PRO
November '23
+140
in 1 channels
Get PRO
October '23
+108
in 0 channels
Get PRO
September '23
+19
in 0 channels
Get PRO
August '23
+21
in 0 channels
Get PRO
July '23
+182
in 0 channels
Get PRO
June '23
+77
in 0 channels
Get PRO
May '23
+55
in 0 channels
Get PRO
April '23
+115
in 0 channels
Get PRO
March '23
+135
in 0 channels
Get PRO
February '23
+54
in 0 channels
Get PRO
January '23
+79
in 0 channels
Get PRO
December '22
+75
in 0 channels
Get PRO
November '22
+109
in 0 channels
Get PRO
October '22
+227
in 0 channels
Get PRO
September '22
+85
in 0 channels
Get PRO
August '22
+96
in 0 channels
Get PRO
July '22
+102
in 0 channels
Get PRO
June '22
+124
in 0 channels
Get PRO
May '22
+86
in 0 channels
Get PRO
April '22
+103
in 0 channels
Get PRO
March '22
+99
in 0 channels
Get PRO
February '22
+157
in 0 channels
Get PRO
January '22
+166
in 0 channels
Get PRO
December '21
+279
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
10 September0
09 September+11
08 September+5
07 September+10
06 September+13
05 September+4
04 September+42
03 September+8
02 September+3
01 September+2
Channel Posts
# የ'ኔ መጨረሻ ●•• አምና ወዳጆቿ...         ሙዚቃ መዉደዷን ሲያወጉ ሰምቼ         ካሴት አዉጥቻለሁ አመቱን ለፍቼ         ''አንባቢ ነች'' ሲሉ ሆኛለሁ ፀሀፊ         ጥቂት ጠብቄያለሁ ሆኜ ልብስ ሰፊ         አጥር ለማጠንከር ግንበኛ ሆኛለሁ      እግሯንም ለመንካት ጫማ ጠርጌያለሁ እሷን ለመማረክ ቀን ይገኛል ብዬ ያልሆንኩትን ስሆን እሷን ተከትዬ ዛሬ ዕድሉ ቀንቶኝ ከፊቷ ቆሜያለሁ ሰርጓን ልቀርፅላት ካሜራ ይዣለሁ። 😭😝

2
ነገ ለማንም አልተፈቀደችም!" በዚህች ምድር ላይ ሁላችንም እንግዶች ነን። ነገ ለሁላችንም የተሰጠች ዋስትና አይደለችም፤ ስለዚህ በልባችሁ ያሰባችሁት ነገር ካለ አሁኑኑ አድርጉት። ይቅርታ መጠየቅ ከፈለጋችሁ—አሁኑኑ ጠይቁ። የናፈቃችሁት ሰው ካለ—አሁኑኑ ንገሯቸው። ለቤተሰቦቻችሁና ለጓደኞቻችሁ፦ እንደምትወዷቸውና የእናንተ ስለሆኑ ምን ያህል ደስተኛ እንደሆናችሁ አሁኑኑ ንገሯቸው። "የእኔ ስለሆንክ/ሽ ደስ ይለኛል" የሚለው ቃል ትልቅ ስንቅ ነው። ተስፋ ሁኑላቸው፦ ብዙዎች በውስጣቸው ምን ዓይነት ጦርነት እያለፉ እንደሆነ አናውቅም። በተለይ ወንዶች ስሜታቸውን አውጥተው ስለማይናገሩ፣ በአእምሯቸው ውስጥ የሚጋፈጡት "ሲኦል" ከባድ ነው። ሳትረፍዱ "ጠንካራ ነህ" በሏቸው። ትንሿ ደግነታችሁ አንድን ሰው ህይወቱን ከማጥፋት ሊታደገው፣ ትንሽ የመኖር ተስፋም ሊሰጠው ይችላል። ምክንያቱም ነገ የራሷ የሆነ ሌላ እቅድ ሊኖራት ይችላል! "መልካም_ሰኞ!" ከራስ ወደ ራስ! (መልካም ቀን) 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
615
3
#ያልተፈታ_እንቆቅልሽ በአንድ ወቅት አንድ በጣም የሚናገርና ፈጣሪ የለም ብሎ የሚያምን ጸጉር አስተካካይ ነበር... አንድ ቀን አንድ ትሁት ቄስ ጸጉራቸውን ሊስተካከሉ ወደዚህ ጸጉር ቤት ገቡ። አስተካካዩ ሥራውን እየሰራ፣ እንደ ልማዱ አንድ ሁለት ወሬ ጀመረ... "አባቴ እኔ እኮ ፈጣሪ አለ የሚለውን ነገር አላምነውም!" አላቸው፡፡ ቄሱም በመገረም "ለምን ልጄ?" ብለው ጠየቁት... አስተካካዩም በኩራት እንዲህ አለ፦ "ወደ ውጭ ወጥተው መንገዱን ይመልከቱ! ፈጣሪ ቢኖር ኖሮ ይሄ ሁሉ በሽተኛ ይኖር ነበር... ይሄ ሁሉ የታረዘና የተራበ ሕፃን ይታይ ነበር? ይሄ ሁሉ ግፍና መከራ በምድር ላይ ይፈጸም ነበር? አፍቃሪ የሆነ አምላክ ቢኖር ኖሮ ይሄን ሁሉ መከራ አይፈቅድም ነበር... ስለዚህ ፈጣሪ የለም!" ብሎ በድፍረት ተናገረ። ቄሱም በዚያ ሰዓት ክርክር ውስጥ ሳይገቡ ጸጉራቸውን ተስተካክለው፣ ክፍያቸውን ከፍለው ወጡ... ልክ ከጸጉር ቤቱ በር ላይ እንደወጡ፣ ቄሱ አንድ ሰው አዩ፡፡ ያ ሰው ጸጉሩ በጣም አድጎና ተንጨባርሮ፣ ጺሙም ተዘበራርቆ ፊቱ ሁሉ ተሸፍኖ ነበር... ቄሱ ወዲያውኑ ወደ ጸጉር ቤቱ ተመልሰው ገቡ፡፡ ቄሱም አስተካካዩን ጠርተው፦ "ልጄ ሆይ፣ አሁን አንድ እውነት ገባኝ፤ በዚህ #ሰፈር ላይ ጸጉር አስተካካይ የሚባል ሰው የለም" አሉት። አስተካካዩ እየሳቀ "ምን ማለትዎ ነው አባቴ... እኔ እኮ እዚህ ቆሜ ጸጉርዎን አሁን አስተካከልኩልዎት። እንዴት የለም ይላሉ?" አላቸው... ቄሱም ወደ ውጪ ጠቁመው፦ "አየህ፣ ጸጉር አስተካካይ ቢኖር ኖሮ ያ ሰውዬ ጸጉሩ እንደዛ ተንጨባርሮ በመንገድ ላይ ይሄድ ነበር? ጸጉር አስተካካይ ቢኖር ኖሮ እኮ ሁሉም ሰው ጸጉሩ የተስተካከለ ይሆን ነበር" አሉት። አስተካካዩም "ኧረ አባቴ! እኔ እኮ አለሁ። ችግሩ ያ ሰውዬ ወደ እኔ መጥቶ አስተካክለኝ ስላላለን እንጂ፣ እኔ እኮ ዝግጁ ነኝ" አለ። ቄሱም ፈገግ አሉና "በትክክል! ፈጣሪም አለ! ችግሩ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መጥተው እርዳን፣ ማረን ስለማይሉት እንጂ፣ ፈጣሪ ሁልጊዜም ዝግጁ ነው! አሉት..." አስተካካዩም ዝም ብሎ ማሰብ ጀመረ፤ "እና ሰው ምን ነካው፣ ይሄንን ሂዎት መርጦ የሚኖረው አለ?" ቄሱም "እሱ ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው ልጄ፣ በዓለማችን ላይ ላለው መከራ ሁሉ ተጠያቂው ፈጣሪ አይደለም..." ብለውት ሄዱ። #ጠቅለል ስናደርገው ለስንፍና፣ ለውድቀት ምክንያታችን ፈጣሪ የሰጠን እድላችን አይደለም! የምንደበቅበት፣ የአለመቻል መደበቂያ ያደረግነው እኛ ነን! ከሰበበኝነት ወጠን መንገዳችንን እናስተካክል! አላማችንን እንወጥን፤ ግፉበት! ይሄ እራስን ማታለል (self-deception) ነው!! ነቃ በል ወንድሜ /እህቴ🤝 #መልካም_ቀን🤝 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 If you like, Share to your friends @yenbabalem1 @yenbabalem1
924
4
...."ማንኛዉም ጠንካራ ሰው የጥንካሬዉ ምንጭ ያለፈበት የመከራ መንገድ ነው። ድሎት ዱለት እንጂ ጉልበት እና ጽናትን አያጠግብም። መከራ የጠንካራ ሰው አሻራ ነው። ክርስቶስን ማንም ሰው የሚያስታዉሰዉ በመስቀሉ እንጂ አሳ አበርክቶ በመቆለሉ አይደለም። ከታምራቱ ይልቅ ስቅላቱ አይረሴ አድርጎታል። በምድር ላይ ጥልቅ ሃሳብ ይዘው እንደበጋ መብረቅ ምድርን ያናወጡ ፈላስፋወችማ ከክርስቶስ በፊት ስንት አዝማን ቀድመው ነበሩ። እነሶቅራጥስ እነቡድሃ... ሰዉን ሰዉ የሚአደርገው ቁመናው ሳይሆን ፈተናው ነው።" ተልሚድ ይስማዕከ ወርቁ @yenbabalem1 @yenbabalem1
893
5
ዳርክ ሳይኮሎጂ @yenbabalem1.pdf
931
6
No text...
879
7
No text...
0
8
No text...
0
9
#ህልም_ተስፋ_ለውጥ! 🧛ትልቅ ህልም ማየት ድፍረት ነው! ​በሕይወት ጉዟችን አሁን ካለንበት ጠባብ ማዕቀፍ እና ፈተናዎች አልፈን፣ ከፍ ወዳለ የስኬት ለውጥ ለመድረስ መነሻው ህልም ነው። ህልም የሌለ
#ህልም_ተስፋ_ለውጥ! 🧛ትልቅ ህልም ማየት ድፍረት ነው! ​በሕይወት ጉዟችን አሁን ካለንበት ጠባብ ማዕቀፍ እና ፈተናዎች አልፈን፣ ከፍ ወዳለ የስኬት ለውጥ ለመድረስ መነሻው ህልም ነው። ህልም የሌለው ሕይወት መድረሻ እንደሌለው መርከብ ነው። ​✨የህልም ኃይል ምን ይመስላል! ህልም የተስፋ እና የጉዞ መርከብ ነው። ዛሬ ባለው ችግር ሳንወሰን፣ ነገ በሚመጣው ብሩህ ጊዜ ላይ ትኩረት እንድንሰጥ ያደርገናል። ህልም የውስጥ ማቀጣጠያ ሃይል (Motivation) ነው። ጠዋት ከእንቅልፍ ስንነሳ በጉጉት ነቅተን ግልጽ ዓላማና ምክንያት ይፈጥርልናል። ህልም የትዕግስት እና ወጥነት መሰረት ነው። ታላላቅ ህልሞች በአንድ ቀን ባይሳኩም፤ ትዕግስት፣ ጽናት እና ከውድቀት መማርን አስተምረው ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ያደርሰናል። ህልም የእውነት መነሻ ነው። በዓለም ላይ ያሉ ትላልቅ ስኬቶች እና ፈጠራዎች ሁሉ መነሻቸው በአንድ ሰው አእምሮ ውስጥ በታየ ቀላል ህልም ነበር። ​💡 ማስታወሻ፦ በልባችን ውስጥ ትልቅ ህልም ካለ፡ እሱን እውን ለማድረግ ዛሬውኑ አነስተኛ እርምጃ መጀመር ያስፈልጋል። አቅጣጫን እንጂ ህልምን መቀየር ሽንፈት ነው! ከህልማችን ጋር ብቻችንን የቀረን ቢመስልም በህልማችን ተስፋ ስንቅ ብዙ ነን✍️ ከራስ ወደ ራስ! (መልካም ቀን) 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
1 830
10
#ኗሪ_አልባ_ጎጆዎች! አያቶች! በባዶ መስክ ተመራምረው፣ ጥበባቸውን፣ ዕድሜያቸውን ገብረው፣ የጎጆ ንድፍ ሲያበጁ፣ አረጁ፣ ዘመናቸውን ፈጁ፣ አባቶች! መላ ዘመናቸውን፣ ጎጆ በመቀለስ አሳለፉ፣ ሳይኖሩበ
#ኗሪ_አልባ_ጎጆዎች! አያቶች! በባዶ መስክ ተመራምረው፣ ጥበባቸውን፣ ዕድሜያቸውን ገብረው፣ የጎጆ ንድፍ ሲያበጁ፣ አረጁ፣ ዘመናቸውን ፈጁ፣ አባቶች! መላ ዘመናቸውን፣ ጎጆ በመቀለስ አሳለፉ፣ ሳይኖሩበት አለፉ፣ ልጆች! ጎጆውን ለመውረስ ሳይከጅሉ፣ እንዲህ አሉ፣ «ያባቶቻችን ጎጆ፣ ይኹን ባዶ ይኹን ምንም፣ በኛ ቁመት፣ በኛ መጠን፣ አልተቀለሰም!» "ኢትዮጵያ_እየተመከረች_ነው😐" ከራስ ወደ ራስ! (መልካም ቀን) 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
1 903
11
የዚህ ቻናል ቤተሰቦች boost በማድረግ የምትችሉትን ተባበሩ (premium yalachihu)🙏 https://t.me/boost/yenbabalem1
1 966
12
የፍልስፍና ሀሁ.@Yemesahft_Alem .pdf
1 966
13
📚ሁሌም ማንበብ! 📚📖 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
1 884
14
#ጅል_ካልተፈተነ_አያልፍም! ጅል የሚነቃው ሲዘንብ ነው፡፡ ያኔ ይበሰብሳል እንጂ መጠለያ አያገኝም፡፡ የሚወዱን ሰዎች በፍቅር እንደ ዣንጥላ ከበላያችን የሚዘረጉበት ዘመን አለ፤ ከብቸኝነት ዶፍ ከመልከስከስ ንዳድም ጠባቂዎቻችን የሚሆኑበት፡፡ ሁልጊዜ ግን እንደዚያ አይቀጥልም፣ አንድ ቀን ግፋችን ከብዷቸው ቸልተኝነታችን አድክሟቸው እንደ ዣንጥላ ይታጠፋሉ። ወይም አያያዛችንን ዓይቶ ጠንካራ ነፋስ ከእጃችን ይነጥቃቸዋል፡፡ ዶፍ ውስጥ ካለመጠለያ የመቆሚያ ዘመን አለ። ጅል ግን ይኼን ቀድሞ አይረዳም፡፡ ጅል ከጅልነቱ ይፈወስ ዘንድ፤ በመከራ መጠመቅ አለበት! በመከራ ያልተፈወሰ ጅል፤ ሞት ብቻ ነው የሚገላግለው። ከራስ ወደ ራስ! (መልካም ቀን) 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
2 000
15
እኛና አምላክ 😊 ለራሳችሁ አልቅሱ አይደለ ያልከን? 🤷‍♂️ ይሄው ለራሳችን እያለቀስን ነው። ፈቃዳችንን ሳትጠይቀን በራስህ ፈቃድ ስላመጣህን እያለቀስን ነው። በግጥሙ ድንገት ዱብ እንዳለው ኦማር ካያም ካመጣህን በኋላ ስለ አሁን፣ ስለ ዛሬ፣ ስለ ነገ ባለማወቃችን እያለቀስን ነው። ⏳ መኖር ቅጣት ሆኖብን እያለቀስን ነው። ለራሳችን ባዕድ በመሆናችን እያለቀስን ነው። ባጭሩ ከልደት እስከ ሞት የኛ ፈቃድ ስለሌለበት እያለቀስን ነው። የማናውቀውን ሕይወት እየኖርን የማናውቀውን ሞት እንሞታለን። ... እግዚአብሔርም በቃሉ እንዲህ ሲል መለሰ። እንደ እግዚአብሔር ያለ ክንድ አለህን? ወይስ እንደሱ ባለ ድምፅ ታንጎዳጉዳለህን? በውኑ ከተወለድክ ጀምሮ ማለዳን አዘሀልን? 🌞 ከሰማይ ሁሉ በታች ያለው ገንዘቤ ነው አለኝ። 🪙 ይሄው እንደምታዩት የእግዚአብሔር መልስ ጥያቄ ነው።🍭ስጠይቀው መልሶ እኔኑ ይጠይቀኛል። ሰውንና እግዚአብሔርን አንድ የሚያደርጋቸው ይሄው ነው። ጥያቄ ጥያቄ ጥያቄ። ከ ዮናስ ጎርፌ የተወሰደ /ስነ አመክንዮ/ 📖
1 876
16
በዜሮ ... (አሌክስ አብርሃም) አንድ ጓደኛየ መንጃ ፈቃድ አውጥቶ መኪና መንዳት በጀመረ በመጀመሪያው ቀን በሰላም በእግሬ ከምሄድበት ጠራኝና "ና ግባ አደባባዮን ላሻግርህ" አለኝ "ግዴለም በእግሬ እሻገራለሁ" አልኩ። ነዝንዞ  አስገባኝና ጋቢና አስቀመጠኝ። መንግስትና ህዝብ ንዳ ብሎ ፈቃድ ከሰጠው እኔ ማነኝ ችሎታውን የምጠራጠር ብየ ተመቻቸሁ። ገና በሩን ከመዝጋቴ  ስለመኪና ባህሪና ስለአነዳድ ቴክኒክ ልቤ እስኪደክም ያስረዳኝ ጀመር። ያለምንም ዓላማ ከተማችንን አንድ ጊዜ አዞረኝ። እስከዚህ ደህና ነበር።   "ይሄ ፍሬን ይባላል፣ ድንገተኛ ነገር ...ለምሳሌ ሰው ፣ አህያ ወይም  የተናኘ  ባል የሚነዳው መኪና ቢገቡብህ ማቆሚያ ነው"  አለና አጎንብሶ ፍሬኑንን ይፈልግ ጀመረ...(ተናኘ ሹፌር ያገባች የቀድሞ  ፍቅረኛው ናት፤ከነቂሙ ነው መንጃ ፈቃድ የያዘው?) "ፍሬኑን እስክትፈልግ ግን ....ከማለቴ  ፍሬኑን አግኝቶ ባለ በሌለ ሀይሉ ረገጠው። ወደፊት ተወርውሬ የሆነ ነገር ጋር ተጋጭቸ ተመለስኩ። ዘና ብሎ "አሁን የገጨኸው ዳሽ ቦርድ ይባላል የትም አገር የሚያጋጥም ነገር ነው" አለና ቀጠለ። ደረቴን ደግፌ  እያሳልኩ ዝም አልኩ። ብቻ እንዲህ አሰቃይቶኝ በመጨረሻ "አንዲት ብዙ ሹፌሮች ያልባነኑባት ቴክኒክ ላሳይህ ወደፊት ይጠቅምህ ይሆናል" አለኝ። ወይ እዳየ። ከዚህ ሁሉ ለዓመታት የነዳ ሹፌር ተደብቆ  ገና በአንድ ቀን ምን ተገልጦለት ይሆን እያልኩ ሳስብ በከተማችን አለ ወደሚባለው ቁልቁለት መንገድ ወሰደኝና "አሁን እዚህ ቁልቁለት ላይ ሞተሩን ታጠፋውና በዜሮ ትሄዳለህ ...መሪዋ ላይ ብቻ መጫወት ነው...ነዳጅ አተረፍክ ማለት ነው አባቴ" ብሎ ትልቅ ግኝት እንደነገረኝ አይነት በኩራት ሀሀሀሀሀ ብሎ ሳቀ። እኔ ግን ነፍሴ ተጨነቀች።  መኪናው ወደታች ፍጥነት እየጨመረ  መምዘግዘግ ጀመረ ። ወገኖቸ ባጭሩ ፍሬን ቢረግጥ ምን ቢረግጥ (እኔን ሁሉ እግሬን ቢረግጥ) መኪናው አልቆምም አለ። አታምኑኝም ዞር ስል የሹፌሩ በር ተከፍቶ አጅሬው ሲዘል ተገጣጠምን። ለደይቃወች ራሱን በሚነዳ መኪና ከተጓዝኩ በኋላ .... መኪናዋና እኔ ለግንባታ ፒራሚድ መስሎ  የተከመረ አሸዋና ጠጠር ክምር ጫፍ ላይ ጉብ አልን። እዚህ  ቴውድሮስ አደባባይ ያለውን የአፄ ቴውድሮስን የመድፍ ሀውልት ነበር የምንመስለው። አሁን ያለንበትን የኑሮ ሁኔታ ሳየው፣  የሆነ ቴክኒክ ላሳያችሁ ብሎ ያሳፈረን ሹፌር ዘሎ የወረደ እስኪመስለኝ ቀላል እየተምዘገዘግን ነው?! ብቻ ማረፊያችንን ያሳምረው። ለእኔ በነጠላው  የደረሰ አምላክ በጅምላ ይድረስልን። @yenbabalem1 @yenbabalem1
2 196
17
#አፍሪካ_ከበዳት! "አውሮፓ ውስጥ  መብራት ሲጠፋ 'ምንድነው የተበላሸው?' ብለው  ባለሙያ ይፈልጋሉ፤ አፍሪካ ውስጥ ግን መብራት ሲጠፋ መጀመሪያ የምናደርገው ነገር በመስኮት አንገታችንን አስወጥተን የጎረቤት መጥፋቱን ማረጋገጥ ነው። የእነሱም ከጠፋ በሰላም እንተኛለን፤ ምክንያቱም የጋራ መከራ ሰላም ይሰጠናል !" (ሮበርት ሙጋቤ) ✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️ የተማሩ ድሆች፣ መሃይም ሀብታሞች፣ ሰካራም ሃያሲ፣ ጉርስ ያጣ ደራሲ፣ ዘራፊ ነጋዴ ፣ ሰላም ጠል ወንበዴ፣ ዘረኛ ካድሬዎች ፣ ህልም አልባ መሪዎች፣ ሆድ አደር ሰባኪ፣ ውሸታም አምላኪ፣ ቆብ ቀዳጅ መነኩሴ፣ ተሳዳቢ ቄሴ፣ ትቢተኛ ሼህዎች፣ ግር ባይ አማኞች፣ አስመሳይ ተዋናይ፣ የዳኛ ቂል አባይ፣ እኝን ሁሉ ጉዶች ሀገር ተሸክማ፣ እንዴት ከፍ ትበል? እንዴት ሆና ትልማ? ከራስ ወደ ራስ! (መልካም ቀን) 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
1 978
18
#የተሰጠን_ምነኛ_መልካም_ነው! ጠቢቡ መነኩሴ ከዛፍ ስር ተቀምጦ ፀሎት እያደረሰ ባለበት ሰዓት ሽቅብ ወደ ዛፉ ቅርንጫፍ አማተረ። ቁራ ከቅርንጫፉ ላይ ሆኖ አምርሮ እያለቀሰ አየው። ''ቁራ ምን ገጠመህ ? ለምንድን ነው እንዲህ የምታለቅሰው?" አለው መነኩሴው። "ደስታን አጥቻለሁ፤ ህይወት በጣም አስጠልታኛለች፤ ያየኝ ሰው ሁሉ በድንጋይ ፡በቀስትና ወንጭፍ ወርውሮ ሊገድለኝ ይምክራል። ለአፍታ ከዛፎች ቅርንጫፍ ላይ ሳርፍ ሰው አየኝ አላየኝ ሰቀቀን ነው። ለምን እንዲህ እንደምጠላ አላውቅም፡፡ ደስታን አጥቻለሁ። ህይወት በጣም አስጠልቶኛል።" አለ ቁራ እንባ እየተናነቀው። "እኔ ጠቢብ ነኝ፤ የምትፈልገውን ልሰጥህ እችላለሁ። ምን እዳደርግልህ ትሻለህ?" አለ ሞነኩሴው። ''ከፊትህ ሞገስ ካገኘሁ እባክህን #ዳክዬ አድርገኝ።" "እንደ ፍቃድህ ዳክዬ አደርግሃለሁ። ነገር ግን ከዚያ በፊት ዳክዬን ፈልግና በህይወቱ ደስተኛ መሆኑን ጠይቅ?" አለው። ቁራው ዳክዬ ፍለጋ በረረ... ከብዙ ድካም በኋላ ዳክዬዋ ከሀይቅ ውስጥ እየዋኘች አገኘና "በጣም ታምርያለሽ፤ የላባሽ ላዛነትና ንጣት ግሩም ነው። በዚያ ላይ ሰዋች ይወዱሻል ከአዋዋፍት መካከል እንዳንቺ ደስተኛ የለም" አለ ቁራ። "ኧረ ተወኝ ወዳጄ ምኑን አማርኩኝ ካልጠፋ ቀለም ድፍን ነጭ አርጎኝ፤ በዚያ ላይ ክንፍ እያለኝ መብረር ነፍጎኝ፤ ከአሁን አሁን አዞ በላኝ ብዬ በፍርሃት ሰውነቴ እያለቀ ስለምን ደስተኝነት ነው ምትደሰኩርብኝ? ደስተኛ አዕዋፋት ፈልገህ ከሆነ ሂድ ወደ #ፒኮኮች በቀለማት ወዳጌጡት። በጎብኚ ታጅቦ በዙ(zoo) እና ፓርክ ተጠብቀው ከሚኖሩ ፒኮኮች ጋ ሂድ " አለችው። ቁራ ወደ ፒኮክ በረረ። ፒኮክ በመቶዎች በሚቆጠሩ ጎብኚ ተከብቦ ነበር ቁራው የደረሰው። ቀስ በቀስ ጎብኚዎች ሂደው ሲያልቁ ቁራ ወደ ፒኮክ ጠጋ በማለት፦ "ፒኮክ በቀለማት ያሸበረቅሽ ቆንጆ፣ በሰዎች የተወደድሽ እድለኛ ፍጥረት ነሽ መቼም ከአዋዋፍት መካከል እንዳንቺ ደስተኛ የለም..!' አላት፡፡ "በሰው መወደዴ ምን ፈየደልኝ? ዘመኔን በሙሉ በዙ(zoo) ውስጥ ተቆልፎብኝ እስረኛ እንድሆን አረገኝ እንጂ፣ ላባየን ለቁስ ማስጌጫ የሚፈልጉ ሰዋች፣ ድፍት አርገው ሊነጫጩኝ እንደሚሹ ብታውቅ እድለኛ ባላልከኝ ነበር... እድለኝነቱ ቀርቶ ለአንድ ቀን #እንዳንተ በነፃነት ከአድማስ እስከአድማስ በርሬ ብሞት..!" ቁራ በሰማው ነገር እየተደመመ ወደ ሰማይ ከፍ ብሎ በረረ። ደስተኛ ለመሆን ከፈለግን ትኩረታችንን ባለን ነገር ላይ እናድርግ ፤ ከአላስፈላጊ ንፅፅር ወጠን አቅማችንን ፈልገን ከውስጣችን ቤት እንስራ! ከራሳችን ጋር ውድድር ማድረጉ ይበጃል እና የማይጠቅመንን ንፅፅር እናስወግድ ! 😞➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️➡️😞 ከራስ ወደ ራስ! (መልካም ሰንበት) 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
2 008
19
#ጾም_አትጠብቁ! ሁሌም በ'ለት በ'ለት ፣ ሰው እያቆሰለ የበደ'ላችን ስለት ። ላየበጀን ላይጠቅመን ፣ ቂምን እንደ ጥሪት በብዙ ከምረን ፣ መቼ እንደሚያበቃ ቀናችንን ሳናውቅ፣ ይቅርታ ለማለት...!ፆ
#ጾም_አትጠብቁ! ሁሌም በ'ለት በ'ለት ፣ ሰው እያቆሰለ የበደ'ላችን ስለት ። ላየበጀን ላይጠቅመን ፣ ቂምን እንደ ጥሪት በብዙ ከምረን ፣ መቼ እንደሚያበቃ ቀናችንን ሳናውቅ፣ ይቅርታ ለማለት...!ፆምን የምንጠብቅ!? ለምን??? መጠበቅ ነዉ እንጂ ንፁህ ሁነን ብቁ፣ ይቅርታ ለማለት ፆም አትጠብቁ! በንባብ ዓለም ስም እንኳን ለፍልሰታ ፆም በሰላም አደረሳችሁ እንላለን🤝 💘💘💘💘🤎🤎💘💘💘💘 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
1 828
20
👉አንዲት ዝንብ ዝናብ ዘንቦባት በረዳትና በአንድ ትልቅ በሬ ቀንድ ላይ አርፋ ፀሐይ እየሞቀች ረዥም ሰዓት ቆየች። ብርዱ ከለቀቃት በኋላ ወደ በሬው ጆሮ ጠጋ አለችና፡ "አዝናለሁ በሬ ሆይ... እንግ
👉አንዲት ዝንብ ዝናብ ዘንቦባት በረዳትና በአንድ ትልቅ በሬ ቀንድ ላይ አርፋ ፀሐይ እየሞቀች ረዥም ሰዓት ቆየች። ብርዱ ከለቀቃት በኋላ  ወደ በሬው ጆሮ ጠጋ አለችና፡ "አዝናለሁ በሬ ሆይ... እንግዲህ መሄዴ ነው" አለችው። ... በሬውም ዘወር ብሎ፡ "ስታርፊ አልተሰማኝም፤ ስትነሺም የሚሰማኝ አይመስለኝም!" ብሎ መለሰ። ... በሕይወታችን ውስጥ አንዳንዶች መኖራቸው የማይጠቅም፣ መሄዳቸው የማይጎዳ ሆነው ሳለ... ራሳቸውን እንደ ትልቅ ነገር የሚቆጥሩ (Main character syndrome) ያለባቸው አሉ። ... ክብደታችሁን የማያውቁ ሰዎች "እሄዳለሁ" ቢሉ እንደማስፈራሪያ አትቁጠሩት። መኖራቸው ላልተሰማችሁ መሄዳቸው ምን ጉዳት!!? 🤎🤎🤎🤎🤎🤎🤎🤎🤎🤎🤎 📚 📚 ሁሌም ማንበብ! 📚📚 Share and like @yenbabalem1 @yenbabalem1
2 413