en
Feedback
Addis Post

Addis Post

Open in Telegram
3 889
Subscribers
-124 hours
-347 days
-17230 days
Posts Archive
በድንገት እኩል ለሊት ወይም ሊነጋ ሲል ከእንቅልፋችን ምንነቃበት 3 ምክንያቶች? "ነጋ ወይስ አልነጋም" ብለን ስልካችንን በተደጋጋሚ ቼክ ምናረድ ሰዎች ጥቂት አደለንም፣ ግን ለምን ብላችሁ እራሳችሁን ጠይቃችሁ ታውቃላችሁ? ምክንያቱን ካወቅክን ለመፍትሄው አንቸገርም። 1. ከመጠን ያላፈ ጭንቀት: ምናልናት ነገ ጠዋት ሚጠብቀን ሚያጓጓ ወይም ሁሉ ነገራችንን ሚፈትን ስራ ይጠብቀን ይሆናል፡ ጭንቀት መነሻው ብዙ ቢሆንም፣ ፍርሃትን ያቀፈ የስሜት ስብስብም ነው። አብዛኛው የስነ-ልቦና አማካሪዎች እንደሚሉት፡ ጭንቀት የአብዛኛው ሰው እንቅልፍ አለመተኛት ምክንያትም ነው። ስለዚህ የመንቃት ከዛም በትግል የመተኛት ድግግሞሽ ውስጥ እንገባለን። ጭንቀታችን ሰው እንደሞናችን ሚጠበቅ ቢሆንም፣ ጭንቀትን ለመቀነስ ደሞ ህይወት እድል ሰታናለች። የሁላችንም ችግር ይለያያል። 2. የተፋረሰ የእቅልፍ ሰዓት: እራሳችንን ማስለመድ ያለበት ነገር፣ ምንተኛበትን እና ምንነቃበትን ሰዓት ተመሳሳይ ማድረግ ነው። ስንፈልግ ቀን፣ ስንፈልግ ማታ መተኛታችን፣ ለሊት ላይ እንቅልፍ ጨርሰን እንድድነቃ ያደርገናል። 3. የጤና ችግሮች: የስኳር መጠን መውረድ፡ ቶሎ ቶሎ መሽናት.....ድብርት ምናምን...ተያያዥ ህመሞች እንቅልፋችንን በሰላም እንዳንተኛ ያደርጋሉ። @addisposts ነን! መልካም ሰኞ!

እንደምን አደራችሁ!! መልካም የስራ ቀን! መልካም ሰኞ @adissposts ነን፡

ትምህርቱን አቋርጦ ትልቅ ህልም ሰንቆ፣ አስደናቂ ሄሊኮፕተር በመስራት የራሱን ህይወት የቀጠፈው ወጣት...... ይህ ወጣት ከ3 አመታት በፊት የ7ኛ ተማሪ ነበር። ት/ቤት ገብቶ ብዙም ደስተኛ ስላልነበር በአነስተኛ ብረታ ብረቶች ስራ ይሰራ ነበር። ብዙም ሳይቆይ ወዲያው በፈጠራ ስራ ተጠመደ። በአነስተኛ ጉልበት ረጅም ርቀት ምትሄድ ባለ 1 መቀመጫ ሄሊክፕተር መስራት ጀመረ። ወደ 1600 ሰዓታትም በፈጀው ሙከራ እና ስራ የሚደንቅ ውጤት ሲያይ ነበር። ለ3-4 አመታት በዚህ ሙከራ ተሰማርቶ፣ በአከባቢው እንደ እብድ ሲታይ፣ ግን ደሞ ማይታመን ውጤት በቅጽበት እያሳየ ነበር። ለመጨረሻ ሙከራ ያደረገበትን ምሽት እየቀረጸውም ነበር፣ ድንገት ግን ፊልም ሚመስል አሳዛኝ ክስተት ሆነ። የሄሊኮፕተሩ ተሽከርካሪ ብረት ወልቆ ወደ ውስጥ በመሹለክ ጭንቅላቱን አገኘው። ሼይክህ እስማኤል ወዲያው ሆስፒታል ቢወሰድም፣ ህይወቱን ማትረፍ አልተቻለም። በወቅቱ አለም መነጋገሪያ አድርጎትም ነበር። ብሩክ ቀን እየተጠነቀቃችሁ! እኛ @addisposts ነን። ሼር ያድርጉ!

ኢራን በባለፈው በሶሪያ በሚገኘው ቢሮዬ እስራኤል ለከፈተችብኝ ጥቃት ምላሽ ሰጥቻለሁ ስትል አስታወቀች። 300 ድሮኖችን በእስራኤል ሰማይ ላይ አዝንባለች። እስራኤል በበኩሏ 99% የሚሆነውን መክቻለው አክሽፌያለሁ ብላለች። "የቃል ኦፕሬሽን" ብላ ኢራን የሰየመችው አዲሱ ጥቃት፣ ወደ ጎረቤት ሀገራት ግጭት እንዳይስፋፋ የተሰጋ ሲሆን፣ የባይደን መንግስት ኦፕሬሽኑን "የሽብር ጥቃት" ብሎ ጠርቶታል። የባይደን መንግስት በዚህ ጉዳይ ከእስራኤል ጎን መቆሙን ቢያሳውቅም፣ የእስራኤልን የስለላ ድርጅት ሞሳድን የሚገዳደር እንቅስቃሴ አሁንም ቀጥሏል። ኢራን አሁንም ቢሆን እስራኤልን ማስፈራራቷ አይሏል። "አሁንም በድጋሜ" ጥቃት ከከፈተችብኝ ቅጣቴንም ከበድ አረገዋለሁ ብላለች። አሜሪካንም በግልጽ "አይመለከትሽም" የሚል ብላሽ ሰታታለች። አለም የእስራኤልን የበቀል ጥቃት ምን ሊሆን እንደሚችል እየጠበቀ ነው። @addisposts ነን የትም ሽፋን ያላገኙ ምርጥ መረጃዎችን ያግኙ

ኢራን ምሽቱን እስራኤል ላይ የድሮን ዝናብ ስታዘንብ ማምሸቷን ተገለጸ። ይህን ተከትሎ እስራኤል በግዛቷ ድንገተኛ ደውል ደውላለች። እስራኤል በዘመኗ እንደዚህ አይነት ውርጅብኝ እና ጥቃት ወርዶባት እንደማያቅ አሳውቃለች። አሁን ላይ ቀጥታ በምሽት የእስራኤል ሰማይ ላይ የኢራን ድሮኖች እንደ እሳት ሲወነጨፉ ታይቷል። ኢራን ከድሮን በተጨማሪ ሮኬቶችን ቀላቅላ ተኩሳለች። የእስራኤል እና ኢራን ፍጥቻ ወዴት ያመራ ይሆን? ከራሺያ ጋር ትግል የቀጠለው የዩክሬኑ ዘነለስኪ፣ አሜሪካ እሱን ረስታ ትኩረቷ ሁሉ እስራኤል ላይ ሆኗል። @addisposts ነን አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ።

የገንዘብ የመግዛት አቅም አሁን ካለበት የባሰ ከቀነሰ ኑሯችን ወዴት ያመራ ይሆን? ኢትዮጵያ ጫና ላይ ነች፣ በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ሌላ ራስ ምታት እና ትኩሳት ወደ ህዝባችን እየመጣ ነው። ኢትዮጵያ ምን አይነት አጣብቂኝ ውስጥ ነች? ኢትዮጵያ እምቢ ወይም እሺ ብትል፣ በሁለቱም አማራጭ መጥፎ ውጤቶች አሉበት። ብድር ልውሰድ ብትል ዛሬ ሱቅ ገብተን በ100 ብር ምንገዛው እቃ 180-250 ብር ይንራል። አይ ብድር አንፈልግም ካልንም ደሞ የአጠቃላይ ብድራችን 28 ቢሊዮን ዶላር ሽግሽግ ሳይኖረው፣ ብድር መክፈል እንደማንችል ተቆጥሮ፣ አለም አቀፍ ኢንቨስተሮች የቢዝነስ ሰዎች ሁሉ መንገዳቸውን ዘግተው፣ ኢኮኖሚውን ዜሮ ያረጉታል። አሁን አሁን ከእስር በእስር ግጭት በተጨማሪ በአለም መድረክ የታወቅንበት ጉዳይ፣ የኢኮኒሚያችን መቆርቆዝ ነው።

ኢራን የእስራኤልን ግዙፍ ጀልባ በቁጥጥር ስር አውላ ወሰደች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጠባቂ ሄሊኮፕተር የእስራኤል ንብረትነት ያለውን ግዙፍ ጀልባ ሲቆጣጠር የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ተለቋል። እስ
ኢራን የእስራኤልን ግዙፍ ጀልባ በቁጥጥር ስር አውላ ወሰደች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጠባቂ ሄሊኮፕተር የእስራኤል ንብረትነት ያለውን ግዙፍ ጀልባ ሲቆጣጠር የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ተለቋል። እስራኤል ምን አለች? የእስራሌል ባለ ስልጣናት ኢራን ዋጋ ትከፍልበታለች በማለት መልዕክት ልከዋል። ጀልባው እንዴት ሊወሰድ ቻለ? ጀልባው ከአረብ ኢሜሬትስ ተነስቶ በህንድ ውቂያኖስ በኩል በማለፍ በንግድ ስራ ላይ ያተኮረ ቢሆንም፣ ኢራን ግን እስራኤልን ማመን ማቆሟን ተገልጿል። የኢራን መንግስት ለእገታው እውቅና የሰጠ ሲሆን፣ እስራኤል በበኩሏ ይህ የለየለት የውንብድና ስራ በመሆኑ በአለም አቀፍ ህግ ያስከስስሳል ብላለች። ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ታጣቂዎችን እንደምትደግፍ እንዲሁም እስራኤልን ለማጥፋት ከፍተኛ ፖለቲካዊ ፍላጎት ያላቸውን ሀይሎች ተገን አድርጋ ልትወጋት ደፋ ቀና እያለች መሆኑን ባለ ስልጣናቱ ጨምረው ገልጸዋል። ኢራን በባለፈው እስራኤል በሶርያ ዲፕሎማቲክ ቢሮ በወሰደችው የአየር ጥቃት በተፈጠረው ጥፋት እና የንጽሁሃን እልቂት፣ እስራኤል ከኢራን ከባድ አጸፋ ይወሰድብኛል ብላ እየፈራች መሆኑን ተናግራለች። እስራኤል ከኢራን መልሶ ጥቃት እንደሚደርስባትም በማወቅ ከአሜሪካ እና መሰል ሀገሮች ብዙ ድጋፍን እየተቀበለች ዝግጅቷን ቀጥላለች። @addisposts ነን

አሜሪካ እና ቻይና ሰማዩን ለመያዝ የገቡበት ትንቅንቅ። አስተውለን ከሆነ ወፎች፥ አሳዎች እንዲሁም በርካታ ህይወት ያላቸው ፍጥረታት ተሰብስበው ይንቀሳቀሳሉ፡ ይህም ሊያጠቃቸው የሚፈልግን ግራ ያጋባል።
+1
አሜሪካ እና ቻይና ሰማዩን ለመያዝ የገቡበት ትንቅንቅ። አስተውለን ከሆነ ወፎች፥ አሳዎች እንዲሁም በርካታ ህይወት ያላቸው ፍጥረታት ተሰብስበው ይንቀሳቀሳሉ፡ ይህም ሊያጠቃቸው የሚፈልግን ግራ ያጋባል። አሜሪካ ከ10 አመታት በፊት ያበለጸገችው ቴክኖሎጂ እንደ አንዳንድ ተመራማሪዎች ከሆነ ከኑውክለር የባሰ አደገኛ ነው። በመቶ እና በሺህ የሚቆጠሩ ጥቃቅን ድሮኖች እንደ ንብ ሲጓዙ፡ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም AI ታግዘው እንደፈለጉ ቦታ ሲቀይሩ፡ የጠላትህ ድሮን መጥለፊያ ግራ አጋብቶ እንዲጠቃ ያረገዋል። ከሰሞኑ ስለዚህ ቴክኖሎጂ ምን አዲስ ነገር አለ? ቻይና ይህንን ዘርፍ ተቀላቅላ ከፍተኛ የምርምር ውጤት እያገኘች ሲሆን፡ አሜሪካ በበኩሏ ላለመቀደም ብዙ እየሰራችበት ነው። ይህ ቴንክኖሎጂ ከክላስተር ቦምብ ጋር ቢመሳሰልም፡ ግን በሰው ሰራሽ አስተውሎቱ እና ውስብስብ ቀመሩ ድንቅ አድርጎታል። ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ስራ ላይ አውላ አመርቂ ውጤት ያሳየችው ያስመሰከረችው እስራኤል ነች። ንቦች በብዛት ሆነው ሲሄዱ ሚያሰሙትን አስፈሪ ድምጽ፡ ይህ የድሮን ውጤት ምድር ላይ የከተመ ጠላ በማስፈራራት ስነ ልቦና የማዳከም ብቃት አለው። @addisposts ነን 🙏🙏🙏

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በቁጥጥር ስር ዋለ። ከጥቂት ወራት በፊት ታስሮ ከእስር የተፈታው የቀድሞ የአውሎ ሚዲያ ባልደረባ አሁን ላይ " አልፋ ቲቪ " የተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ መስራች እና አዘጋጅ ጋዜ
+1
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በቁጥጥር ስር ዋለ። ከጥቂት ወራት በፊት ታስሮ ከእስር የተፈታው የቀድሞ የአውሎ ሚዲያ ባልደረባ አሁን ላይ " አልፋ ቲቪ " የተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ መስራች እና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ጠበቃ ታደለ ገብረመድህንን ዋቢ አድርጎ አዲስ ስታንዳር አስነብቧል። የጋዜጠኛውን መታሰር ባለቤቱ ሄለን አባተ አረጋግጠዋል። በሌላ በኩል ፤ ትላንት የፊንፊኔ ኢንተግሬትድ ብሮድካስቲንግ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ሰቦንቱ አህመድ በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን (በለቡ ፖሊስ ጣቢያ ነበረች) ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ መወሰዷን የጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ለሚ ታዬ መናገራቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ አስነብቧል። ሰቦንቱ ትላንት በፖሊስ የተያዘችው አመሻሽ ላይ ከስራ ቦታዋ ስትወጣ ሲሆን በቁጥጥር ስር ያዋሏት ፖሊሶች የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመያዛቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። አክለውም፤ ትላንት ለቡ ፖሊስ ጣቢያ እያለች አነጋግረዋት እንደነባርና የተያዘችበት ምክንያት ምን እንደሆነ እንዳልተገለጸላት ፍርድ ቤትም እንዳልቀረበች ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ " አስታውቀዋል። ጋዜጠኛዋ ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ ከተማ እንድትወሰድ ተደርጓል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" Galatoomaa Tour " የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ወደ በሰኔ እና ሃምሌ ወር 202
+1
" Galatoomaa Tour " የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ወደ በሰኔ እና ሃምሌ ወር 2022 ወደ #ሰሜን_አሜሪካ እና #አውሮፓ እንደሚጓዙ ታውቋል። አመራሮቹ ጉዟቸውን " Galatoomaa Tour " በሚል የሚያደርጉ ሲሆን በተለያዩ ከተሞች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጉዞውን በተመለከተ እስካሁን በሁለቱ ወራት የሚያዳርሷቸውን ከተሞች እና ቀናት ይፋ ከመሆን በዘለለ ለጊዜው በዝርዝር ይፋ የተደረገ መረጃ የለም። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC ትላንት በቁጥጥር ስር የዋሉት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ አጠቃላይ እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች / የሚዲያ አካላትን ቁጥር 16 አድርሶታል። የኢትዮጵያ
+1
#EHRC ትላንት በቁጥጥር ስር የዋሉት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ አጠቃላይ እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች / የሚዲያ አካላትን ቁጥር 16 አድርሶታል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ " የሚዲያ ባለሙያዎች መታሰራቸው ከመገናኛ ብዙሃን ህጉ ጋር የሚጻረርና መዘዙ ከመገናኛ ብዙሃን እና ሃሳብን ከመግለጽ የዘለለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው " ብለዋል ከመገናኛ ብዙሀን ህግ ጋር በተጻራሪ ከፍርድ በፊት ረዘም ላለ ጊዜ አስሮ ማቆየት፣ ታሳሪዎች ያሉበትን ቦታ አለመግለጽ እና መደበኛ ባልሆነ እስር ቤት ማሰር ሁኔታውን እንደሚያባብስ በመግለፅ ሁሉም የሚዲያ አካላት በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ኮሚሽኑ ሁኔታውን መከታተሉን እንደሚቀጥልም አሳውቀዋል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ፌዴራል_ፖሊስ_ወንጀል_ምርመራ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሙሊሳ አብዲሳ የሰጡት ማብራሪያ ፦ " ህግ ማስከበር ሲባል ብሄርን አይለይም፤ ሃይማኖትን አይለይም ፤ የፖለቲካ status አይለይም ፤ የሚዲያ አክቲቪስት ማንም ማንም ይሁን የSocial Status ፣ ሃይማኖቱ ምንም መሰረት አያደግም። ህግ ለሁሉም እኩል ነው። እንደ ፖሊስ ሞያዊ ነፃነቱን ጠብቀን የምርመራ ስራ ጥቆማ ሲደርሰን በየትኛውም አካል ላይ ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው። እንደሚታወቀው በአሁን ሰዓት ብዙ የሚዲያ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ብሄርን ከብሄር የሚያጋጩ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ ፣ ጥርጣሬን የሚፈጥሩ የህዝቦቻችንን ፣ አጠቅላይ የኢትዮጵያን ህዝብ አብሮነት የሚፈታተኑ እነሱ ጥቅም የሚያገኙበትን በሚዲያ ዘመቻ የሚያደርጉትን በሽብር ድርጊት ውስጥ የተሳተፉትን ሰዎች በማስረጃ ላይ ሆነን መረጃ በመሰብሰብ በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ወደ ህግ እያቀረብን ነው። ስለዚህ የሆነ ሚዲያ ወይ ጋዜጠኛ የሆነ ምንም ቢሆን እንደ defense ሊቀርብ አይችልም። በወንጀል ውስጥ የተሳተፈ መረጃ የተገኘበት ማንኘውም ሰው ላይ እርምጃ ይወሰዳል፤ በህግ ይጠየቃል፤ ግልፅ በሆነ ነፃ በሆነ ፍርድ ቤት አቅርበን ምርመራ ስራ እንሰራለን። ስለዚህ በአሁን ሰዓት የሚዲያ ስራ ላይ የተሳተፉ ሰዎች እሱን እየተጠቀሙ አጠቃላይ stability እንዳይኖር የሆነ title እየሰጡ እንደ ገቢ ምንጭ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልተረዳው ነገር እነኚህ አክቲቪስት የተባሉ ታሰሩ የተባሉ ግለሰቦች እንደ ገቢ ምንጭ የሚጠቀሙት አይነት ነው ያለው። በምርመራ እንዳገኘነው አንድ ግለሰብ ከ4 ዩትዩበሮች ጋር ውል አስሯል፣ ከአንዱ ዩትዩበር 25 ሺህ ብር ነው የሚከገለው በአንድ ጊዜ እስከ 100 ሺህ ነው የሚከፈለው፤ ይሄን ለማድረግ ተመልካች እንዲያገኝ ለማድረግ ብሄርን ከብሄር የሚያጋጭ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጭ ፣ ወይም የመንግስትን ተቋም ፣ ወይም የመንግስትን ተሿሚዎች በሚያሸማቅቅ መልኩ ግልፅ በሆነ መልኩ characterize በማድረግ title እየሰጡ እንዲህ እያደረጉ ተመልካችን፣ like , share በብዛት እንዲያገኙ ብዙ ነገር በማድረግ ይሄን መሰረት በማድረግ destabilize በማድረግ የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን፣ የሃሰት የውሸት ፕሮፖጋንዳዎችን በመልቀቅ ህዝቦች አብረው እንዳይኖሩ ሀገሪቱ በሰላም ተረጋግታ እንዳትኖር አጠቃላይ የማወክ ስራ እና ጥርጣሬ በሚፈጥር መልኩ ጥላቻን በውሸት ዘመቻ እያደረጉ ህዝቡ ላይ ይሄን እየጫኑ ለራሳቸውን የገቢ ምንጭ አድርገው ሀገሪቷን አደጋ ላይ ለመጣይ የሚሰሩ አካላት ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት። ይሄንን ደግሞ ፖሊስ ህግን መሰረት በማድረግ ፍርድ ቤት በማቅረብ የጊዜ ቀጠሮ በመጠየቅ በራሳቸው ፍላጎት በሚፈልጉት ጠበቃ ተወክለው በቤተሰቦቻቸው እየተጠየቁ ይሄን የምርመራ ስራ ፣ የህግ ማስከበር ስራ በደንብ እየተሰራ ነው። ስለዚህ በአጠቃላይ ማንኛውም ሰው ከህግ በታች ነው። ከህግ በታች እስከሆነ ድረስ ጥቆማ የቀረበበትን እንደፖሊስ ሙያን መሰረት አድርጎ የህግ የማስከበሩን ስራ ማንኛውም ሰው ላይ በየትኛውም ላይ ብዙ እሱን የሚከተል ሰው ሊኖር ይችላል ከዚህ በፊት እንደተደረገው ፣ የሃይማኖት ሰው ሊሆን ይችላል፣ ማንኛውም ሰው ሊሆን ይችላል ዋናው መሰረት የህግ ስህተት አለ ? ወይስ የለም ? የሚለው ነው። ስለዚህ እስካሁን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ስም ብዙ ነገሮች ተችለዋል በአሁን ሰዓት ግን የለየለት የሽብር ስራ ፣ የሽብር ፈጠራ ፣ ሀገርን የማፍረስ ስራ ፣ ህግ የሌለ እስከማስመሰል ፣ የፍትህ ተቋማት እርምጃ መውሰድ አይችሉም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሶ ሀገርን የማፍረስ ተልዕኮ ላይ እየሰሩ ያሉት አካላት ላይ የህግ የበላይነት ለማስከበር ከምን ጊዜውም በላይ የፌዴራል ፖሊስ ከሌሎች የፍትህ ተቋማት ጋር በመሆን የምርመራ ስራን እየሰራ ይገኛል። " @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የ " ፍትህ መጽሔት " ማኔጂግ ዳሪክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ " የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በህዝብ ዘንድ አመኔታ ለማሳጣትና ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት ወንጀል " መጠርጠሩን መርማሪ
+1
#Update የ " ፍትህ መጽሔት " ማኔጂግ ዳሪክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ " የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በህዝብ ዘንድ አመኔታ ለማሳጣትና ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት ወንጀል " መጠርጠሩን መርማሪ ፖሊስ ዛሬ ለፍ/ቤት ገልጿል። ፖሊስ ጋዜጠኛ ተመስገን በተጠረጠረበት ሁከትና አመጽ ማስነሳት ወንጀል á‰ áˆáˆľáŠ­áˆ­ ለማስመረጥና የምስክር ቃል ለመቀበል ተጨማሪ ማስረጃ ለመሰብሰብ እና የምርመራ ስራውን አጠናክሮ ለመቅረብ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንዲሰጠው ችሎቱን ጠይቋል። የጋዜጠኛ ተመስገን ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ መከላከያን መተቸት እምነት ማሳጣት አለመሆኑን ጠቅሶ ተከራክሯል። በምስክር ማስመረጥ ለተባለውም ቢሆን ተመስገን አገር የሚያውቀው በመሆኑ ማስመረጥ ጥያቄው ተገቢ እንዳልሆነ ገልጿል። ጠበቃው አክሎም ጋዜጠኛ ተመስገን የሚሰራበት ሚዲያ ፍቃድ ያለው ህጋዊ ተቋም እንደመሆኑ ወንጀል ሰል እንኳ ቢባል በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ áŠĽáŠ•áŒ‚ በጊዜ ቀጠሮ ሊጠየቅ እንደማይገባ ተከራክሯል። ፖሊስ በዩቱዩብ ቃለመጠይቅ እያደረገ ከሌሎች አካላት ጋር ሁከትና አመጽ የማነሳሳት ሾል እየሰሩ ነው ሲል ባቀረበው የመነሻ ምርመራ ሪፖርትን በተመለከተ ጋዜጠኛ ተመስገን ከ4 አመት ወዲህ ምንም አይነት ከማንም áŒ‹áˆ­ ቃለመጠየቅ እንዳላደረገ ጠበቃ ሄኖክ አብራርቷል።  á‰ áˆšáˆ°áˆŠá‰ á‰ľ ሚዲያ የሀገር áˆ˜áŠ¨áˆ‹áŠ¨á‹Ť ተቋምም ቢሆን ተተችቻለው በህዝብ ዘንድ እምነት አጣሁ ብሎ አለመቅረቡን  áŒ á‰…ሰው ቢቀርብ በመገናኛ ብዙሀን አዋጅ መሰረት በሚሰራበት ሚዲያ ማስተካከያ áŠ¨áˆ›á‹ľáˆ¨áŒ እንደማይታለፍ መከራከሪያ ነጥቡ ጠቅሷል። ያንብቡ ⬇️ https://telegra.ph/Tarik-Adugna-05-27 ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት📣 የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ፤ " የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ወደ ቅዱስ ላልይበላ ዓለም አቀፍ ቅርስ ሊመለከት ይገባል " ሲሉ ጥሪ አ
+1
#ትኩረት📣 የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ፤ " የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ወደ ቅዱስ ላልይበላ ዓለም አቀፍ ቅርስ ሊመለከት ይገባል " ሲሉ ጥሪ አቀረቡ። ብፁዕነታቸው ቅዱስ ላልይበላን በማስመልከት ዛሬ በተሰጠ መግለጫ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እና በነበረው ጦርነት የቅዱስ ላልይበላ ቅርስ የቱሪዝም እና የከተማው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ጫና ውስጥ መውደቁን ገልጸዋል፤ በዚህም አገልጋዮች ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን አሳውቀዋል። ቅዱስ ላልይበላ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሐብት እንደመሆኑ አቅም በፈቀደ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ለድጋፍ እጁን እንዲዘረጋ ጥሪ አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው ሁለችንም የድርሻችንን በመወጣት ቅርሳችን እንጠብቅ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ዜጎች ድጋፋቸውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ አቢሲኒያ እና ዳሽን ባንኮች በ 👉 0712 የባንክ የሒሳብ ቁጥር ማድረግ ይችላሉ። ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911061164 እና 0913912457 መደወል ይቻላል። ምንጭ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
ቀይ መስቀል ድጋፍ እያደረገ ነው። የደቡብ ኦሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በቶልታ፣ መጸርና በርካ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አፍርጓል። የሰሞኑን ፀጥታ ችግር ተከትሎ በደቡብ አሪ ወረዳ መፀር፣
+5
ቀይ መስቀል ድጋፍ እያደረገ ነው። የደቡብ ኦሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በቶልታ፣ መጸርና በርካ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አፍርጓል። የሰሞኑን ፀጥታ ችግር ተከትሎ በደቡብ አሪ ወረዳ መፀር፣ ቶልታና በርካ አካባቢዎች ከፍተኛ የቤት ቃጠሎና የንብረት ውድመት የተከሰተ ሲሆን ነዋሪዎቹም ከስፍራው ሸሽተዋል፡፡ ራሳቸውን ለማዳን በሐይማኖት ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶችና በፖሊስ ጣቢያዎች የተጠለሉት የማኅረሰቡ አካላትን የደቡብ ኦሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከራሱና ማኅበረሰቡን በማስተባባር የዕለትና ሌሎችንም ድጋፍ ለመስጠጥ ችሏል፡፡ የተደረገው ድጋፍ ፦ ለሶስቱም አካባቢዎች ለበርካ፣ ቶልታና መፀር 130 ደርዘን እሽግ ውሃ፣ 3 ሺህ ዳቦ፣ 50 አገልግል እንጀራ፣ 10 ኩንታል ሞኮሮኒ፣ 2 ኩንታል ሩዝ፣ 6 ኩንታል ነጭ ዱቀት፣ 2 ኩንታል ጤፍ፣ 18 ደርዘን ጁስ፣ 6 ደርዘን ብስኩት እና ሌሎችም ይገኙበታል። አሁንም ድጋፉን ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ቀይ መስቀል ጥሪ አቅርቧል፦ ችግር ላይ የወደቁ ወገኖችን ለማገዝ በገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የሚፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ERCS 1000040792981 መላክ እንደሚችሉ ተገልጿል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Udpate በጂንካና አካባቢው ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች 22 ሲፈቱ ቀሪዎቹ ላይ ምርመራ መቀጠሉ ተሰምቷል። ዞኑ ዛሬ በሰጠው መግለጫ የተከሰተው ችግር በቁ
+1
#Udpate በጂንካና አካባቢው ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች 22 ሲፈቱ ቀሪዎቹ ላይ ምርመራ መቀጠሉ ተሰምቷል። ዞኑ ዛሬ በሰጠው መግለጫ የተከሰተው ችግር በቁጥጥር ስር ውሎ ማኅበረሰቡም ወደ ቀደመው የኑሮ ሁኔታ እየተመለሰ ነው ብሏል። የዞኑ ም/አስተዳዳሪና የሰላም እና ፀጥታ ኃላፊ አቶ ደሞ በዛብህ ፤ ከፀጥታው ችግር ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን ካሉበት አድኖ በሕግ ጥላ ሥር የማዋል ሥራ እየተሰራ ነው ያሉ ሲሆን ለጊዜው እስካሁን 132 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፤ ከእነዚህ መካከል በተደረገ የማጥራት ሥራ 22ቱ ዛሬ ተፈተዋል ሲሉ ተናግረዋል። [NB. ትላንት የደቡብ ፖሊስ ሰጥቶ በነበረው ቃል የተያዙ ተጠርጣሪዎች 133 ናቸው ብሎ ነበር] አቶ ደሞ የጸጥታ ኃሎች በሰሩት ስራ አብዛኛው አካባቢ አንፃራዊ መረጋጋት መፈጠሩን ገልፀዋል። በዚህም የቅድመ ማስጠንቀቂያ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚመች መልኩ ተግባራቸውን ለማከናወን ተንቀሳቅሰዋል። ኃላፊው፤ የፀጥታው ኮማንድ ፖስት ባካሄደው ወቅታዊ ሁኔታ ግምገማ በቶልታና መጸር 145 ቤቶች በእሳት የተቃጠሉ ሲሆን ከዚህ መካከል 1 መስጂድ ይገኝበታል ብለዋል። አንድ ቀበሌ ያልተጣራ ያለ በመሆኑ ኮማንድ ፖስቱ በቀጣይ አጣርቶ ለሕዝብ ግልጽ ያደርጋል ሲሉ ገልፀዋል። በጂንካ ዙሪያ 6 ቤቶች መቃጠላቸውን አሳውቀዋል። በፀጥታ መዋቅሩ የተገመገመና የተለየ የተፈናቀሉ አባወራ 237፤ እማወራ 136 በአጠቃላይ 333 አባወራና እማወራዎች ተፈናቅለው በት/ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ተጠልለው ይገኛሉ። 979 ቤተሰቦች ከቤት-ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም ለጊዜው በጸጥታ አካላት ተለዩ ናቸው። የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሪፖርት ሲመጣ ቁጥሩ ከሚጠበቀው በላይ ሊያሻብቅ እንደሚችል ተገምቷል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Russia የሩሲያው ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸውን ሩስያን ለማግለል የሚደረገው ሙከራ አይሳካም ሲሉ ምእራባውያንን አስጠነቀቁ። ሩስያ በዩክሬን የጀመረችውን " ልዩ ወታራዊ ዘመቻ " ተከትሎ
+1
#Russia የሩሲያው ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸውን ሩስያን ለማግለል የሚደረገው ሙከራ አይሳካም ሲሉ ምእራባውያንን አስጠነቀቁ። ሩስያ በዩክሬን የጀመረችውን " ልዩ ወታራዊ ዘመቻ " ተከትሎ ጠንከር ያሉ ማዕቀቦችን በጣሉባት ምእራባውያን እና አሜሪካ ላይ እምነት እንደማይኖራት ገልጻለች፡፡ ፕሬዜዳንት ፑቲን ፥ " በሶቬት ህብረት ጊዜ ጠቅላላ ማእቀብ ተጥሎ ነበር፤ ሙሉ በሙሉ ተገልላም ነበር፤ ነገርግን ሶቬት አሁንም በስፔስ ቀዳሚ ነች " ሲሉ ተደምጠዋል። ፕሬዝደንቱ የመገለል ፍላጎት እንደሌላቸው እና በዚህ ዘመናዊ አለም ማግለል እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡ በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ሩሲያ በዩሪ ጋጋሪ አማካኝነት ወደ ስፔስ ያደረገችው በረራ እና በፈረንጆቹ 1957 የስፑትኒክ አንደኛ ወደ ስፔስ መብረር አሜሪካን አስደንግጦ ነበር፡፡ በወቅቱ አሜሪካ ከሩሲያ ጋር ለመወዳደር ስትል ናሳን አቋቁማ ነበር፡፡ ፕሬዜዳንት ፑቲን በዩክሬን " ወታደራዊ ዘመቻ " ለማድረግ የተገደዱት፤ አሜሪካ ዩክሬንን እና ኔቶን በመጠቀም ለማስፈራራት ስለሞከረች እና ይህንም መከላከል ሲለሚገባ ነው ብለዋል፡፡ ፑቲን ሩሲያ በዩክሬን ሁሉንም የምትፈልገውን አላማ ታሳካለች ብለዋል፡፡ ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Rubel ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በምዕራባውያን ብርቱ የሆነ ማዕቀብ ምክንያት የሩስያ የመገበያያ ገንዘቧ የሆነው #ሩብል ከአሜሪካ #ዶላር አንፃር በእጅጉ ቀንሶ እንደነበር ይታወሳል። ከሳምን
+1
#Rubel ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በምዕራባውያን ብርቱ የሆነ ማዕቀብ ምክንያት የሩስያ የመገበያያ ገንዘቧ የሆነው #ሩብል ከአሜሪካ #ዶላር አንፃር በእጅጉ ቀንሶ እንደነበር ይታወሳል። ከሳምንታት በፊት በተለዋወጥነው መረጃ 1 የአሜሪካ ዶላር በ117.18 የሩስያ ሩብል እስከመመንዘር ደርሶ ነበር። ይህም ፥ የሩሲያው ሩብል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ደረጃ ዋጋው እንዲወርድ አድርጎት ነበር። አሁን ላይ ግን በሩብል እና የአሜሪካ ዶላር ያለው ልዩነት በእጅጉ ጠቧል። ከሳምንታት በፊት በ117.18 ሩብል ሲመነዘር የነበረው የአሜሪካ ዶላር ዛሬ በ80.25 ሩብል እየተመዘረ ይገኛል። 👉 የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ/ም - አንድ የአሜሪካ ዶላር 117.18 ሩብል ፤ 👉 ዛሬ ሚያዚያ 2 ቀን 2014 ዓ/ም - አንድ የአሜሪካ ዶላር 80.25 ሩብል ፤ የምዕራባውያን ጠንካራ ማዕቀቦችን ተከትሎ የኢኮኖሚ ተንታኞች የሩስያ ኢኮኖሚ በአጭር ጊዜ ሊሽመደመድ እንደሚችል እና የከፋ ችግር ላይ እንደምትወድቅ መግለፃቸው ፤ ሩስያ በበኩሏ እየተጣሉባት ያሉት ማዕቀቦች ይበልጥ ነፃና ጠንካራ ሀገር እንደሚያደርጋት መግለጿ ይታወሳል። @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በዝርፊያ ምክንያት የወደቀው የአዋሽ 2 - አሰላ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ጥገና መጠናቀቁ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፥ " በዘራፊዎች ተቆርጦ የወደቀው ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የ
+1
#Update በዝርፊያ ምክንያት የወደቀው የአዋሽ 2 - አሰላ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ጥገና መጠናቀቁ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፥ " በዘራፊዎች ተቆርጦ የወደቀው ከአዋሽ 2 ወደ አሰላ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን በእንጨት ምሰሶ የመተካት ሥራ ተጠናቋል " ብሏል። መጋቢት 24 / 2014 ዓ.ም በዶዶታ ወረዳ እና ጌራ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው የምሰሶ አካላት ዝርፊያ 2 ምሰሶዎች የወደቁ ሲሆን በአካባቢው በከፊል ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ቆይቷል። ለቀናት ሲያከናወን የቆየውን ጥገና ተከትሎ ዛሬ ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ ይከናወናል ተብሏል። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል @tikvahethiopia

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
በቤት ኪራይ ዋጋ መናር ምክንያት የማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ አደጋ ላይ መውደቁ ተሰምቷል። የማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ ፥ በሀገራችን የካንሰር ህመምን መከላከልና ህክምና
+1
በቤት ኪራይ ዋጋ መናር ምክንያት የማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ አደጋ ላይ መውደቁ ተሰምቷል። የማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ ፥ በሀገራችን የካንሰር ህመምን መከላከልና ህክምናው ላይ ማገዝ ከሚያደርጉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች መካከል አንዱ ሲሆን ተከራይቶ በሚሰራበት ግቢ ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚመጡ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የካንሰር ህሙማንን እና አስታማሚዎቻቸውን ማረፊያ በማዘጋጀት የምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ ወጪዎችን ከህክምና ወጪያቸው ጋር በመሸፈን ህክምናቸውን እንዲከታተሉ ያደረጋል። አሁን ላይ ግን በቤት ኪራይ ዋጋ ንረት አጠቀላይ የድርጅቱ ህልውና ከፍተኛ አደጋ ላይ እንደወደቀ ታውቋል። የማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ መስራች አቶ ወንዱ በቀለ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፥ በወር 50 ሺህ ብር ነበር የምንከፍለው ፤ 50 ሺህ ብሩን እራሱ ለመክፈል እየተቸገርን አሁን 65 ሺህ ብር ጨምረውብን በወር 115 ሺህ ብር በፐርሰንት ሲታይ 140 ፐርሰንት ነው የተጨመረብን ፤ በዓመት ወደ 1.4 ሚሊዮን ብር ነው የሚያስከፍለው ይሄ በፍፁም የማይታሰብ እና በእኛ አቅም የሚሆን አይደለም። የሶሳይቲው ፣ የህብረቱ እና የህሙማኑ አገልግሎት አደጋ ላይ ወድቋል" ብለዋል። ጉዳዩን በተመለከተ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ጅማ ዲልቦ በሰጡት ቃል እንዲህ ያለው ችግሩ የማቲዎስ ወንዱን ጨምሮ የብዙ ድርጅቶች ችግር መሆኑን በግለፅ ባለስልጣን መ/ቤቱ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ደብዳቤ በመፃፍ በመናጋገር እየጠየቀ መሆኑን አስረድተዋል። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽንም አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግላቸው የድጋፍ ደብዳቤ እንደተሰጣቸውና ውጤቱ እየተጠበቀ መሆኑን ለቴሌቪዥን ጣቢያው ገልፀዋል። @tikvahethiopia