en
Feedback
Dn Abel Kassahun Mekuria

Dn Abel Kassahun Mekuria

Open in Telegram

ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Dn Abel Kassahun Mekuria

Channel Dn Abel Kassahun Mekuria (@dnabel) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 527 subscribers, ranking 4 368 in the Religion & Spirituality category and 1 829 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 527 subscribers.

According to the latest data from 27 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -16 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 38.77%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 11.90% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 7 184 views. Within the first day, a publication typically gains 2 205 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 238.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?ig...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

18 527
Subscribers
-224 hours
-177 days
-1630 days
Posts Archive
በእኛ ላይ ሊደርሱ ካሉ ክፉ አደጋዎች የዳንባቸውን ጊዜያቶች እስኪ እናስተውል። ከእነዚያ አስከፊ ሁኔታዎች ተአምር በሚመስል መንገድ የተረፍንባቸውንና ‹ለጥቂት እኮ ነው…› እያልን የምናስታውሳቸውን ሰ
በእኛ ላይ ሊደርሱ ካሉ ክፉ አደጋዎች የዳንባቸውን ጊዜያቶች እስኪ እናስተውል። ከእነዚያ አስከፊ ሁኔታዎች ተአምር በሚመስል መንገድ የተረፍንባቸውንና ‹ለጥቂት እኮ ነው…› እያልን የምናስታውሳቸውን ሰዓታት እስኪ ለአፍታ ደግመን እናስባቸው። በእነዚያ የጭንቅ ጊዜያቶች ሁሉ የታደገንን የጠባቂ መልአካችንን የተዘረጋች ክንድ እናያለን፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙር የነበረው ቅዱስ ፖሊካርፐስ በጠባቂ መልአኩ አማካኝነት እንዴት ከሞት በተአምር ሊተርፍ እንደ ቻለ ይናገራል፡፡ ቅዱሱ አብሮት በአገልግሎት ከሚረዳው ዲያቆን ጋር በጉዞ ሳሉ ቀኑ ስለመሸባቸው መንገድ ዳር ካለ አንድ ትንሽ ቤት ገብተው ይተኛሉ፡፡ በእኩለ ሌሊትም የፖሊካርፐስ ጠባቂ መልአክ በሕልሙ ተገልጦ ‹ፖሊካርፐስ ሆይ ሊፈርስ ነውና ፈጥነህ ይህንን ቤት ለቅቀህ ውጣ› እያለ ሶስት ጊዜ አስጠነቀቀው፡፡ ፖሊካርፐስ ራእዩን እንዳየ ያንን ቤት ለቆ በፍጥነት ወጣ፡፡ ወዲያውም ቤቱን እያየው በፊቱ ፈራርሶ ወደቀ፡፡ እርሱም ሊመጣበት ከነበረው ሞት በጠባቂ መልአኩ አማካኝነት ዳነ፡፡ እንኳን ለጠባቂያችን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንልን! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com

የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እና ሥርዓት እንዴት አሁን ያለበትን ዓይነት ቅርጽ ሊይዝ ቻለ? በዚህ ሂደት ውስጥስ በቤተ ክርስቲያን የተካሄዱ ዓለማቀፉዊ ጉባኤያት (Ecumenical Councils) ድርሻቸው ምን ነበር? ይህን አጠር ባለ መንገድ ለመረዳት “ጉባኤ ኒቅያ” የተሰኘውን ሦስት ክፍሎች ያሉትን ተከታታይ ትምህርት ከማስታወሻ ጋር እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ። https://youtu.be/Epd_EC5diLI?si=JlViJ7yVxsPkpyHA

የልደት ቀኔን አስመልክቶ በጎ ምኞታችሁን እና ምርቃቶቻችሁን እንደ ወንዝ ላፈሰሳችሁልኝ ሁሉ፣ እግዚአብሔር እንደ ወንዝ የሚፈስ ሰላሙን ይስጣችሁ። አምላከ ጳውሎስ ያክብርልኝ!
+1
የልደት ቀኔን አስመልክቶ በጎ ምኞታችሁን እና ምርቃቶቻችሁን እንደ ወንዝ ላፈሰሳችሁልኝ ሁሉ፣ እግዚአብሔር እንደ ወንዝ የሚፈስ ሰላሙን ይስጣችሁ። አምላከ ጳውሎስ ያክብርልኝ!

ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስ
ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስት ሰዓት) መንገድ ላይ የሚገኝ ሰው ወይ ምንም ማረፊያ የሌለው ምስኪን ነው፣ አለዚያ ደግሞ እንደዚያች ሳምራዊት ሴት ከሰው የተገለለ ብቸኛ ነው።(ዮሐ 4፥6) አብርሃም ድንኳኑን ያሰናዳው ያማረ ለለበሱ፣ ብድር ለሚመልሱ፣ በመልክም በገንዘብም ዓይን ውስጥ ለሚገቡ ሰዎች ሳይሆን፣ ሰው ለሸሻቸው መጠጊያ ለሌላቸው እና በፀሐይ ንዳድ እየተንገበገቡ ማረፊያ ፈልገው ለሚዞሩ አስታዋሽ አልባ ምስኪኖች ነበር። አብርሃም በደጁ የሚያልፉ ምስኪን እንግዶቹን “ና እስኪ” ብሎ በማቃለል ቃል አይጠራቸውም። እየሮጠ ወደ እነርሱ ሄዶ “ጌቶች (እመቤት) እባካችሁ ወደ ቤቴ ግቡልኝ” ብሎ በትሕትና ይለምናቸዋል እንጂ። ይህንን ግን በምን አወቅን? በሦስት ሰዎች ተመስለው ወደ ቤቱ ቅድስት ሥላሴ በመጡ ጊዜ አብርሃም እነርሱን ያስተናገደበትን መንገድ አይተን ተረዳን። አብርሃም በዚህች ቀን ተዘጋጅቶ ይጠብቅ የነበረው ሰውን እንጂ እግዚአብሔርን አልነበረም። እግዚአብሔር ግን አብርሃም ለምስኪናኑ ያሳይ የነበረው ቸርነቱን አይቶ በቤቱ ሊስተናገድ ወደደ። አብርሃም ለድሆች ሲል በከፈተው በር በኩል በመካንነት ምክንያት የተዘጋውን የሣራን ማኅፀን የሚከፍት የሠራዊት ጌታ ገባለት። የአንተን የብዙ ዓመታት ጥያቄ ለመመለስ እግዚአብሔር ወደ ሕይወትህ የሚገባው፣ ለሌሎች ሰዎች ብለህ በከፈትኸው የመልካምነት እና የቅንነት በር በኩል ነው። ዲያቆን አቤል ካሳሁን ሐምሌ ቅድስት ሥላሴ -2017 ዓ.ም. https://t.me/Dnabel እንኳን አደረሳችሁ!

“ቅዱሱ በሰይፍ ወደሚቀላበት አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሞት ጥላ ዙሪያውን ቢከበውም ‹‹የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል›› ብሎ የተነገረውን የጌታን ቃል አምኖ የልብሱን ኮሌታ ከፍ በማድረግ አን
“ቅዱሱ በሰይፍ ወደሚቀላበት አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሞት ጥላ ዙሪያውን ቢከበውም ‹‹የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል›› ብሎ የተነገረውን የጌታን ቃል አምኖ የልብሱን ኮሌታ ከፍ በማድረግ አንገቱን ለሰያፊው አመቻቸ፡፡(ዮሐ 11:25) ወታደሩም በያዘው ሰይፍ የጳውሎስን አንገት ከሰውነቱ ለየው፡፡ በቃሉ ትምህርት ምድርን ወደ ገነት የቀየረው፣ የብዙዎችን ስብራት የጠገነው፣ ሙት ያስነሣው፣ ሽባ የተረተረው የጳውሎስ አፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ታተመ፡፡ ይህ እንኳን ሰውን ሰማይና ምድርንም የሚያስደነግጥ ክስተት ነው፡፡ ለዚህም ነው ሊቁ በመልክእ ነገሩን ሲያደንቅ ‹‹ጳውልስ ወጴጥሮስ አመ አፉክሙ ተኀትመ፣ ዘበሰማያት ወዘበምድር እስከ ንፍቀ ሰዓት አርመመ ››/‹‹ጳውሎስ እና ጴጥሮስ ሆይ፣ አንደበታችሁ በተዘጋ ጊዜ፤ በሰማይም በምድርም እስከ ግማሽ ሰዓት ዝምታ ሆነ ›› የሚለው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕትነትን በሚቀበልበት ጊዜ በቦታው ላይ የነበሩ የዓይን ምስክሮች እንዳሉት ሞቱም በተአምራት የተከበበ ነበር፡፡ እነዚህም ሰዎች በሰይፍ ከተቆረጠው ከቅዱሱ አንገት ደም እና ውኃ ፈልቋል ያሉ ሲሆን፣ አንዳንዶች ደግሞ ራሱ ሦስት ጊዜ ወደ መሬት እንደ ነጠረችና በእነዚያም ቦታዎች ላይ ውኃ (ጠበል) መፍለቁን ተናግረዋል፡፡” ቅዱስ ጳውሎስ፣ ገጽ፡ 410 ቅዱሱ ሰማዕት ጳውሎስ ሆይ፣ እንደ ኤፌሶን ሽማግሎች ስለ ክርስቶስ የተሰየፈች አንገትህን አንድ ጊዜ አቅፈን እንስመው ዘንድ ብታድለን ምን ነበር?! #ኃምሌ 5 ሮም አደባባይ ላይ!

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!

በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋዛችሁ? ይ
በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋዛችሁ? ይኸው “ራእየ ኒፎን” በቀሲስ ታምራት ውቤ። ቀሲስ ታምራ ውቤ ይህን ድንቅ መጽሐፍ በመተርጎማቸው፣ ቅድስና ርቆ እንደ ተሰቀለ ውብ ፍሬ እያጓጓ የማይደረስበት ለሚመስለን ለዛሬ ክርስቲያኖች፣ ዛፉን ዘንበል አድርጎ ፍሬውን የማቅረብ ያህል ነው ድርሻቸውን ተወጥተዋል። ደግሞ የአተረጓጎም ለዛው፣ እና የቋንቋው ውበት ደግሞ አስደናቂ ነው። አንዴ ካነሡት አስቀምጡኝ አይልም። የነገ ሰንበት ሐምሌ 5 - 8:00 ሰዓት ቀጠሯችሁ “ከቅዱስ ኒፎን” ጋር ካልሆነ በቀር ሌላ ከማንም ጋር አይሁን። ቀሲስ ታምራት ውቤ ጥሩ ነፍስ የሚያጠግብ ድግስ ደግሰው እየጠሩን ነው። ብንገኝ ብዙ እናተርፋለን። ቦታ: ቦሌ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ትልቁ አዳራሽ

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ

ለቅዱሳን ቤተሰቦቹ የጸሎት መልስ የሆነው፣ ለዚህች ዓለም የሚነድና የሚያበራ መብራት የነበረው፣ የሥጋን ጣዕም ያልቀመሰው ፍጹም ተሐራሚ፣ ተፈጥሮው የሰው ኑሮው የመልአክ የነበረው፣ ዕረፍትን የማያውቅ የበረሃው ሰው የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደቱ ዛሬ ይታሰባል። ቅዱሱ ሰማዕት እንደ ኖኅ ጻድቅ የነበረ፣ እንደ አብርሃም በእግዚአብሔር የተወደደ፣ እንደ ዮሴፍ የታሰረ፣ እንደ አቤል በአመጻ የተገደለ፣ እንደ ሄኖክ አካሄዱን ከአምላኩ ጋር ያደረገ ነው። በመንፈስ ቅዱስ አሳዳጊነት በመላእክት አገልግሎት በበረሃ ያደገው ዮሐንስ ክብሩ እንዴት ያለ ነው? እርሱ እንደ ሕፃናት ባለቀሰ ጊዜ የሚያባብለው ሰው አልነበረም። “አይዞህ ልጄ” እያለች የምታጽናናው እናቱም ገና በልጅነቱ ተለይታዋለች። ነገር ግን እግዚአብሔር ብቻውን በበረሃ አልተወውም። አጥንት በሚያለመልም የመላእክት ምስጋና አረጋጋው። በልዩ ጥበቡም አሳድጎ በመንፈስ እንዲጠነክር አደረገው። የእግዚአብሔር አብን ልጅ ዮሴፍ በናዝሬት (የሰው ልጅ) እንዳሳደገ፣ የዘካርያስን (ለሰውን) ልጅ ዮሐንስን እግዚአብሔር በበረሃ አሳደገ። እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን! ዲያቆን አቤል ካሣሁን የመጥምቀ መለኰት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ

ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል። ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com https://t.me/Dnabel

ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!! "ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡
ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!! "ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡ በዕለተ ዓርብ ከልጅሽ ቀኝ በፈሰሰው ውኃ ተጠምቃ የውግታቱን ደም ተቀብታ ቅድስት ቤተክርስቲያን ታመሰግንሻለች። የልዑል እግዚአብሔር በግ የተባለ ልጅሽ አማኑኤል የተሞሸረባት መርዓዊ ሰማያዊ የተባለባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንኳን እመቤታችን ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com https://t.me/Dnabel

የቅዱስ ጳውሎስ ልብስ! በዚህ የሐዋርያት ጾም ሐዋርያው ጳውሎስን እንዴት እያነበባችሁ ነው?
+1
የቅዱስ ጳውሎስ ልብስ! በዚህ የሐዋርያት ጾም ሐዋርያው ጳውሎስን እንዴት እያነበባችሁ ነው?

እንደ እድል ሆኖ ያደግኹት በመልአኩ ቤት ነው። ስለ እርሱ በቃል የማይገለጽ ልዩ ፍቅር አለኝ። በሄድኩበት ሁሉ ስሙ ሲጠራ ከሰማኹ አንዳች የደስታ ስሜት ሰውነቴን ውርር ያደርገዋል። "ሚካኤል" ብዬ ያ
እንደ እድል ሆኖ ያደግኹት በመልአኩ ቤት ነው። ስለ እርሱ በቃል የማይገለጽ ልዩ ፍቅር አለኝ። በሄድኩበት ሁሉ ስሙ ሲጠራ ከሰማኹ አንዳች የደስታ ስሜት ሰውነቴን ውርር ያደርገዋል። "ሚካኤል" ብዬ ያልቀለለ ሸክም፣ ያልተመለሰ ጸሎት የለኝም። አንዳንዴ መልአኩ በጣም ቅርቤ ይመስለኛል። ደግሞ ስለ እርሱ ሳስብ ያሳዝነኛል። ለምን? እንጃ ግን ለእኔ ስለሚያዝንልኝ ይሆናል። ስለ እኔ የሚጨነቅ፣ የሚሳሳልኝ ይመስለኛል። ስለዚህ ያሳዝነኛል። ሚካኤል የዋህ፣ ትሑት፣ ሰውን ወዳጅ መልአክ ነው። ሁልጊዜ ሲዘመር ደስ የሚለኝ መዝሙር አለ:- ነዋ ሚካኤል መልአከክሙ          ይስአል ለክሙ በእንተ ምሕረት ትርጉም:- "እነሆ ሚካኤል መልአካችሁ ምሕረትን ይለምንላችሁ" ሚካኤል መልአኬ፣ ሚካኤል መልአካችን! ከታናሽነቴ ጀምሮ እኔን የመገበኝ፣ ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com ፎቶ: ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል መግቢያ

ቤትህ ውስጥ ከፍተህ የረሳኸው ባንቧ ቢኖርና ድንገት ሌሊት ከእንቅልፍህ ስትነቃ መሬቱ እንዳለ በውኃ ተጥለቅልቆ ብታገኝ በቅድሚያ ምን ታደርጋለህ? የፈሰሰውን ውኃ ለመጥረግ ወይስ የሚፈሰውን ቧንቧ ለመዝጋት ነው የምትቸኩለው? ቧንቧውን ሳትዘጋ መሬት ላይ ያለውን ውኃ ለማፈስ ብትሞክር ትርፉ ድካም ነው። ቀኑን ሙሉ ስትዝቅ ብትውል ቤትህ የሞላውን ውኃ አታጎድልም። እናስ? ቧንቧውን ዝጋዋ! በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ መፍትሔ በማታገኝበት ነገር ላይ ጊዜህን አታባክን። ለዚህ የሚዳርገኝ መነሻው ምክንያት ምንድን ነው? ብለህ ራስህን ጠይቅ። አእምሮህ ውስጥ የሞሉትን ክፋቶች ከመቁጠር በላይ እነዚያ ክፋቶች የገቡበትን አንድ ቀዳዳ ወይም ሽንቁር ለማወቅ ጣር። እርሱን ያወቅኸው ቀን ለችግርህ ትልቁን መፍትሔ አብረህ ታገኛለህ። ያን ቀዳዳ ከዘጋህ ወይም ምንጩን ካደረቅኸው የቀረው ቀስ እያለ ተኖ መጥፋቱ አይቀርም። ከመውደቅህ በላይ የውድቀትህ ምክንያት ያስጨንቅህ። ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com