ch
Feedback
Dn Abel Kassahun Mekuria

Dn Abel Kassahun Mekuria

前往频道在 Telegram

ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW

显示更多

📈 Telegram 频道 Dn Abel Kassahun Mekuria 的分析概览

频道 Dn Abel Kassahun Mekuria (@dnabel) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 527 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 4 368,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 829

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 527 名订阅者。

根据 27 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -16,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.77%。内容发布后 24 小时内通常能获得 11.90% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 7 184 次浏览,首日通常累积 2 205 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 238

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው። ይወዳጁን ለፌስቡክ ገጽ https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL ለyoutube https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_ ለInstagram https://www.instagram.com/abelkassahunm?ig...

凭借高频更新(最新数据采集于 28 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

18 527
订阅者
-224 小时
-177
-1630
帖子存档
በእኛ ላይ ሊደርሱ ካሉ ክፉ አደጋዎች የዳንባቸውን ጊዜያቶች እስኪ እናስተውል። ከእነዚያ አስከፊ ሁኔታዎች ተአምር በሚመስል መንገድ የተረፍንባቸውንና ‹ለጥቂት እኮ ነው…› እያልን የምናስታውሳቸውን ሰ
በእኛ ላይ ሊደርሱ ካሉ ክፉ አደጋዎች የዳንባቸውን ጊዜያቶች እስኪ እናስተውል። ከእነዚያ አስከፊ ሁኔታዎች ተአምር በሚመስል መንገድ የተረፍንባቸውንና ‹ለጥቂት እኮ ነው…› እያልን የምናስታውሳቸውን ሰዓታት እስኪ ለአፍታ ደግመን እናስባቸው። በእነዚያ የጭንቅ ጊዜያቶች ሁሉ የታደገንን የጠባቂ መልአካችንን የተዘረጋች ክንድ እናያለን፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙር የነበረው ቅዱስ ፖሊካርፐስ በጠባቂ መልአኩ አማካኝነት እንዴት ከሞት በተአምር ሊተርፍ እንደ ቻለ ይናገራል፡፡ ቅዱሱ አብሮት በአገልግሎት ከሚረዳው ዲያቆን ጋር በጉዞ ሳሉ ቀኑ ስለመሸባቸው መንገድ ዳር ካለ አንድ ትንሽ ቤት ገብተው ይተኛሉ፡፡ በእኩለ ሌሊትም የፖሊካርፐስ ጠባቂ መልአክ በሕልሙ ተገልጦ ‹ፖሊካርፐስ ሆይ ሊፈርስ ነውና ፈጥነህ ይህንን ቤት ለቅቀህ ውጣ› እያለ ሶስት ጊዜ አስጠነቀቀው፡፡ ፖሊካርፐስ ራእዩን እንዳየ ያንን ቤት ለቆ በፍጥነት ወጣ፡፡ ወዲያውም ቤቱን እያየው በፊቱ ፈራርሶ ወደቀ፡፡ እርሱም ሊመጣበት ከነበረው ሞት በጠባቂ መልአኩ አማካኝነት ዳነ፡፡ እንኳን ለጠባቂያችን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን! መልካም በዓል ይሁንልን! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com

የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እና ሥርዓት እንዴት አሁን ያለበትን ዓይነት ቅርጽ ሊይዝ ቻለ? በዚህ ሂደት ውስጥስ በቤተ ክርስቲያን የተካሄዱ ዓለማቀፉዊ ጉባኤያት (Ecumenical Councils) ድርሻቸው ምን ነበር? ይህን አጠር ባለ መንገድ ለመረዳት “ጉባኤ ኒቅያ” የተሰኘውን ሦስት ክፍሎች ያሉትን ተከታታይ ትምህርት ከማስታወሻ ጋር እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ። https://youtu.be/Epd_EC5diLI?si=JlViJ7yVxsPkpyHA

የልደት ቀኔን አስመልክቶ በጎ ምኞታችሁን እና ምርቃቶቻችሁን እንደ ወንዝ ላፈሰሳችሁልኝ ሁሉ፣ እግዚአብሔር እንደ ወንዝ የሚፈስ ሰላሙን ይስጣችሁ። አምላከ ጳውሎስ ያክብርልኝ!
+1
የልደት ቀኔን አስመልክቶ በጎ ምኞታችሁን እና ምርቃቶቻችሁን እንደ ወንዝ ላፈሰሳችሁልኝ ሁሉ፣ እግዚአብሔር እንደ ወንዝ የሚፈስ ሰላሙን ይስጣችሁ። አምላከ ጳውሎስ ያክብርልኝ!

ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስ
ፀሐይ ናላ በምታዞርበት እና ሁሉም ለማረፍ ወደ አልጋው በሚሽቀዳደምበት በቀትር ሰዓት አብርሃም ግን በድንኳኑ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ እንግዳ በተስፋ ይጠባበቅ ነበር።(ዘፍ 18) በዚህ የቃጠሎ ጊዜ (ስድስት ሰዓት) መንገድ ላይ የሚገኝ ሰው ወይ ምንም ማረፊያ የሌለው ምስኪን ነው፣ አለዚያ ደግሞ እንደዚያች ሳምራዊት ሴት ከሰው የተገለለ ብቸኛ ነው።(ዮሐ 4፥6) አብርሃም ድንኳኑን ያሰናዳው ያማረ ለለበሱ፣ ብድር ለሚመልሱ፣ በመልክም በገንዘብም ዓይን ውስጥ ለሚገቡ ሰዎች ሳይሆን፣ ሰው ለሸሻቸው መጠጊያ ለሌላቸው እና በፀሐይ ንዳድ እየተንገበገቡ ማረፊያ ፈልገው ለሚዞሩ አስታዋሽ አልባ ምስኪኖች ነበር። አብርሃም በደጁ የሚያልፉ ምስኪን እንግዶቹን “ና እስኪ” ብሎ በማቃለል ቃል አይጠራቸውም። እየሮጠ ወደ እነርሱ ሄዶ “ጌቶች (እመቤት) እባካችሁ ወደ ቤቴ ግቡልኝ” ብሎ በትሕትና ይለምናቸዋል እንጂ። ይህንን ግን በምን አወቅን? በሦስት ሰዎች ተመስለው ወደ ቤቱ ቅድስት ሥላሴ በመጡ ጊዜ አብርሃም እነርሱን ያስተናገደበትን መንገድ አይተን ተረዳን። አብርሃም በዚህች ቀን ተዘጋጅቶ ይጠብቅ የነበረው ሰውን እንጂ እግዚአብሔርን አልነበረም። እግዚአብሔር ግን አብርሃም ለምስኪናኑ ያሳይ የነበረው ቸርነቱን አይቶ በቤቱ ሊስተናገድ ወደደ። አብርሃም ለድሆች ሲል በከፈተው በር በኩል በመካንነት ምክንያት የተዘጋውን የሣራን ማኅፀን የሚከፍት የሠራዊት ጌታ ገባለት። የአንተን የብዙ ዓመታት ጥያቄ ለመመለስ እግዚአብሔር ወደ ሕይወትህ የሚገባው፣ ለሌሎች ሰዎች ብለህ በከፈትኸው የመልካምነት እና የቅንነት በር በኩል ነው። ዲያቆን አቤል ካሳሁን ሐምሌ ቅድስት ሥላሴ -2017 ዓ.ም. https://t.me/Dnabel እንኳን አደረሳችሁ!

“ቅዱሱ በሰይፍ ወደሚቀላበት አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሞት ጥላ ዙሪያውን ቢከበውም ‹‹የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል›› ብሎ የተነገረውን የጌታን ቃል አምኖ የልብሱን ኮሌታ ከፍ በማድረግ አን
“ቅዱሱ በሰይፍ ወደሚቀላበት አደባባይ ከደረሰ በኋላ የሞት ጥላ ዙሪያውን ቢከበውም ‹‹የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል›› ብሎ የተነገረውን የጌታን ቃል አምኖ የልብሱን ኮሌታ ከፍ በማድረግ አንገቱን ለሰያፊው አመቻቸ፡፡(ዮሐ 11:25) ወታደሩም በያዘው ሰይፍ የጳውሎስን አንገት ከሰውነቱ ለየው፡፡ በቃሉ ትምህርት ምድርን ወደ ገነት የቀየረው፣ የብዙዎችን ስብራት የጠገነው፣ ሙት ያስነሣው፣ ሽባ የተረተረው የጳውሎስ አፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ታተመ፡፡ ይህ እንኳን ሰውን ሰማይና ምድርንም የሚያስደነግጥ ክስተት ነው፡፡ ለዚህም ነው ሊቁ በመልክእ ነገሩን ሲያደንቅ ‹‹ጳውልስ ወጴጥሮስ አመ አፉክሙ ተኀትመ፣ ዘበሰማያት ወዘበምድር እስከ ንፍቀ ሰዓት አርመመ ››/‹‹ጳውሎስ እና ጴጥሮስ ሆይ፣ አንደበታችሁ በተዘጋ ጊዜ፤ በሰማይም በምድርም እስከ ግማሽ ሰዓት ዝምታ ሆነ ›› የሚለው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕትነትን በሚቀበልበት ጊዜ በቦታው ላይ የነበሩ የዓይን ምስክሮች እንዳሉት ሞቱም በተአምራት የተከበበ ነበር፡፡ እነዚህም ሰዎች በሰይፍ ከተቆረጠው ከቅዱሱ አንገት ደም እና ውኃ ፈልቋል ያሉ ሲሆን፣ አንዳንዶች ደግሞ ራሱ ሦስት ጊዜ ወደ መሬት እንደ ነጠረችና በእነዚያም ቦታዎች ላይ ውኃ (ጠበል) መፍለቁን ተናግረዋል፡፡” ቅዱስ ጳውሎስ፣ ገጽ፡ 410 ቅዱሱ ሰማዕት ጳውሎስ ሆይ፣ እንደ ኤፌሶን ሽማግሎች ስለ ክርስቶስ የተሰየፈች አንገትህን አንድ ጊዜ አቅፈን እንስመው ዘንድ ብታድለን ምን ነበር?! #ኃምሌ 5 ሮም አደባባይ ላይ!

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!

በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋዛችሁ? ይ
በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋዛችሁ? ይኸው “ራእየ ኒፎን” በቀሲስ ታምራት ውቤ። ቀሲስ ታምራ ውቤ ይህን ድንቅ መጽሐፍ በመተርጎማቸው፣ ቅድስና ርቆ እንደ ተሰቀለ ውብ ፍሬ እያጓጓ የማይደረስበት ለሚመስለን ለዛሬ ክርስቲያኖች፣ ዛፉን ዘንበል አድርጎ ፍሬውን የማቅረብ ያህል ነው ድርሻቸውን ተወጥተዋል። ደግሞ የአተረጓጎም ለዛው፣ እና የቋንቋው ውበት ደግሞ አስደናቂ ነው። አንዴ ካነሡት አስቀምጡኝ አይልም። የነገ ሰንበት ሐምሌ 5 - 8:00 ሰዓት ቀጠሯችሁ “ከቅዱስ ኒፎን” ጋር ካልሆነ በቀር ሌላ ከማንም ጋር አይሁን። ቀሲስ ታምራት ውቤ ጥሩ ነፍስ የሚያጠግብ ድግስ ደግሰው እየጠሩን ነው። ብንገኝ ብዙ እናተርፋለን። ቦታ: ቦሌ መድኃኔዓለም ቤ/ክ ትልቁ አዳራሽ

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ!

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ

ለቅዱሳን ቤተሰቦቹ የጸሎት መልስ የሆነው፣ ለዚህች ዓለም የሚነድና የሚያበራ መብራት የነበረው፣ የሥጋን ጣዕም ያልቀመሰው ፍጹም ተሐራሚ፣ ተፈጥሮው የሰው ኑሮው የመልአክ የነበረው፣ ዕረፍትን የማያውቅ የበረሃው ሰው የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ልደቱ ዛሬ ይታሰባል። ቅዱሱ ሰማዕት እንደ ኖኅ ጻድቅ የነበረ፣ እንደ አብርሃም በእግዚአብሔር የተወደደ፣ እንደ ዮሴፍ የታሰረ፣ እንደ አቤል በአመጻ የተገደለ፣ እንደ ሄኖክ አካሄዱን ከአምላኩ ጋር ያደረገ ነው። በመንፈስ ቅዱስ አሳዳጊነት በመላእክት አገልግሎት በበረሃ ያደገው ዮሐንስ ክብሩ እንዴት ያለ ነው? እርሱ እንደ ሕፃናት ባለቀሰ ጊዜ የሚያባብለው ሰው አልነበረም። “አይዞህ ልጄ” እያለች የምታጽናናው እናቱም ገና በልጅነቱ ተለይታዋለች። ነገር ግን እግዚአብሔር ብቻውን በበረሃ አልተወውም። አጥንት በሚያለመልም የመላእክት ምስጋና አረጋጋው። በልዩ ጥበቡም አሳድጎ በመንፈስ እንዲጠነክር አደረገው። የእግዚአብሔር አብን ልጅ ዮሴፍ በናዝሬት (የሰው ልጅ) እንዳሳደገ፣ የዘካርያስን (ለሰውን) ልጅ ዮሐንስን እግዚአብሔር በበረሃ አሳደገ። እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን! ዲያቆን አቤል ካሣሁን የመጥምቀ መለኰት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል

#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ
#ጉዞ ወደ ሮም አደባባይ

ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል። ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com https://t.me/Dnabel

ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!! "ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡
ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች!!! "ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው፡፡ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ መውጣት ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች፡፡ በዕለተ ዓርብ ከልጅሽ ቀኝ በፈሰሰው ውኃ ተጠምቃ የውግታቱን ደም ተቀብታ ቅድስት ቤተክርስቲያን ታመሰግንሻለች። የልዑል እግዚአብሔር በግ የተባለ ልጅሽ አማኑኤል የተሞሸረባት መርዓዊ ሰማያዊ የተባለባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታመሰግንሻለች" አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንኳን እመቤታችን ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com https://t.me/Dnabel

የቅዱስ ጳውሎስ ልብስ! በዚህ የሐዋርያት ጾም ሐዋርያው ጳውሎስን እንዴት እያነበባችሁ ነው?
+1
የቅዱስ ጳውሎስ ልብስ! በዚህ የሐዋርያት ጾም ሐዋርያው ጳውሎስን እንዴት እያነበባችሁ ነው?

እንደ እድል ሆኖ ያደግኹት በመልአኩ ቤት ነው። ስለ እርሱ በቃል የማይገለጽ ልዩ ፍቅር አለኝ። በሄድኩበት ሁሉ ስሙ ሲጠራ ከሰማኹ አንዳች የደስታ ስሜት ሰውነቴን ውርር ያደርገዋል። "ሚካኤል" ብዬ ያ
እንደ እድል ሆኖ ያደግኹት በመልአኩ ቤት ነው። ስለ እርሱ በቃል የማይገለጽ ልዩ ፍቅር አለኝ። በሄድኩበት ሁሉ ስሙ ሲጠራ ከሰማኹ አንዳች የደስታ ስሜት ሰውነቴን ውርር ያደርገዋል። "ሚካኤል" ብዬ ያልቀለለ ሸክም፣ ያልተመለሰ ጸሎት የለኝም። አንዳንዴ መልአኩ በጣም ቅርቤ ይመስለኛል። ደግሞ ስለ እርሱ ሳስብ ያሳዝነኛል። ለምን? እንጃ ግን ለእኔ ስለሚያዝንልኝ ይሆናል። ስለ እኔ የሚጨነቅ፣ የሚሳሳልኝ ይመስለኛል። ስለዚህ ያሳዝነኛል። ሚካኤል የዋህ፣ ትሑት፣ ሰውን ወዳጅ መልአክ ነው። ሁልጊዜ ሲዘመር ደስ የሚለኝ መዝሙር አለ:- ነዋ ሚካኤል መልአከክሙ          ይስአል ለክሙ በእንተ ምሕረት ትርጉም:- "እነሆ ሚካኤል መልአካችሁ ምሕረትን ይለምንላችሁ" ሚካኤል መልአኬ፣ ሚካኤል መልአካችን! ከታናሽነቴ ጀምሮ እኔን የመገበኝ፣ ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው! ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com ፎቶ: ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል መግቢያ

ቤትህ ውስጥ ከፍተህ የረሳኸው ባንቧ ቢኖርና ድንገት ሌሊት ከእንቅልፍህ ስትነቃ መሬቱ እንዳለ በውኃ ተጥለቅልቆ ብታገኝ በቅድሚያ ምን ታደርጋለህ? የፈሰሰውን ውኃ ለመጥረግ ወይስ የሚፈሰውን ቧንቧ ለመዝጋት ነው የምትቸኩለው? ቧንቧውን ሳትዘጋ መሬት ላይ ያለውን ውኃ ለማፈስ ብትሞክር ትርፉ ድካም ነው። ቀኑን ሙሉ ስትዝቅ ብትውል ቤትህ የሞላውን ውኃ አታጎድልም። እናስ? ቧንቧውን ዝጋዋ! በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ መፍትሔ በማታገኝበት ነገር ላይ ጊዜህን አታባክን። ለዚህ የሚዳርገኝ መነሻው ምክንያት ምንድን ነው? ብለህ ራስህን ጠይቅ። አእምሮህ ውስጥ የሞሉትን ክፋቶች ከመቁጠር በላይ እነዚያ ክፋቶች የገቡበትን አንድ ቀዳዳ ወይም ሽንቁር ለማወቅ ጣር። እርሱን ያወቅኸው ቀን ለችግርህ ትልቁን መፍትሔ አብረህ ታገኛለህ። ያን ቀዳዳ ከዘጋህ ወይም ምንጩን ካደረቅኸው የቀረው ቀስ እያለ ተኖ መጥፋቱ አይቀርም። ከመውደቅህ በላይ የውድቀትህ ምክንያት ያስጨንቅህ። ዲያቆን አቤል ካሳሁን abelzebahiran@gmail.com