en
Feedback
ዜና ቅዱሳን

ዜና ቅዱሳን

Open in Telegram

በዜና ቅዱሳን መርሐ ግብር ላይ ያላችሁን ሀሳብ አስተያየትና ጥቆማ @abrishte ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ

Show more
842
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
October '24
October '24
+26
in 0 channels
September '24
+10
in 0 channels
Get PRO
August '240
in 0 channels
Get PRO
July '240
in 0 channels
Get PRO
June '240
in 0 channels
Get PRO
May '240
in 0 channels
Get PRO
April '240
in 0 channels
Get PRO
March '24
+7
in 0 channels
Get PRO
February '24
+3
in 1 channels
Get PRO
January '24
+4
in 0 channels
Get PRO
December '23
+7
in 0 channels
Get PRO
November '23
+13
in 0 channels
Get PRO
October '23
+4
in 0 channels
Get PRO
September '23
+7
in 0 channels
Get PRO
August '23
+24
in 0 channels
Get PRO
July '23
+21
in 0 channels
Get PRO
June '23
+14
in 0 channels
Get PRO
May '23
+10
in 0 channels
Get PRO
April '23
+10
in 0 channels
Get PRO
March '23
+11
in 0 channels
Get PRO
February '23
+25
in 0 channels
Get PRO
January '23
+38
in 0 channels
Get PRO
December '22
+45
in 0 channels
Get PRO
November '22
+28
in 0 channels
Get PRO
October '22
+31
in 0 channels
Get PRO
September '22
+23
in 0 channels
Get PRO
August '22
+9
in 0 channels
Get PRO
July '22
+33
in 0 channels
Get PRO
June '22
+24
in 0 channels
Get PRO
May '22
+96
in 0 channels
Get PRO
April '22
+26
in 0 channels
Get PRO
March '22
+90
in 0 channels
Get PRO
February '22
+44
in 0 channels
Get PRO
January '22
+55
in 0 channels
Get PRO
December '21
+28
in 0 channels
Get PRO
November '21
+50
in 0 channels
Get PRO
October '21
+42
in 0 channels
Get PRO
September '21
+124
in 0 channels
Get PRO
August '21
+70
in 0 channels
Get PRO
July '21
+128
in 0 channels
Get PRO
June '21
+87
in 0 channels
Get PRO
May '21
+330
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
15 October0
14 October+2
13 October+3
12 October0
11 October+2
10 October+5
09 October0
08 October+2
07 October+1
06 October+4
05 October0
04 October0
03 October+2
02 October+4
01 October+1
Channel Posts
🕤🕤የየካቲት ፳፬ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ቅዱስ አጋቢጦስ ኤጲስቆጶስ 🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿# እንኳን ለከበረ አባት ለንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ወታደር አለቃ ለነበረው ብዙ ተአምራትን ላደረገ፤ ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ለገደለው ለኤጲስቆጶስ ቅዱስ አጋቢጦስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ በጋዛ ሰማዕት ከሆኑ ከጢሞቴዎስ፣ ከቆጵሮስ ከአገረ ከሚናስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።🌿🌿# ❇️#ይህም አባት በከሀድያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ነበር። ወላጆቹም ደጎች ምእመናን ነበሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረውት ዲቁና ተሾመ። ከዚያም በኋላ እናትና አባቱን ትቶ ወደ አንድ ገዳም ሔደ የሸመገሉ መነኰሳትን አገለገለ። ከእርሳቸውም በጎ አምልኮትን አገለገለ። ከእርሳቸው በጎ አምልኮትን ተማረ አረጋውያኑንም እያገለገለ በገድል ተጠመደ ያለ ማቋረጥም በጾም በጸሎትና በስግደት ይተጋል ከጥዋትም እስከ ምሽት በመጾም የሽንብራ አሠር የሚመገብ ሆነ። ከእንቅልፍም ጋር ሊታገል በወደደ ጊዜ ከሽምብራ አሠር ጋር አመድ እየተመገበ ሰማንያ ቀን ኖረ ከዚህም ተጋድሎ ውስጥ እያለ ኃይሉ ግን ይጨመርለት ነበር። ለአረጋውያንም አገልግሎቱን አላስታጐለም ሲጠራቸው ጌቶቼ ይላቸዋል የጽድቅንና የትሩፋትን ሥራ ሁሉ ፈጸመ። ❇️#እግዚአብሔርም የሚያስደንቁ ብዙዎች የሆኑ ታላላቅ ተአምራቶችን በእጆቹ ገለጠ። ከእርሳቸውም አንዲቷን ብላቴና አዳናት እርሷም እንደ ዕንጨት የደረቀች እስከምትሆን ብዙ ዘመን ጭንቅ በሆነ ደዌ ታማ የኖረች ናት። ዳግመኛም ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ገደለው። ከሰውና ከእንስሳም፡አስጨናቂ የሆኑ በሽታዎችን አስወገደ። የተጋድሎውና፡የኃይሉ ጽናት ወሬው በተሰማ ጊዜ ስሙ ሉክያኖስ፡የሚባል መኰንን ወደርሱ ልኮ አስመጥቶ ያለ ውዴታው በግድ የጭፍራ አለቃ አድርጎ ሾመው እርሱ ግን ተጋድሎውን አልተወም ጾምንም ጸሎትንም የትሩፋትን ሥራ የሚጨምር ሆነ እንጂ የቀደመ ሥራውን አልተወም በጥቂት ቀኖችም ዲዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስን እግዚአብሔር አጠፋቸው አምላክን የሚወድ ጻድቅ ሰው ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ነገሠ ይህም ቅዱስ ከጭፍራ ውስጥ ይወጣ ዘንድ ምክንያት የሚሻ ሆነ። ❇️#ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እጅግ የሚወደው መልከ መልካም የሆነ ወጣት ብላቴና ነበር ክፉ ጋጌንም ተጫነበት በቀንም በሌሊትም ታላቅ ሥቃይን የሚያሠቃየው ሆነ ቅዱስ አጋቢጦስንም ከሚያውቁት ውስጥ አንድ ሰው በአየው ጊዜ "የወታደር አለቃ አጋቢጦስ ቢመጣ በአዳነህ ነበር" አለው የታመመውም "እርሱ በንጉሥ ጭፍራ ሥርዓት ውስጥ ያለ፡፡ በውኑ ይህን ሥራ መሥራት ይችላልን" አለ ሰውዬውም ገድሉንና ሥራውን ሁሉ አስረዳው። ጋጌን ያደረበትም "በእውነት ሊያድነኝ ዘንድ የወታደር አለቃ አጋቢጦስን ፈጥናችሁ አምጡልኝ" አለ። ንጉሥም ይህን በአወቀ ጊዜ ቅዱስ አጋቢጦስን እንዲአመጡት አዘዘ በመጣ ጊዜም በወጣቱ ላይ ጸለየ በከበረ መስቀልም አማተበው በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ኃይል ዳነ ንጉሡም በዚህ ደስ ብሎት ቅዱስ አጋቢጦስን አከበረው "ምን እንዳደርግልህ ትሻለህ?" አለው እርሱም ንጉሡን "ከወታደርነት ውስጥ አሰናብተኝ" አለውና አሰናበተው አስቀድሞ ወደ ነበረባትም ቦታው ተመለሰ ብዙ ዘመናትም እጅግ እየተጋደለ ኖረ። ❇️#ከዚህም በኋላ የዚያች አገር ኤጲስቆጶስ ይዞ ቅስና ሾመው ይህም ኤጲስቆጶስ በሞተ ጊዜ ቅዱስ አጋቢጦስን ይሾምላቸው ዘንድ ሕዝቡ ሊቀ ጳጳሳቱን ለመኑት እርሱም ሾመላቸው መልካም ተናጋሪዎች የሆኑትን የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው። እግዚአብሔርም የትንቢትን ጸጋ የተሠወረውንም የማወቅ ድንቆች ተአምራቶችንም የማድረግ ሀብትን ሰጠው። በሥውር ኃጢአትን ሆነ የሚሠሩትን ኃጢአተኞች የሚገሥጻቸው ሆነ በንስሐም እስኪመለሱ ከመቅደስ ያርቃቸዋል። ❇️#ዳግመኛም በገድሉ መጽሐፍ ተጽፎ የተገኘ የታላቅ ወንዝ ወራጅ ውኃን በመስቀሉ አቁሞ ወደ ሌላ መንገድ መለሰው የዕውር ዐይኖችንም ገለጠ ለምጻሞችንም አነጻ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳነ። ያማረና መልካም የሆነ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን ፈጽሞ በዚህች ዕለት የካቲት24 ዐረፈ፡፡ 🙏🙏# ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አጋቢጦስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።🙏🙏 #ምንጭ፦ የየካቲት24 ስንክሳር። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣

2
+2
No text...
130
3
No text...
1
4
https://youtu.be/PhR9XTDf2Co?si=WiSLxh-uwQKi6IfB
182
5
🕤🕤የየካቲት ፲፯ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#አባ ሚናስ መነኰስ ወሰማዕት🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን ከላይኛው ግብጽ ከአክሚም መንደር ለሆነ ስለ እግዚአብሔር አብ አባትነት ስለ ወልድ ልጅነት መስክሮ በእስላሞች መኰንን እጅ ሰማዕትነት ለተቀበለ ለታላቁ ጻድቅ ወሰማዕት ለመነኰስ አባ ሚናስ ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን።🌿🌿# ❇️#የዚህም ቅዱስ፡ ወላጆቹ ምድርን የሚያርሱ ክርስቲያን ገበሬዎች ናቸው። እርሱም ይህን ዓለም ንቆ ትቶ በአገረ አክሚም በሚገኝ በአንድ ገዳም መነኰሰ ለመብልና ለመጠጥ ሳይገዛ በየሁለት ቀን እየጾመ ብዙ ቀኖችን ኖረ ከዚያም ወጥቶ ወደ እስሙናይን አገር ሒዶ በአንድ ገዳም ውስጥ እያገለገለና እየተጋደለ ከገዳሙ ደጃፍ ሳይወጣ ዐሥራ ሰባት ዓመት ኖረ። ❇️#እስላሞችም በግብጽ አገር በነገሡ ጊዜ ለእግዚአብሔር ከርሱ ጋር ለዘላለሙ ህልው የሆነ የባሕርዩ የተወለደ ልጅ የሚሠርፅ መንፈስ ቅዱስም የለውም እንደሚሉ ሰማ ስለዚህም ነገር እጅግ አዘነ። ከአበ ምኔቱም ቡራኬ ተቀበለ ወደ እስሙናይን ከተማ ወጥቶ ሔደ የእስላሞች ሠራዊት አለቃ በሆነ በመኰንኑ ፊት ቁሞ እንዲህ አለው "እናንተ ለእግዚአብሔር ከባሕርዩ የተወለደ ልጅ እንደ ሌለው አድርጋችሁ የምትናገሩ እውነት ነውን?" መኰንኑም "አዎን ልጅ አለው ማለትን ከእግዚአብሔር እናርቃለን" አለ። አባ ሚናስም "ያለ ልጅ ልታምኑ አይገባም እርሱም ያለ ዘር ያለ ሩካቤ የሆነ ነው ከባሕርዩ ተወለደ እንጂ" አለው። መኰንኑም "ልጅ አለው ማለት በሕጋችን ክህደት ነው" አለ። አባ፡ሚናስም እንዲህ አለው "መኰንን ሆይ እወቅ የከበረ ወንጌል በወልድ ያመነ የዘላለም ሕይወት አለው በእግዚአብሔር ልጅ በወልድ ያላመነ ሕይወትን አያይም የእግዚአብሔር ቊጣ በላዩ ይወርዳል እንጂ ብሏልና"። ስለዚህም መኰንኑ እጅግ ተቆጣ ራሱንም በሰይፍ እንዲቆርጡ ሥጋውንም በየቊርጥራጭ ቆራርጠው ከባሕር እንዲጥሉት አዘዘ ምእመናንም ሥጋውን ወስደው በበጎ አገናነዝ ገንዘው ቀበሩት መታሰቢያውንም አደረጉ። 🙏🙏#ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።🙏🙏 #ምንጭ፦ የየካቲት17 ስንክሳር። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
143
6
No text...
97
7
🕤🕤የየካቲት ፲፯ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ሊቀ-ነቢያት ቅዱስ ሙሴ🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን የእግዚአብሔር ሰው ለሆነ ለየዋህ ለትሑቱ ለቢያት አለቃ ለቅዱስ ሙሴ ለዕረፍቱ መታሰቢያ ለበዓል፣ በሰላም አደረሰን።🌿🌿# ❇️#ይህ ነቢይ ነፍሱን ስለእርሳቸው አሳልፎ እስከ መስጠት ደርሶ ከእግዚአብሔር ወገኖች ጋር የደከመ ነው እርሱም በግብጽ አገር በኤርትራ ባሕርም ድንቆች ተአምራትን ያደረገ ነው። ይህም ስለ ፈርዖን ትእዛዝ ወላጆቹ በግብጽ ወንዝ ውስጥ በጣሉት ጊዜ አውጥታ ላሳደገችው ለፈርዖን ልጅ ለተርሙት ልጅዋ መባልን አልወደደም። እርሱ ፈርዖን የዕብራውያንን ወንዶች ልጆች ይገድሏቸው ዘንድ አዝዞ ነበርና። በአገኘችውም ጊዜ ለርሷ ልጅ ሊሆናት ወስዳ በመልካም አስተዳደግ አሳደገችው። ❇️#አርባ ዓመትም በሆነው ጊዜ አንዱን ዕብራዊ የግብጽ ሰው የሆነ ሲያጠቃው አየ ለዕብራዊው ተበቅሎ ግብጻዊውን ገደለው። በማግሥቱ ሁለት ዕብራውያን እርስ በርሳቸው ሲጣሉ አያቸው ሊያስታርቃቸውና በመካከላቸው ሰላምን ሊአደርግ ወደደ። አንዱ ዐመፀኛም "ትላንት ግብጻዊውን እንደገደልከው ልትገድለኝ ትሻለህን" አለው። ስለዚህም ነገር ሙሴ ፈርቶ ወደ ምድያም አገር ሸሸ በዚያም ሚስት አግብተሸ ሁለት ልጆችን ወለደ በዚያም አርባ ዓመት ኖረ በጳጦስ ቊጥቋጦ ውስጥ እግዚአብሔር ተናገው። ወደ ግብጽ አገርም ሒዶ የእስራኤልን ልጆች ከዚያ እንዲያወጣቸው አዘዘው። ❇️#ከዚህም በኋላ ሕዝቡን ከግብጽ አገር አወጣቸው የኤርትራንም ባሕር ከፍሎ በውስጡ አሳለፋቸው የባሕሩንም ውኃ በጠላቶቻቸው በፈርንና በሠራዊቱ ላይ ገልብጦ አሠጠማቸው። ከዚህም በኋላ በምድረ በዳ ውስጥ አርባ ዓመት ሙሉ መና አወረደላቸው ውኃንም ከአለት አፈለቀላቸው ይህን ሁሉ በጎ ሥራ በዚህ በደግ ነቢይ ሙሴ እጅ እግዚአብሔር አደረገላቸው እነርሱ ግን ይዘልፉት ነበር ብዙ ጊዜም በድንጊያ ሊወግሩት ሽተው ነበር። እርሱ ግን በእነርሱ ላይ ልቡን አስፍቶ በመታገሥ ስርሳቸው ወደ እግዚአብሔር ይማልዳል። እነርሱንም አብዝቶ ከመውደዱ የተነሣ እግዚአብሔርን "አቤቱ የዚህን ሕዝብ በደሉን ይቅር ካላክ ከሕይወት መጽሐፍህ ሰርሰዘኝ" አለው። ❇️#ሰው ከወዳጁ ጋር እንደሚነጋገር አምስት መቶ ሰብዓ ቃላትን ከእግዚአብሔር ጋር እንደተነጋገረ መጽሐፍ ምስክር ሆነ። የእስራኤል ልጆችም በሚያዩት ጊዜ እንዳይሞቱ ፊቱን እስከ መሸፈን ድረስ በእግዚአብሔር በጌትነቱ ብርሃን ፊቱ በራ። ❇️#መቶ ሃያ ዓመት የሆነ ዕድሜውም በተፈጸመለት ጊዜ ለአገልጋዩ ለነዌ ልጅ ለኢያሱ ሕዝቡን እርሱ እንዲጠብቃቸው በእጁ ውስጥ እንዲአስረክበው እግዚአብሔር ሙሴን ለኢያሱ አስረክብ ብሎ አዘዘው። ሙሴም ኢያሱን ጠርቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ አዘዘው ሕጉንም እንዲጠብቅ ሕዝብንም ለኢያሱ በእጁ አስረከባቸው ወደ ምድረ ርስት እርሱ እንደ ሚአስገባቸው አረጋገጠላቸው። ❇️#ሙሴም እግዚአብሔር እንዳዘዘው በምስክር ድንኳን ውስጥ የሚሠራውን ሁሉ ሠርቶ ከአዘጋጀ በኋላ በናባው ተራራ ውስጥ ዐረፈ በዚያም በመላእክት እጅ በሥውር ተቀበረ። የእስራኤል ልጆች ወስደው እንዳያመልኩት እግዚአብሔር የሙሴን ሥጋ ሠወረ። በእስራኤል ልጆች ውስጥ እንደ ሙሴ ያለ ደግ የዋህ ቅን የሆነ ነቢይ እንደማይነሣ መጽሐፍ ምስክር ሆነ። ❇️#ሰይጣንም የሙሴን ሥጋ ለእስራኤል ሊገልጠው በወደደ ጊዜ ሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ በጻፈው መጽሐፍ እንደመሰከረ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ገሠጸው ከዚህም ሥራ ከለከለው። የእስራኤል ልጆች አርባ ቀን አለቀሱለት። 🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሊቀ ነቢያት በቅዱስ ሙሴ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።🙏🙏 #ምንጭ፦ የመስከረም 8 ስንክሳር። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
102
8
+2
No text...
101
9
🕝🕝የካቲት 16🕝🕝 🍀ጻድቁ ንጉሥ ገብረ ማርያም/ሐርበይ/🍀 🌿🌿እንኳን ለኢትዮጵያዊው ለጻድቁ ንጉሥ ለላሊበላ ታላቅ ወንድም ለሆነው ለቅዱስ ገብረ ማርያም ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣በሰላም አደረሳችሁ🌿🌿 📚📚የላስታ ገሥታት የዘር ሐረጋቸው ከንጉሥ ሰሎሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ገደማ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ "የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት "ወይም" የላስታ መንግሥት" በመባል ይታወቃል፡፡ ከላስታ(ከዛጉዌ)ነገሥታት መካከል ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቅዱስ ገብረ ማርያም፣ ቅዱስ ላሊበላና ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ እነዚህ አራቱ ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ(ዘፍ14፥18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሰውንም በቅድስናና፡ በንጽሕና አገልግለው አልፈዋል፡፡ 📚📚ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ገብረማርያም በሌላኛው ስማቸው ሐርቤይ እየተባሉ የሚጠሩ ሲሆን የቅዱስ ላሊበላ ታላቅ ወንድም ናቸው፡፡ ታላቁን ጻድቅ ንጉሥ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብን ወልደዋል፡፡ አባታቸው ዣን ስዩም 40ዓመት ከነገሡ በኋላ በ76ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ልጃቸው ገብረ ማርያም ንግሥናውን ተቀብለዋል፡፡ ከእርሳቸው ቀጥሎ ታናሽ ወንድማቸው ቅዱስ ላሊበላ ተወልዶ እንደሚነግስ በትንቢት ተነግሮ፡ ነበር፡፡ ይህን ጊዜ ከላሊበላ ጋር በአባት እንጂ በእናት ይለያዩ ነበርና የበጎ ነገር ጠላት የሆነ ክፉ ሰይጣን የእኅታቸው ክፉ ምክር ተጠቅሞ በወንድማቸው በላሊበላ ላይ በቅናት ክፉ እንዲያስቡ አድርጓቸዋል፡፡ስለ ንግሥናቸው ሲሉ ምንም እንኳን በወንድማቸው ላይ ክፉ አስበው የነበረና በእኅታቸውም ክፉ ምክር መርዝ የሰጡት ቢሆንም በኋላ በክፉ ሀሳባቸው እጅግ ተፀፅተው "አምላኬንም ወንድሜንም አሳዘንኩ" በማለት ወንድማቸውን ይቅርታ በመጠየቅ ላሊበላን አንግሠውት እርሳቸው መንኵሰው ገዳም ገብተዋል፡፡ 📚📚ቅዱስ ላሊበላ ካለበት አክሱም ድረስ ሄደው በዕንባና በልቅሶ ይቅርታ ጠይቀው ወደ አገራቸው ሮሐ ከተማ ይዘውት በመምጣት መንግሥታቸውን አስረክበውት ነው የመነኑት፡፡ በምንኵስናም ሆነው በታላቅ ተጋድሎ በጾም በጸሎት በመትጋት እግዚአብሔርን እያገለገሉ እያለ ጌታችን ተገልጦላቸው "ክብሩ እንደ መላእክት የሆነ ታላቅ ልጅ ትወልዳለህና ወደቤትህ ተመለስ" ብሎ ከነገራቸው በኋላ ወደቤታቸው ተመልሰው ቅዱስ ነአኵቶ ለአብን ወልደዋል፡፡ 📚📚ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያም በዘመናቸው ከነበሩት ከእስክንድሪያ ሊቀ ጳጳሳት ከአባ ዳንኤል ጋር መልእክት በመላላክ "ከሀገሬ ሊቃውንት መነኰሳት የሕዝቡን ቋንቋ የሚሰሙና የሚያስተምሩ ጳጳስ ይሹሙልን" በማለት ለእስክንድሪያ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ 📚📚ምንም እንኳን የእስክንድሪያ ሲኖዶስ በወቅቱ ኢትዮጵያ የራሷንልጆች እንድትሾም ስላልፈለጉና በወቅቱ ፈቃደ እግዚአብሔርም ስላልነበረ የቅዱስ ገብረ ማርያምን ጥያቄ ንግሥት ዘውዲቱና ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ድጋሚ በመጠየቅ ፍጻሜውን እንዲያገኝ ቢያደርጉትም መሠረቱን ግን የጣሉት ዐፄ ገብረ ማርያም ናቸው 📚📚በዘመናቸው ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም ያሠሩ ሲሆን ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታችን ተገልጦላቸው "የእኔን መከራ እያሰብክ ከዓይንህ ዕንባ ሳያቋርጥ በጾም በጸሎት ተወስነህ ስላገለገልኸኝ በአንተ ስም ለተራበ ያበላውን፣ ለተጠማ ያጠጣውን፣ ለታረዘ ያለበሰውን ምሬልሃለሁ" በማለት ትልቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸው በካቲት16 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ጻድቁን፡ንጉሥ ዐፄ ገብረ ማርያምን ሚያዝያ10 ቀን የሚነበበው ስንክሳር በሰፊው ይጠቅሳቸዋል፡፡ 🙏🙏ከጻድቁ ከአቡነ ገብረ ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን! ። 🙏🙏 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧 💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧 .......... የቴሌግራም ቻናላችንን በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣የዜና ቅዱሳን ቤተሰብ ይሁኑ!!!
102
10
No text...
73
11
🕒🕒የካቲት 16🕒🕒 🍀🍀እግዝእትነ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት🍀🍀 🌼🌼እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የኪዳን በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🌼 📚📚7ቱ ኪዳናት 📚📚 🌿🌿ተካየደ' ማለት 'ተስማማ: ተማማለ' እንደ ማለት ሲሆን 'ኪዳን' በቁሙ 'ውል: ስምምነት' እንደ ማለት ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው:: 🌿🌿እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ ሆኑ ታስተምራለች:: ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7 ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን:: 🌿🌿"ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ" "ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3) 1. 🔑🔑 ኪዳነ አዳም 🔑🔑 👉👉አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው:: እግዚአብሔር ከአዳም ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው:: ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ:: (ዘፍ. 3:1) 👉👉አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4) 2. 🔑🔑ኪዳነ ኖኅ🔑🔑 👉👉ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ ከወጣ በሁዋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ" እንዲል:: (ዘፍ. 9:12) 3. 🔑🔑ኪዳነ መልከ ጼዴቅ 🔑🔑 👉👉መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ15 ዓመቱ መንኖ: አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት ነበር:: 👉👉እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን አልቀመሰም:: ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1) 4. 🔑🔑ኪዳነ አብርሃም🔑🔑 👉👉ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና እግዚአብሔር "በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: (ዘፍ. 12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን ሰጠው:: (ዘፍ. 17:1-14) 5. 🔑🔑ኪዳነ ሙሴ🔑🔑 👉👉ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ: የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው:: በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40 ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1, 31:18) 6. 🔑🔑ኪዳነ ዳዊት🔑🔑 👉👉ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ. 131:11) ሲል ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ "አልዋሰሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን:: (መዝ. 88:35) 7. 🔑🔑ኪዳነ ምሕረት🔑🔑 👉👉በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ ነበር:: ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን አደረ:: 👉👉በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ: ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው:: 👉👉የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ: ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ: መሰቀሉ: መሞቱና መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ ኪዳነ ምሕረት ይባላል:: ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት:: 👉👉የእርሷ ኪዳን 6ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል ማርያም ኪዳኗ ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው:: 👉👉እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ! በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ ኃጥአን ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር እንኖራለን:: 👉👉ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ: ኃጢአተነ: ወጌጋየነ: ማርያም እሙ ለእግዚእነ: በኪዳንኪ: ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ::" 👉👉ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል::" 👉👉የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት: ስብሕት: ክብርት: ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም የድኅነታችን መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ አማላጅ ናት:: 👉👉በዚህች ዕለት የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ አምላክ የሆነ ልጁዋ ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል:: በስምሽ ያመነ በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳት አያይም ብሏታል:: 🙏🙏🙏ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን:: በዓሉንም የሰላም: የፍቅርና የበረከት ያድርግልን::🙏🙏🙏 :- መ/ር ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧 💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧 .......... የቴሌግራም ቻናላችንን በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣የዜና ቅዱሳን ቤተሰብ ይሁኑ!!!
70
12
+7
No text...
70
13
🕒🕒የካቲት 16🕒🕒 🍀🍀እናታችን ቅድስት ኤልሳቤጥ🍀🍀 🌼🌼🌼እንኩዋን ለእናታችን ቅድስት ኤልሳቤጥ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🌼🌼🌼 📚📚ቅድስት ኤልሳቤጥ📚📚 👉👉በወንጌላዊው አንደበት የተመሰገነች እናታችን ቅድስት ኤልሳቤጥ ትውልዷ ከነገደ ሌዊ ነው:: ሐረገ ሙላዷም ከቅዱስ አሮን ካህን ወገን ይመዘዛል:: ከአሮን በቴክታና በጥሪቃ ወርዶ ሔርሜላ ላይ ይደርሳል:: 👉👉ይህቺ ሔርሜላ የምትባል ደግ ሴት ማጣት ("ጣ" ጠብቆ ይነበብ) የሚባል የተባረከ ሰው አግብታ 3 ቡሩካት ልጆችን ወለደች:: የመጀመሪያዋን 'ማርያም' አሏት:: እርሷ ቅድስት ሰሎሜን ወለደች:: ሁለተኛዋን 'ሶፍያ' አሏት:: እርሷ ደግሞ ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች:: 👉👉ሦስተኛዋ ግን የተለየች ናት:: 'ሐና' ብለው ሰየሟት:: እርሷም የሰማይና የምድር ንግሥት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ወለደች:: በዚህም መሠረት ድንግል ማርያም: ቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሰሎሜ የእህትማማች ልጆች ናቸው:: 👉👉ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ጊዜ ስም አጠራሩ የከበረ: ደግ ካህን ለሆነ: ለቅዱስ ዘካርያስ አጋቧት:: እርሷ የሊቀ ካህናቱ ሚስት ናትና ክብሯ ከፍ ያለ ነበር:: ምንም ልጅ ባይኖራትም ዘወትር በጸሎትና በጾም: ምጽዋትንም በማዘውተር: ነዳያንንም በማሰብ የምትኖር እናትም ነበረች:: 👉👉ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል::"ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: (ሉቃ. 1:6) 👉👉የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ (አድናቆት) ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር:: 👉👉ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው:: ቅድስቲቷ መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: 👉👉ድንግል እመቤታችን ወደ እርሷ መጥታ 'ሰላም' ባለቻት ጊዜ ምንም ያሳደገቻት ልጇ ማለት ብትሆን: መንፈስ ቅዱስ ስለ ሞላባት እመ ብርሃንን አመስግናታለች:: ቡርክት: ብጽእት: ከፍጥረተ ዓለሙ የከበረች መሆኗንም መስክራለች:: 👉👉በማሕጸኗ ያለ የ6 ወር ጽንስም የእመ አምላክን ድምጽ ቢሰማ በደስታ ዘሏል:: ለፈጣሪውም ስግደተ-ስባሔ አቅርቧል:: ቅድስት ኤልሳቤጥ አክላም "ወምንትኑ አነ ከመ ትምጽኢ ኀቤየ እሙ ለእግዚእየ-የጌታየ እናቱ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይገባኛል?" ስትል በትኅትና ተናግራለች:: ከጌታ እናት ጋር ለ3 ወራት በአንድ ቤት ቆይታለች:: 👉👉ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ:: 👉👉እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት:: ኤልሳቤጥ ማለት 'እግዚአብሔር መሐላየ ነው': አንድም 'የጌታ አገልጋይ' ማለት ነው:: 👉👉ሊቃውንትም:- +"+ ሰላም ለኤልሳቤጥ እንተ ወደሳ ወአልዓላ: ሉቃስ ወንጌለ ሶበ ጸሐፈ ለታኦፊላ: ሐገረ ይሁዳ አሜሃ ሶበ በጽሐት እምገሊላ: ተሐስየ በውስተ ከርሣ ወአንፈርዓጸ ዕጉዋላ: ለማርያም ድንግል ሶበ ሰምዓት ቃላ:: +"+ ሲሉ አወድሰዋታል:: =>ከቅድስት እናታችን ኤልሳቤጥ ክብሯንና በረከቷን ይክፈለን:: :-መ/ር ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧 💧https://t.me/zenaakidusan 💧💧 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧 .......... የቴሌግራም ቻናላችንን በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣የዜና ቅዱሳን ቤተሰብ ይሁኑ!!!
69
14
+1
No text...
69
15
🕤🕤የየካቲት ፲፭ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ቅዳሴ ቤተክርስቲያኖሙ ለ፵ ሐራ ሰማየ🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን ስብስጥ+2
🕤🕤የየካቲት ፲፭ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ቅዳሴ ቤተክርስቲያኖሙ ለ፵ ሐራ ሰማየ🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን ስብስጥያ በምትባል አገር የሰማዕታት አርባ ሐራ ሰማይ ቤተ ክርስቲያናቸው ለከበረችበት በሰላም አደረሰን። 🌿🌿# ❇️#ስብስጥያ በምትባል አገር የሰማዕታት አርባ ሐራ ሰማይ ቤተ ክርስቲያናቸው ተከበረች፦ ይህች ቤተ ክርስቲያን በስማቸው አስቀድማ ተሠራች ታላቁ አባት ባስልዮስም አከበራት ስለርሳቸውም ድርሳናትን ደረሰ የካቲት15 በዚችም ዕለት በዓልን አደረገላቸው። 🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏 #ምንጭ፦ የካቲት 15 ስንክሳር። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
76
16
🕤🕤የየካቲት ፲፭ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ገዳማዊ አባ በፍኑትዮስ 🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን በገድል ተጠምዶ ለኖረ የገዳማውያን አባቶችን ገድል ለጻፈ ብዙ ለደከመ ፤በበረሀ ውስጥ በመግባቱ ከርኃብ የተነሣ ሥቃይ ለደረሰበት፤ ያለምግብ ሦስት ቀን ከቆየ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ሰውነቱን ሁሉ አፉንም ለዳሠሠው ፤ያለ ምግብም ዐሥራ ሰባት ቀን ለኖረ፤ስለእነርሱም ብዙ ምሥጢራትን ላወቀ ለአባ በፍኑትዮስ ለዕረፍት በዓልና በሰላም አደረሰን።🌿🌿# ❇️#ይህም አባት ከታናሽነቱ መንኵሶ በጾምና በጸሎት በስግደትም እየተጋ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ። ያማረ ምንኵስናውን ሥራ ፈጸመ ጊዜ መነኰሳት ከሚኖሩበት ገዳማት ርቆ ወደሚገኝ። በርሀ ውስጥ ይገባ ዘንድ የከበሩ ገዳማውያንንም ይጐበኛቸው ዘንድ ለሚያነቧት ጥቅም ትሆን ዘንድ ገድላቸውንም እንዲጽፍ ልዑል እግዚአብሔር አዘዘው። በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ራሱን ዘንበል አድርጎ ወደ ውስጠኛው በርሀ ገባ በመንደር ውስጥ እንደ ሚዞር ሰው በዱር መካከል ዞረ። ከገዳማውያንም ብዙዎችን አገኛቸውና ዜናቸውን ተረድቶ ገድላቸውን ጻፈ ከውስጣቸውም የከበሩ ገዳምውያን ጢሞቴዎስና አቡናፍር አሉ። ❇️#ይህንንም አባት በፍኑትዮስ ወደ ውስጠኛው በርሀ በመግባቱ ከርኃብ የተነሣ ሥቃይ ደርሶበታል ያለምግብ ሦስት ቀን አድሮአል። ከዚያም በኋላ ተርቦ ለሞት ተቃረበ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ሰውነቱን ሁሉ አፉንም ዳሠሠው ያለ ምግብም ዐሥራ ሰባት ቀን ኖረ። ❇️#ዳግመኛም ከቶ ሰው ሳያዩ ስድሳና ሰባ ዓመት ከዚያም የሚበዛ የሚያስደንቅ የገዳማውያንን ኑሮአቸውን ተናገረ ወደ ውስጠኛው በረሀ በሚገቡ ጊዜ እርሱን ስለሚወጓቸው ከርኵሳን መናፍስትና ከሚያስፈሩ አራዊት ስለሚደርስባቸውም ፈተና ተናገረ ከዚህም በኋላ በትዕግሥታቸው የሚገዙላቸው ይሆናሉ አራዊትም እንደ ባሮች ያገለግሏቸዋል ቅዱስ ቊርባንንም እንዴት እንደሚቀበሉ ደግሞ ተናገረ በዕለተ ሰንበት የመድኃኒታችንን ክርስቶስን ሥጋና ደም መላእክት አምጥተው ያቀብሏቸዋልና ከገነትም ፍራፍሬዎችን ይሰጧቸዋል። ለዚህም አባት ስለ እሊህ ድንቆች ሥራዎች አይቶ ምስክር ሊሆን የተገባው ሆነ ከዚያም በኋላ የካቲት15 በሰላም ዐረፈ። 🙏🙏#ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በፍኑትዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏# #ምንጭ፦ የየካቲት 15 ስንክሳር። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
69
17
No text...
69
18
🕤🕤የየካቲት ፲፭ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ገዳማዊ አባ በፍኑትዮስ 🍁# ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን በገድል ተጠምዶ ለኖረ የገዳማውያን አባቶችን ገድል ለጻፈ ብዙ ለደከመ ፤በበረሀ ውስጥ በመግባቱ ከርኃብ የተነሣ ሥቃይ ለደረሰበት፤ ያለምግብ ሦስት ቀን ከቆየ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ሰውነቱን ሁሉ አፉንም ለዳሠሠው ፤ያለ ምግብም ዐሥራ ሰባት ቀን ለኖረ፤ስለእነርሱም ብዙ ምሥጢራትን ላወቀ ለአባ በፍኑትዮስ ለዕረፍት በዓልና በሰላም አደረሰን።🌿🌿# ❇️#ይህም አባት ከታናሽነቱ መንኵሶ በጾምና በጸሎት በስግደትም እየተጋ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ። ያማረ ምንኵስናውን ሥራ ፈጸመ ጊዜ መነኰሳት ከሚኖሩበት ገዳማት ርቆ ወደሚገኝ። በርሀ ውስጥ ይገባ ዘንድ የከበሩ ገዳማውያንንም ይጐበኛቸው ዘንድ ለሚያነቧት ጥቅም ትሆን ዘንድ ገድላቸውንም እንዲጽፍ ልዑል እግዚአብሔር አዘዘው። በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ራሱን ዘንበል አድርጎ ወደ ውስጠኛው በርሀ ገባ በመንደር ውስጥ እንደ ሚዞር ሰው በዱር መካከል ዞረ። ከገዳማውያንም ብዙዎችን አገኛቸውና ዜናቸውን ተረድቶ ገድላቸውን ጻፈ ከውስጣቸውም የከበሩ ገዳምውያን ጢሞቴዎስና አቡናፍር አሉ። ❇️#ይህንንም አባት በፍኑትዮስ ወደ ውስጠኛው በርሀ በመግባቱ ከርኃብ የተነሣ ሥቃይ ደርሶበታል ያለምግብ ሦስት ቀን አድሮአል። ከዚያም በኋላ ተርቦ ለሞት ተቃረበ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ሰውነቱን ሁሉ አፉንም ዳሠሠው ያለ ምግብም ዐሥራ ሰባት ቀን ኖረ። ❇️#ዳግመኛም ከቶ ሰው ሳያዩ ስድሳና ሰባ ዓመት ከዚያም የሚበዛ የሚያስደንቅ የገዳማውያንን ኑሮአቸውን ተናገረ ወደ ውስጠኛው በረሀ በሚገቡ ጊዜ እርሱን ስለሚወጓቸው ከርኵሳን መናፍስትና ከሚያስፈሩ አራዊት ስለሚደርስባቸውም ፈተና ተናገረ ከዚህም በኋላ በትዕግሥታቸው የሚገዙላቸው ይሆናሉ አራዊትም እንደ ባሮች ያገለግሏቸዋል ቅዱስ ቊርባንንም እንዴት እንደሚቀበሉ ደግሞ ተናገረ በዕለተ ሰንበት የመድኃኒታችንን ክርስቶስን ሥጋና ደም መላእክት አምጥተው ያቀብሏቸዋልና ከገነትም ፍራፍሬዎችን ይሰጧቸዋል። ለዚህም አባት ስለ እሊህ ድንቆች ሥራዎች አይቶ ምስክር ሊሆን የተገባው ሆነ ከዚያም በኋላ የካቲት15 በሰላም ዐረፈ። 🙏🙏#ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በፍኑትዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏# #ምንጭ፦ የየካቲት 15 ስንክሳር። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
87
19
+1
No text...
73
20
🕤🕤የየካቲት ፲፬ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ🍁 ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿
🕤🕤የየካቲት ፲፬ ስንክሳር🕗🕗 🍀🍀ዜና ቅዱሳን🍀🍀 🍁#ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ🍁 ❇️#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!❇️ 🌿🌿#እንኳን ለእስክንድርያ ሀገር ሰባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት ለአባ ቄርሎስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። ❇️#ይህም አባት ፍዩም ከምትባል አገር ነው። በእርሷም ቅስና ተሹሞ ኖረ ከዚህም በኋላ ከዚያ፡ ለቆ ከምስር ከተማ ውጭ ወደ ሆነች የኢትዮጵያውያን የጒድጓድ ውኃ ወዳለበት ወደ ቅዱስ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ በውስጡም ታላቅ ተጋድሎን እነተጋደለ ብዙ ዘመናትን ኖረ። ❇️#የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ውዴታው ይዘው በእስክድርያ አገር ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ በቊርባንና በጸሎት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሊሠሩት የሚገባቸውን ለካህናት ሦርዓትን ሠራ። በሹመቱም ሰባት ዓመት ከዘጠኝ ወር ከሃያ ሰባት ቀን ኑሮ የካቲት14 በሰላም ዐረፈ። 🙏🙏#ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። 🙏🙏# 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔔 https://t.me/zenaakidusan 🔔 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆 🔔...በመጫን የቅዱሳኑን የህይወት ዜና ያጣጥሙ፣
108