en
Feedback
ዳዕዋ በወልቂጤ

ዳዕዋ በወልቂጤ

Open in Telegram

✅የሰለፎች ሚዲያ

Show more
1 201
Subscribers
No data24 hours
-37 days
-1530 days
Posts Archive
photo content

"ወሃ . ብዮች ወሊዮችን አይወዱም" እያሉ የሚከሱ ሰዎች አሉ። ያው እነማን ይህን እንደሚሉ ይታወቃል። እውነት ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ረሒመሁላህ ወሊዮችን ይጠሉ ነበር? አስተምህሯቸውስ ለወሊዮች ጥላቻን የደቀነ ነው? { أَلَاۤ إِنَّ أَوۡلِیَاۤءَ ٱللَّهِ لَا خَوۡفٌ عَلَیۡهِمۡ وَلَا هُمۡ یَحۡزَنُونَ (62) ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ وَكَانُوا۟ یَتَّقُونَ (63) } "ንቁ! የአላህ ወዳጆች በእነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም። (እነሱም) እነዚያ ያመኑትና ይፈሩት የነበሩ ናቸው።" [ዩኑስ፡ 62-63] እነዚህን አንቀፆች ያላግባብ ስለሚመነዝሩ ሰዎች ሲያነሱ ሸይኹ እንዲህ ይላሉ፦ "ይሄ ሐቅ ነው። ነገር ግን አይመለኩም። እኛ መመለካቸውንና ከአላህ ጋር መጋራታቸውን እንጂ ሌላ አንቃወምም። እንጂ እነሱን መውደድ፣ መከተል እና ከራማዎቻቸውን ማመን ባንተ ላይ ግዴታ ነው። የወሊዮችን ከራማዎች የቢድዐ እና የጥመት ሰዎች እንጂ አይክዱም። የአላህ ዲን በሁለት ጫፎች መሀል የሚገኝ ልከኛ መንገድ፣ በሁለት ጥመቶች መሀል ያለ ቅናቻ፣ በሁለት ሃሰቶች መሃል ያለ እውነት ነው።" [ከሽፉ ሹቡሃት] = ተመልከቱ እንግዲህ ወሊዮችን መውደድ ዋጂብ ነው እያሉ ነው ሸይኹ። ልዩነቱ ያለው በመውደድ አመሃኝቶ የአላህን ሐቅ ለነሱ መስጠት አይገባም የሚለው ላይ ነው። ደግሞም ወሊይ ማለት በአንቀጿ መሰረት በአላህ ያመነና እሱን የሚፈራ ሁሉ ነው። ሌላ መስፈርት የለውም። ስለዚህ አማኞች ሁሉ የአላህ ወሊዮች ናቸው። ወልይነት በዘር የሚተላለፍ ንግስና አይደለም። የወልይነት ትርጓሜ ውስጥ ጋርዶ መቀመጥ፣ ትንቢት መናገር፣ የሩቅ ማወቅ፣ ከራማ ማሳየት፣ . . . የሚባል መስፈርት የለም። ጠንቋዮች ደግሞ የአላህ ሳይሆን የሸይጧን ወሊዮች ናቸው። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor

ማነው እውነተኛው አዛኝ? ~ ዛሬም በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ወገናችን በሺርክ ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ነው። ሙታኖችን የሚማፀን፣ ጠንቋይ ጋር የሚመላለስ፣ ዛፍና ድንጋይ የሚያመልክ ብዙ ነው። ይህንን እውነታ ለመቀየር የረባ ድርሻ የሌላቸው፣ እንዲያውም በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ያለው የሺርክ ወረራ ባለበት እንዲቀጥል ሽፋን የሚሰጡ አካላት ህዝባችንን ከዚህ ከባድ ጥፋት ለማትረፍ ደፋ ቀና የሚሉት ዱዓቶችን "እዝነት የላቸውም" እያሉ ሲከሱ ማየት የዘመኑ ትልቅ ስላቅ ነው። እና ህዝብን ወደ ሺርክ እየነዱ ያሉ አካላት ናቸው ተቆርቋሪዎቹ? እና በሺርክ መንዙማ ህዝብን እየበከሉ ያሉት ናቸው አዛኛቹ? ነው ወይስ እንዲህ አይነት የጥፋት ማሽኖችን እያወደሱ በወገን ኣኺራ ላይ ቁማር የሚጫወቱት ናቸው አዛኞቹ? ነው ወይስ ገና በህይወት እያሉ እየተመለኩ፣ እየተማለባቸው፣ ለጭንቅ ለችግር እየተማፀኗቸው እያወቁ ዝም የሚሉ ጣኦቶች ናቸው ለህዝብ የሚያዝኑት? ነው ወይስ ለተውሒድ ደዕዋ እንቅፋት ከመሆን ውጭ የረባ ህዝባዊ ሚና የሌላቸው ናቸው እውነተኛው የህዝብ ተቆርቋሪዎች? ሺርክ አላህ ፈፅሞ የማይምረው፣ መልካም ስራዎችን የሚደመስስ፣ ለዘላለማዊ እሳት የሚዳርግ አደገኛ ጥፋት ነው። ነብያት የተላኩት፣ መፃህፍት የወረዱት፣ ሺርክን ለመጋፈጥ፣ ተውሒድን ለማንገስ ነው። ከኔና ካንተ በላይ ነብዩ ﷺ ለህዝብ አዛኝና ተቆርቋሪ ነበሩ። ያለ ስማቸው፣ ያለ ግብራቸው ጠንቋይ፣ ደጋሚ፣ እብ ድ የተባሉት ህዝቡ መሀል የተንሰራፋውን ሺርክ በመጋፈጣቸው ነው። ስለሚያዝኑ ሺርክን እስከ ደም ጠብታ ታግለውታል። ስለሚያዝኑ ሸፋፍነው ሳይሆን ግልጥልጥ አድርገው ስም እየጠሩ አስተምረዋል። ስለሚያዝኑ ነው በዘመኑ የተፈሩ የታፈሩ የሚመለኩ የነበሩትን እነ ላት፣ ዑዛ፣ መናት ስም እየጠቀሱ ነው እንዳይመለኩ ያስጠነቀቁት። በተመሳሳይ ስለምናዝን ነብዩን፣ ጂላኒን፣ አባድርን፣ አልከሶን፣ ቃጥባሬን፣ አብሬትን፣ ጫሊን፣ ደገርን፣ ነጂሺን፣ ዐሊ ጎንደርን፣ ኑሩሑሴንን፣ ... ማምለክ የተሳሳተ አካሄድ እንደሆነ እናስተምራለን። ወገንን ከሺርክ ለማውጣት ከመታገል በላይ እዝነት የለም። ማዘን መቆርቆራችን የማይገባችሁ የኛና የናንተ እዝነት ለየቅል በመሆኑ ነው። እኛ ነጋ ጠባ ስለ ሺርክ የምንነዛነዘው ወገንን ከዚህ በደል ከማውጣት በላይ እዝነት የለም ብለን ስለምናምን ነው። እናንተ ደግሞ ወትሮም በነ ቃጥባሬ፣ በነ አብሬት፣... ድንበር ለሚያልፍ አካል የውሸት ታሪክ እየፈጠራችሁ ማደንዘዝን እዝነትና ርህራሄ አድርጋችሁታል። እናንተ እንድምታደርጉት አድንቆ መደነቅ አቅቶን አይደለም እሱን መንገድ የተውነው። ይልቁንም መቆርቆር ሳይሆን ሽወዳ ነው ብለን ሰላምናምን ነው የራቅነው። የመረጥነው መንድ ስም የሚያጎድፍ፣ ክብር የሚያሳጣ፣ አለፍ ሲልም ህይወት ሳይቀር ሊያስነጥቅ እንደሚችል አልጠፋንም። ቢሆንም ከነ ምሬቱ መርጠነዋል። { قُلۡ كُلࣱّ یَعۡمَلُ عَلَىٰ شَاكِلَتِهِۦ فَرَبُّكُمۡ أَعۡلَمُ بِمَنۡ هُوَ أَهۡدَىٰ سَبِیلࣰا } «ሁሉም በሚመስለው መንገዱ ላይ ይሠራል፡፡ ጌታችሁም እርሱ መንገዱ ቀጥተኛ የሆነውን ሰው ዐዋቂ ነው በላቸው፡፡ [አልኢስራእ፡ 84] = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ማሳሰቢያ፦ በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ሶስት ፍቺ ማለት ሶስት ጊዜ ደጋግሞ በሶስት ቃል ፍቺውን መግለፅ፣ ወይም በአንድ ቃል ''ሶስት ፈትቻለሁ"፣ "አስር ፈትኛለሁ" ፣ ... ማለት ሊሆን ይችላል። = (ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 13/2014) https://t.me/IbnuMunewor

በአንዴ የተፈፀመ ሶስት ፍች እንደ አንድ ነው ወይስ እንደ ሶስት የሚቆጠረው = አቋም አንድ፦ እንደ ሶስት ነው የሚቆጠረው። ስለሆነም ሌላ ሰው አግብታ ካልተለያየች በስተቀር ሶስቴ የፈታት ሰው ሊመልስ አይፈቀድለትም። ይሄ የብዙሃን ምሁራን አቋም ነው። ማስረጃዎቻቸው ከፊሉ ''ሶሪሕ" አይደሉም። ከፊሉ ሶሒሕ አይደሉም። ፅሁፌን ለማሳጠር ስል አላሰፍራቸውም። መሞገት የሚፈልግ ከስር በአደብ ሃሳብ መለዋወጥ ይቻላል። አቋም ሁለት፦ በአንድ ቃልም ይሁም በተለያየ ቃል በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ሶስት ፍቺ እንደ ሶስት ሳይሆን እንደ አንድ ነው የሚቆጠረው የሚል ነው። ማስረጃቸው፦ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- "كَانَ الطَّلَاقُ عَلَى عَهْدِ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، وَأَبِي بَكْرٍ، وَسَنَتَيْنِ مِنْ خِلَافَةِ عُمَرَ، طَلَاقُ الثَّلَاثِ وَاحِدَةً، فَقَالَ عُمَرُ بْنُ الْخَطَّابِ: إِنَّ النَّاسَ قَدِ اسْتَعْجَلُوا فِي أَمْرٍ قَدْ كَانَتْ لَهُمْ فِيهِ أَنَاةٌ، فَلَوْ ‌أَمْضَيْنَاهُ عَلَيْهِمْ، فَأَمْضَاهُ عَلَيْهِمْ " “በአላህ መልእክተኛ (ﷺ) ዘመን፣ በአቡበክርና ከዑመር ዘመንም ሁለት አመት ጊዜ (በአንዴ የተፈፀመ) ሶስት ፍቺ እንደ አንድ ነበር የሚቆጠረው። ዑመር ብኑል ኸጧብ፡ ‘ሰዎች ቀድሞ ፋታ በነበራቸው ነገር ላይ በርግጥም ቸኮሉ። ስለዚህ እሱኑ (አንዴ የተናገሩትን) ብናፀናባቸውስ?’ አሉ። ከዚያም አፀኑት።” [ሙስሊም፡ 1472] * ከዚህ ዘገባ ቀጥሎ ኢማም ሙስሊም እንዲህ የሚል አስከትለዋል፦ أَنَّ أَبَا الصَّهْبَاءِ، قَالَ لِابْنِ عَبَّاسٍ: أَتَعْلَمُ « أَنَّمَا كَانَتِ الثَّلَاثُ تُجْعَلُ وَاحِدَةً عَلَى عَهْدِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، وَأَبِي بَكْرٍ، وَثَلَاثًا مِنْ إِمَارَةِ عُمَرَ»؟ فَقَالَ ابْنُ عَبَّاسٍ: «نَعَمْ» “አቡ ሶህባእ ለኢብኑ ዐባስ ‘በነብዩ ዘመን፣ በአቡበብክርም እንዲሁ እና ከዑመርም ዘመነ ሹመት ውስጥ ሶስት አመት ያክል (በአንዴ የተፈፀመው) ሶስቱ ፍቺ አንድ ይደረግ እንደነበር ታውቃለህን?’ ሲሏቸው ‘አዎ’ ብለው መልሰዋል።” * አሁንም አልኢማም ሙስሊም ከዚህ ዘገባ ቀጥሎ እንዲህ የሚል አስከትለዋል፦ أَلَمْ يَكُنِ الطَّلَاقُ الثَّلَاثُ عَلَى عَهْدِ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، وَأَبِي بَكْرٍ وَاحِدَةً»؟ فَقَالَ: «قَدْ كَانَ ذَلِكَ، فَلَمَّا كَانَ فِي عَهْدِ عُمَرَ تَتَايَعَ النَّاسُ فِي الطَّلَاقِ، فَأَجَازَهُ عَلَيْهِمْ “ 'በአላህ መልእክተኛና በአቡበክር ዘመን ሶስቱ ፍቺ አንድ አልነበረምን?' በማለት አቡ ሶህባእ ኢብኑ ዐባስን ሲጠይቁ ‘እንደሱ ነበር። በዑመር ዘመነ ሰዎች ፍቺ ላይ በተቻኮሉ (ባበዙ) ጊዜ አፀኑባቸው’ አሉ።” አስተውሉ! ከዚህ ገለፃ የምንረዳው ዑመርም ለሆነ ፋይዳ ብለው ቢቀይሩም የሳቸው ውሳኔ ጊዜያዊ አስተያየት እንጂ ቋሚው ህግ እንዳልሆነ አነጋገራቸው ይጠቁማል። ስለዚህ እንደ ሶስት ይቆጠራል የሚለው ለሰዎች መቀጣጫና መማሪያ እንዲሆን ኋላ ዑመር ረዲየላሁ ዐንሁ ያወጁት እንጂ ነባር ህግ አይደለም ማለት ነው። ነባሩ ህግ ሶሒሕ ሙስሊም ውስጥ በግልፅ እንደሰፈረው መሀል ላይ መመለስ ሳይኖር በአንዴ ከተፈፀመ እንደ አንድ ይቆጠራል የሚለው ነው። ይሄ አቋም የኢብኑ ተይሚያ አቋም ነው። በዚህ የተነሳ "ኢጅማዕ ጥሷል" ተብለው ታስረው ወህኒ ቤት ውስጥ ነው የሞቱት። "ኢጅማዕ ጥሷል" የሚለው ክስ ከእውነት ያፈነገጠ ነው። ምክንያቱም፦ 1. "እንደ ሶስት ነው የሚቆጠረው" የሚለው ፈፅሞ ኢጅማዕ የለበትምና። ለዚህም የኢብኑ ሐጀርንና የነወዊይን ምስክርነት ማቅረብ ይቻላል። ኢብኑ ሐጀር እንደ ሶስት ሳይሆን እንደ አንድ ነው የሚቆጠረው ያሉ ምሁራንን ከዘረዘሩ በኋላ “እንዳየኸው ልዩነት በተጨባጭ ከመከሰቱ ጋር ኢብኑ ቲን እንደ ሶስት በመቆጠሩ ላይ ‘ልዩነት የለም’ ማለቱ የሚደንቅ ነው” ብለዋል። [ፈትሑል ባሪ፡ 9/363] ነወዊይም በጉዳዩ ላይ የተንፀባረቁ የተለያዩ ሀሳቦችን ባሰፈሩበት “እንደ አንድ ብቻ ነው የሚቆጠረው” ያሉትን ከመጥቀሳቸው ጋር “እንዲያውም ከነጭራሹ እንደ ፍቺም አይቆጠርም” የሚል ሀሳብ ከሐጃጅ ብኑ አርጧህ፣ ሙቃቲልና ሙሐመድ ብኑ ኢስሓቅ እንደተንፀባረቀ ጠቅሰዋል። [ሸርሑ ሙስሊም፡ 10/325] 2. ይሄ ''እንደ አንድ ነው የሚቆጠረው" የሚለው አቋም የዐልይ፣ የኢብኑ መስዑድ፣ የዐብዱረሕማን ብን ዐውፍ፣ የዙበይር፣ የሰዒድ ብኑል ሙሰይብ፣ የጣውስ፣ የዒክሪማ፣ የዐምር ብኑ ዲናር፣… የሙሐመድ ብኑ ኢስሓቅ፣ የኢብኑ ወዷሕ፣ የኢብኑ መኽለድ፣ ወዘተ ምርጫ ነው። እነዚህን ሁሉ ታላላቆች ያገለለ አቋም በምን ስሌት ነው እንደ ኢጅማዕ የሚቆጠረው? 3. ይሄ አቋም የዟሂሪያ መዝሀብ አቋምም ነው። ከአቡ ሐኒፋ፣ ከማሊክና ከአሕመድ ተከታዮችም ውስጥ የደገፉት በተጨባጭ አሉ። ስለዚህ ከቀደምቶቹም ከኋለኞቹም መሁራን የተጓዙበት ቀላል አይደሉም። ይህን ሁሉ ያላካተተ ኢጅማዕ ምን አይነት ኢጅማዕ ነው?! ይሄ ሁሉ ዑለማእ የተጓዙበትን አቋም ያስተጋባ ሰው እንዴት ኢጅማዕ ጥሰሃል ይባላል?! የሸውካኒይና የሶንዓኒይ አቋምም ይሄው ነው። ሸይኹል አልባኒይ ቀደም ብሎ በኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ ከተላለፈው "እንደ አንድ ነበር የሚቆጠረው'' ከሚለው ሐዲሥ ስር እንዲህ ይላሉ፡- “ይሄ መረጃ በአንዴ የተፈፀመ ሶስት ፍቺ እንደ አንድ እንደሚቆጠር ፅኑና አስተማማኝ ህግ ነው። ከነብዩ (ﷺ) ህልፈት በኋላም በአቡበክር አስተዳደርና በዑመር የመጀመሪያ ዘመን የተሰራበት ስለሆነ አልተሻረም። በዚያ ላይ ደግሞ ዑመር በኢጅቲሃዳቸው እንጂ በሌላ መረጃ አልተፃረሩትም። ለዚህም ነው መጀመሪያ ላይ ጥቂት ያመነቱት። ‘ሰዎች ተቻኮሉ’ እና ‘ብናፀናባቸውስ?’ የሚለው አነጋገራቸው ይህን ይጠቁማል። አንድ ዳኛ መረጃ ቢኖረው በዚህ መልኩ ሊጠይቅና ሊያመነታ ይፈቀድለታል’ንዴ? ደግሞም ‘ሰዎች ቸኮሉ’ ማለታቸው ቀድሞ ያልነበረ መቻኮል እንደተከሰተ ይጠቁማል። ለዚህም ነው ቅኑ ኸሊፋ በቅጣት መልክ ሶስቱንም ያፀኑባቸው። ከዚህ ሁሉ ጋር በአቡበክርና በዑመርም የመጀመሪያ ዘመን የነበረው በሙስሊሞች ኢጅማዕ የፀና ህግ ለዑመር ግላዊ እይታና ኢጅቲሃድ ሲባል ይተዋልን? እሳቸው ራሳቸው የአላህ መልእክተኛን (ﷺ) እና አቡበክርን ተከትለው በመጀመሪያ ዘመናቸው የሰሩበትን ትተን ኢጅቲሃዳቸውን እንወስዳለን?! በእውነት ይሄ በኢስላማዊ ፊቅህ ውስጥ ከተከሰቱ አስገራሚ ነገሮች ውስጥ ነው!! ምሁራን ሆይ! እባካችሁን ፍንትው ወዳለው ሱና ተመለሱ። በተለይ ደግሞ በዚህ አስደንጋጭ በሆነ መልኩ ፍቺ እንደጉድ ተንሰራፍቶ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተሰቦች አደጋ ባንዣበበባቸው ዘመን!!” [አሶሒሐህ፡ 3/272] የፈለገ ሙሉውን ይየው። በጣም ጠቃሚ ነው።

የማንም ክብር ከተውሒድ በላይ አይደለም። ~ ከመካ በላይ ክቡር ቦታ የለም። ግና ነብዩ ﷺ እና ሶሐቦቻቸው ለተውሒድ ሲባል መካን ጥለው ተሰደዋል። ዝምድና ትልቅ ቦታ እንዳለው የሚታወቅ ነው። ግን ከተውሒድ በላይ ስላልሆነ ነው ነብዩ ﷺ ከአጎታቸው አቡ ለሀብ እና መሰል ዘመዶቻቸው ጋር መፋጠጣቸው። ዘርና ጎሳ ከተውሒድ በላይ አይደለም። ለዚያም ነው ከቁረይሽ ጋር መሞሻለቃቸው። አንድነት ትልቅ የኢስላም እሴት ነው። ተውሒድን ገሸሽ ያደረገ አንድነት ከንቱ ስለሆነ ነው ነብዩ ﷺ "ሙሐመድ ህዝብ ለያየ" የተባሉት። የእውነትም ልዩነት ፈጥረዋል። በተውሒድና በሺርክ ሰበብ የተፈጠረ ስንጥቃት በዘርና በጎሳ ሽቦ አይጠገንም። ተውሒድ የአላህ ሐቅ ነው። የአላህ ሐቅ ከነብያትም ከመላእክትም ክብርና ሐቅ በላይ ነው። ለዒሳ ያለንን አክብሮት ዒሳን በማምለክ እንደማንገልፀው ሁሉ ለሙሐመድ ያለንንም አክብሮት እሳቸውን በማምለክ አንገልፀውም። ዒሳን ማምለክ አይገባም ማለት ዒሳን መሳደብ እንዳልሆነው ሁሉ የቃጥባሬውን ዒሳን ማምለክ አይገባም ማለት ስድብ ተብሎ ሊተረጎም አይገባም። የሁለቱ ደረጃ የተራራቀ ከመሆኑ ጋር። የአንዳንዱ ግንዛቤ በጣም የተዛነፈ ነው። ክርስቲያኖች እንደሚያደርጉት ነብዩላህ ዒሳን፣ መርየምን፣ መልአኩ ጂብሪል (ገብርኤልን)፣ ሚካኢልን፣ ... ማምለክ አይቻልም ሲባል እነዚህን ደጋጎች እየሰደባችሁ ነው አይሉም። ቃጥባሬን፣ አብሬትን፣ አልከሶን፣ ኑራሑሴንን፣ ጂላኒን፣ ዐሊ ጎንደርን፣ ደገርን፣ ገታን፣ መጂትን፣ ነጃሺን ፣ አባድርን፣ ... ማምለክ አይቻልም ሲባል ግን ወሊዮችን ሰደባችሁ የሚል ክስ ያነሳሉ። እነ ዒሳ፣ እነ መርየምኮ በኢስላም እናንተ ከምትጠሯቸው ይበልጣሉ። እነሱን አታምልኩ ማለት ስድብ ሳይሆን እንዴት ነው ከነሱ በታች የሆኑ "ወሊዮችን" አታምልኩ ማለት ስድብ የሚሆነው? በማርያም መማል ካልተቻለ በጂላኒ መማል አይገባም ሲባል ለምን ይጎረብጠሃል? "ገብርኤል ማረኝ" ፣ "ሚካኤል ተከተለኝ" ማለት ካልተቻለ እንዴት አባድር፣ ጂላኒ ድረሱልኝ ይባላል? የሺርክ ቡላና ዳለቻ አለው'ንዴ? ዒሳም፣ ሙሐመድም፣ ሌሎች ክቡራን ነብያትም (ሰላም በሁሉም ላይ ይሁንና)፣ እንደ ኣሲያ፣ መርየም፣ ኸዲጃ፣ ዓኢሻ፣ ፋጢማ፣ እንዲሁም እንደ አቡበክር፣ ዑመር፣ ... ያሉ ደጋጎችም ዝናብ አይሰጡም። ለችግር አይደርሱም። ከመከራ አያወጡም። የላቀው አላህ እንዲህ ይላል፡- {أَمَّن یُجِیبُ ٱلۡمُضۡطَرَّ إِذَا دَعَاهُ وَیَكۡشِفُ ٱلسُّوۤءَ وَیَجۡعَلُكُمۡ خُلَفَاۤءَ ٱلۡأَرۡضِۗ أَءِلَـٰهࣱ مَّعَ ٱللَّهِۚ قَلِیلࣰا مَّا تَذَكَّرُونَ} {ወይስ ያ ችግረኛ በለመነው ጊዜ መልስ የሚሰጥ፣ ክፉንም የሚያስወግድ፣ በምድርም ላይ ምትኮች የሚያደርጋችሁ (ይበልጣል ወይስ የሚያጋሩት?) (ይህን የሚያደርግ) ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለ ወይ?! ጥቂትን እንጂ አትገሰፁም!} [አነምል፡ 62] ይህንን ማድረግ የሚችለው አንድ አምላክ ብቻ ነው። ይህንን የሚያደርግ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለ ወይ?! እኮ ማን?! ፅሁፌን ብዙዎች በሚያመልኳቸው ጂላኒይ ንግግር እቋጫለሁ። እንዲህ ይላሉ፡- “አንተ ችግርህን ለፍጡር የምታቀርበው ሆይ! ወደማይጠቅምህና ወደማይጎዳህ ፍጡር አቤት ማለትህ ምን ይፈይድሃል?! ብተመካባቸውና በጌታህ ሐቅ ላይ ብታጋራቸው ያርቁሃል። ከሱ ቁጣ ላይም ይጥሉሃል። … አንተ መሀይም! ፍጡርን በመማፀንህ ግልግልን እየተመኘህ አውቃለሁ ብለህ ትሞግታለህ!! … ወዮልህ! አላህ ከማንም የበለጠ ቅርብህ ሆኖ ሳለ ከሱ ሌላ ስትከጅል አታፍርም?!” [አልፈትሑ አርረባኒ ወልፈይዱ አርረሕማኒ፡ 117-118] አታፍርም ወይ?! እፈር እንጂ! = የቴሌግራም ቻናል:- https://t.me/IbnuMunewor

የቀበሮ ባህታውያን ~ የዐረብ ሃገራት መሪዎች ብዙ ችግር እንዳለባቸው የሚታወቅ ነው። ለማንም #ጥፋት የምንከላከልበት ምንም አይነት ምክንያት የለም። ከመሆኑም ጋር ከነ ችግራቸው አላህ ይጠብቃቸው። አላህ መቃናትን ይስጣቸው። የሃገር መፍረስ በሊቢያ፣ በየመን፣ ... ሲጠቅም አላየንም። ሙዐመር አልቀዛፊን " ግ.ደ.ሉ.ት! ደሙ በጫንቃዬ ላይ ነው" እያሉ የቀሰቀሱት እነ ቀርዷዊ ናቸው። የኢኽዋን በጎች ግን ዛሬ "ጋዳፊን በሴራ ያስገደሉት ምእራባውያን ናቸው" እያሉ የአዞ እንባ እያነቡ የዋሆችን እየሸወዱ ነው። የቀበሮ ባህታውያን! "የቀበሮ ባህታዊ ከበግ መሀል ይፀልያል" አሉ። ህሊና ቢስ ፍጡሮች ሆነው እንጂ እንዴት ነው የቱርክን፣ የኢራንን መንግስት የሚያወድስ አካል ሳዑዲን የሚያብጠለጥለው? በዚህ መጠን ነው በጭንቅላታችሁ ላይ የምትሸፍቱት?! "ሳዑዲ ንጉሳዊ ናት" ብሎ ይከሳሉ። እና ቀጠር ያለው አስተዳደር የኺላፋ ስርአት ነውንዴ?! ሰርክ የምትቆዝሙለት የኦቶማን ቱርክ ስርአትስ ንጉሳዊ አልነበረም ወይ? ወይ ከታሪክ የሉ! ወይ ከሸሪዐ የሉ! ወይ ከህሊና የሉ! ቢያንስ አንዱ ጋ እንኳ እረፉ እንጂ! "ሳዑዲ ሸሪዐ የለም" ይላሉ። የአቶማን ቱርክ ነው ሸሪዐ የነበረው? የኤርዶጋን ቱርክ ነው ሸሪዐ ያለው? ወይስ ኢራን? ወይስ ቀጠር? ወይስ ሙርሲ ነበር ሸሪዐ የዘረጋው? ወይስ ሃማስ ነው በሸሪዐ የሚያስተዳድረው? እስኪ አንድ ጥቀሱ። በነዚህ ዲንን ሽፋን በሚያደርቁ ቆሻ .ሻ የቡድን ፖለቲካ በሚያራምዱ አካላት የተሸወዳችሁ አካላት ብትነቁ መልካም ነው። ቡድኑ ሁሌ ሙስሊሙ ላይ የሚደርሱ ወቅታዊ መከራዎችን ለቡድናዊ ትርፍ ለመጠቀም የሚተጋ የደም ነጋዴ ነው። እንጂ እያንዳንዱ የዐረብ ሃገራትን የሚኮንንበት ነጥብ በባሰ መልኩ ከሚከላከልላቸው መንግስታት ውስጥ ይገኛል። በገዛ ህሊናው ላይ የሸፈተ ሰው ካልሆነ በስተቀር ለኢራንና ለቱርክ የሚከላከል አካል ሳዑዲን ነጥሎ ከማብጠለጥል ጀርባ ያደፈጠ ኢኽዋናዊ ምክንያት እንዳለ አይጠፋውም። በመካከለኛው ምስራቅ ትልቁ የአሜሪካ የጦር ካምፕ ያለውኮ በቀጠር ነው። በቱርክም የአሜሪካ የጦር ካምፖች አሉ። ኢማራት የሂንዱ የአምልኮ ቦታ በመፍቀዷ የጮሁ ሰዎች ስለ ቀጠር ቤተ ክርስቲያን ግን ትንፍሽ የማይሉት ለምን ይመስላችኋል? ያደፈጠ ኢኽዋናዊ ቫይረስ ነው እንዲህ የሚያደርጋቸው። ደግሞ በሃኒያ ሞት ደስታቸውን ገለፁ እያሉ ይከሳሉ። (በቅድሚያ እኔ እዚህ ውስጥ ራሴን አላስገባሁም።) ግን ደግሞ የኢኽዋን ቡድንኮ ሳዑዲ ላይ በሚደርሱ ፈተናዎች ሁሉ በመደሰት ነው የሚታወቀው። በኮሮና ጊዜ የሃገራችን ታዋቂ ኢኽዋኒዮች ሲቀባበሉት የነበረውን ፅሁፍ እናስታውሳለን። ፍልስጤማውያንም በንጉስ ዐብደላህ ሞት ሲደሰቱ ነበር። (አያይዤዋለሁ።) ከመቼ ወዲህ ነው ደግሞ የሞራል ሰባኪ የሆናችሁት? እኮ እናንተ! ለማንኛውም እወቁ! እናንተ ስለ ሳዑዲ ከምታወሩት በላይ ስለ ኢራን፣ ቱርክ፣ ቀጠር፣ ስለ ሙርሲ የአገዛዝ ዘመን ብዙ ማውራት እንችላለን። ዝምታን የመረጥነው በሳዑዲ ለሚታዩ ክፍተቶች ሽፋን እየሰጠን እንዳይመስል ብለን ነበር። እንደ ቅዱስ ሲሰራራችሁ ግን በሚገባችሁ ቋንቋ ለማውራት እንገደዳለን። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፡- ❝የዲን መጀመሪያውም መጨረሻውም ውጫዊውም ውስጣዊዉም  ተውሂድ ነው ኢኽላስም ዲንን ለአላህ ብቻ ጥርት ማድረግ ነው እሱም «ከአላህ በስተቀር በሃቅ የሚመለክ ሌላ አምላክ የለም» የሚለውን ማረጋገጫ ነውና።❞ 📚 مجموع الفتاوى (٢٦/١٠) https://t.me/Daewa_Selefya

+2
🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚القواعد الحسان المتعلقة بتفسير القرآن -22 📝تأليف: العلامة الإمام عبدالرحمن بن ناصر السعدي رحمه الله تعالى 🎙لفضيلة الشيخ محمدزين بن الشيخ آدم حفظه الله ورعاه 📚የአል_ቀዋዒዱል_ሒሳን ኪታብ ማብራሪያ - ክፍል - 22 📝የኪታቡ ደራሲ ፡- ሸይኽ አብዱራህማን ኢብኑ ናስር አስ'ሰዓዲ ረሂመሁሏህ 🎙የደርሱ አቅራቢ ሸይኽ ሙሐመድዘይን ሸይኽ ኣደም   ሀፊዘሁላህ 🗓ዛሬ ማክሰኞ ሙሀረም 24-1446 (ሐምሌ 23-2016)  የተሰጠ ደርስ ነው ። 🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4689 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓ https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4481 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ 🕌ቦታ ፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ "نورها الله تعالى بمنه وكرمه بنور التوحيد والسنة " 🗓ዘወትር ከሰኞ እስከ ሐሙስ ከሰዓት 8:10 እስከ 9፡00 ድረስ በቀጥታ ይተላለፋል 👉በሸይኽ ሙሐመድዘይን ሸይኽ ኣደም የሚሰጡ ትምህርቶችን ለመከታተል.... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn Or https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam

ሌላ ዙር የኒያ ፕሮግራምና የግንባታ ስራ፦ ከዚህ በፊት ባለፉት አመታት የኒያ ፕሮግራም ሲደረግ የቆየ ቢሆንም ነግር ግን በዛን ስአት የአላህ አለመፍቀድ ሁኖ ወደ ግንባታ ሳይገባ ቢቀርም ዛሬ ግን የአ
ሌላ ዙር የኒያ ፕሮግራምና የግንባታ ስራ፦ ከዚህ በፊት ባለፉት አመታት የኒያ ፕሮግራም ሲደረግ የቆየ ቢሆንም ነግር ግን በዛን ስአት የአላህ አለመፍቀድ ሁኖ ወደ ግንባታ ሳይገባ ቢቀርም ዛሬ ግን የአላህ መልካም ፈቃድ ታክሎበት ከብዙ ጥረት በኋላ ዛሬ ላይ በቀጥታ መርከዙን በማፍረስ በህንጻ መልኩ የመልሶ ግንባታ ላይ ነን።በመሆኑም ሀገራችን ላይ ያለው የገባያ ንረት የማቴሪያል ውድነት ትላንት ባሰብነዉ መልኩ ሳይሆን ቀርቶ ከእጥፍ በላይ ጭማሬ በማሳየቱ በእጃችን ላይ ያለውን ገንዘብ እንዲዳከም አድርጎታል።ሆኖም ግን  የያዝነውን ይዘን ወደ ግንባታ የገባን ስለሆንን ዛሬም እንደትላንቱ አብረን ተባብረን እንገንባ ስንል።ከአላህ በኋላ ወደ እናንተ መጥታል። መርከዙ በG+2 ስለሆነ የሚገነባው አላህ አሳክቶት የተቀላጠፈ እንደሁ የብዙዎችን ጥያቄ ይመልሳል ተብሎ ይገመታል። *የመርከዙን ዲዛይን ከስር አያይዣለሁ። ☞መርከዝ ኢብኑ አባስ በከሚሴ☟ https://t.me/+lmLw2jJXwF45Zjdk ↪️ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ አካውንት 👇👇 ስም—  አወል አሕመድ እና ኸድር አህመድ መሀመድ  ቁጥር-  1000365610456

ሴት ወንዶችን ማከም ~ ጥያቄ፦ አድማጭ እንደምትለው እድሜዋ ሃያ ስድስት አካባቢ የሆነች ወጣት ነች። በስርአት የለበሰች ናት። በዚህም ጌታዋን ታመሰግናለች። ክሊኒክ ውስጥ ነርስ ሆና ትሰራለች። ቁስለኞችን ታክማለች። እንዲሁም ለሴቶችም ለወንዶችም መርፌ ትወጋለች። በዚህን ጊዜ መድሃኒቱን ለመስጠት ስትል የህመምተኛውን አካል ትነካለች። "ስራዬ ይሄ ነው። ሌላ የሪዝቅ ሰበብ የለኝም። የተከበሩ ሸይኽ ሆይ! ይሄ ስራዬ ችግር አለበትን? አላህ ይመንዳዎትና ይመልሱልኝ" ትላለች። መልስ፦ ይሄ ስራዋ ምንም ችግር የለበትም። ምክንያቱም ሴት ወንድን እንድታክም የሚገፋ ምክንያት ከኖረ በዚህ ላይ ችግር የለምና። በዚህ ላይ አካሉን እንድትነካው የሚያስገድድ ሁኔታ ኖረም አልኖረም ችግር የለውም። ነገር ግን ከወንዶች ጋር በተያያዘ ቀጥታ አካል እንዳትነካ ጓንቶችን ልትለብስ ይገባታል። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ከዌብሳይታቸው የተወሰደ = * ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor * ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL * ዋትሳፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M

በሃገራችንም ያለው ተጨባጭ ይሄው ነው። የኢኽዋን አልሙስሊሚን አመለካከት እየተከተሉና እያራመዱ ኢኽዋኒዮች መሆናቸውን ግን አያምኑም። ከስንት አንድ ካልሆነ በስተቀር ኢኽዋኒይነቱን የሚያምን የለም። በግምት የዛሬን 12 አመት አካባቢ አንዱ ታዋቂ የሃገራችን ኢኽዋኒይ "እኔ እንደ ሌሎቹ ኢኽዋኖች ማንነቴን አልደብቅም። በግልፅ ኢኽዋኒነቴን እነግርሃለሁ" እያለ መስማቴን በሚገባ አስታውሳለሁ። ለማንኛውም በፊክራችሁ ኢኽዋኒዮች ሆናችሁ ሳለ ራሳችሁን ለመግለፅ የምትሸማቀቁ ኢኽዋኒዮች ሆይ! የምትሳቀቁበት ቡድን ለምን አይቀርባችሁም? = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

+1
🔖አዲስ ተከታታይ ትምህርት 📚القواعد الحسان المتعلقة بتفسير القرآن -15 📝تأليف: العلامة الإمام عبدالرحمن بن ناصر السعدي رحمه الله تعالى 🎙لفضيلة الشيخ محمدزين بن الشيخ آدم حفظه الله ورعاه 📚የአል_ቀዋዒዱል_ሒሳን ኪታብ ማብራሪያ - ክፍል - 15 📝የኪታቡ ደራሲ ፡- ሸይኽ አብዱራህማን ኢብኑ ናስር አስ'ሰዓዲ ረሂመሁሏህ 🎙የደርሱ አቅራቢ ሸይኽ ሙሐመድዘይን ሸይኽ ኣደም   ሀፊዘሁላህ 🗓ዛሬ እሮብ ሙሀረም 11-1446 (ሐምሌ 10-2016)  የተሰጠ ደርስ ነው ። 🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4614 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በ Pdf መልክ በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ ↓↓↓ https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn/4481 ═════ ≪ °📓🖇📓° ≫ ════ 🕌ቦታ ፉሪ አቡበክር አስ-ሲዲቅ መስጂድ "نورها الله تعالى بمنه وكرمه بنور التوحيد والسنة " 🗓ዘወትር ከሰኞ እስከ ሐሙስ ከሰዓት 8:10 እስከ 9፡00 ድረስ በቀጥታ ይተላለፋል 👉በሸይኽ ሙሐመድዘይን ሸይኽ ኣደም የሚሰጡ ትምህርቶችን ለመከታተል.... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/abuhuzeyfashaikhmohammedzeyn Or https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam

ኢማም አል-ፈቂህ ኢብራሂም አል-ተይሚ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡- ❝አንድም ሰው በአላህ ከማመን በኋላ በላጭን ነገር አልተሰጠም በተለያዩ ችግሮችና  ጉዳቶች ፈተናዎች ጊዜ መታገስን ሶብርን የተሠጠ ቢሆን እንጂ።❞ 📚(الصبر والثواب عليه) (ص - ٢٨) https://t.me/Daewa_Selefya

سورة الكهف 🎙أبوبكر الشاطري ❤️ t.me/abu_reyyis_arreyyis

አባካኝነትን እንራቅ ~ ሁሉም ነገር ልክ አለው። እዝነት ልክ አለው። መስዋእትነት ልክ አለው። ዒባዳ ልክ አለው። ቸርነት ልክ አለው። ደግነት ልክ አለው። መልካም ነገር ከልኩ ሲያልፍ ስሙ ይቀየራል። ደግነቱ ሞኝነት ይሆናል። ጥንቃቄው ፍርሃት ይሆናል። ብልህነቱ አጉል ብልጣብልጥነት ይሆናል። ያኔ ውበቱን መልኩን ያጣል። ያኔ ጉዳዩ ወደ ውጉዝነት ተሸጋግሯል ማለት ነው። ይህ እንዳይሆን ትኩረት መስጠት ይገባል። በልክ መሆን ውበት ነው። በልክ መሆን ጨዋነት ነው። በልክ መሆን ታስቦበት ሲሆን ዒባዳ ነው። በልክ መሆን ሞገስ አለው። ልክ ማለት ወደ ላይም ወደ ታችም ድንበር አለማለፍ ነው። በአቋምህ ድንበር አትለፍ። በንግግርህ ድንበር አትለፍ። በገንዘብ አያያዝህ ድንበር አትለፍ። በጊዜ አጠቃቀምህ ድንበር አትለፍ። ለሁሉም ነገራችን ለከት ሊኖረው ይገባል። ለምሳሌ ገንዘብ ጋር የተያያዘውን አባካኝነት ላንሳ። ጌታችን አላህ አባካኝነትን ይነቅፋል። እንዲህ ይላል፦ { وَلَا تُبَذِّرۡ تَبۡذِیرًا (26) إِنَّ ٱلۡمُبَذِّرِینَ كَانُوۤا۟ إِخۡوَ ٰ⁠نَ ٱلشَّیَـٰطِینِۖ وَكَانَ ٱلشَّیۡطَـٰنُ لِرَبِّهِۦ كَفُورࣰا (27) } "ማባከንንም አታባክን፡፡ አባካኞች የሰይጣናት ወንድሞች ናቸውና፡፡ ሰይጣንም ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው።" [አልኢስራእ፡ 26-27] በዚህ ቦታ ላይ አባካኝነት ከግልፅ ክልከላ ባለፈ በጥብቅ እየተኮነነ ነው። ሙስሊም የሆነ ሰው እንዲህ ዓይነቱን ማሳሰቢያ እንደዋዛ ሊያልፈው አይገባም። ስለዚህ፦ * አመጋገባችን ላይ ብክነት እንዳይኖር እንጠንቀቅ። በልካችን እናቅርብ። በልካችን እንመገብ። አላህ አባካኞችን አይወድም። {وَكُلُوا۟ وَٱشۡرَبُوا۟ وَلَا تُسۡرِفُوۤا۟ۚ إِنَّهُۥ لَا یُحِبُّ ٱلۡمُسۡرِفِینَ } "ብሉ፤ ጠጡም፤ አታባክኑም፡፡ እርሱ አባካኞችን አይወድምና።" [አልአዕራፍ፡ 31] * ስንታጠብ፣ ውዱእ ስናደርግ፣ እቃ ስናጥብ ውሃ አናባክን። ነብያችን ﷺ በውዱአቸውም በትጥበታቸውም ላይ የውሃ አጠቃቀማቸው የተመጠነ ነበር። በመኖሪያ ቤቶችም ይሁን በመስጂዶች ወይም በሌላ ቦታዎች የውሃ አጠቃቀማችን በልክ ይሁን። ስንጨርስ ቧንቧዎችን በትክክል እንዝጋ። የተበላሸውን እንጠግን። * ያለ ፋይዳ መብራቶችን አናብራ። በማይፈልግ ቦታና ጊዜ የሚበሩትን እናጥፋቸው። የቤታችንን መብራት፣ ማገዶ፣ ናፍጣ፣ ነዳጅ፣ ሲሊንደር ጋዝ፣ ... ያለ ፋይዳ ሲሰራ አይተን አንለፍ። * በጥቅሉ ልብሳችን፣ ገንዘባችን፣ ሞባይላችን፣ ኮምፒተራችን፣ ... ሁሉም አይነት ንብረታችን ባግባቡ ሊይያዝ የሚገባ የጌታችን ስጦታ ነው። ያለ አገልግሎት የትኛውም ሃብት ሊባክን አይገባም። ጌታችን ስለዋለልን ኒዕማዎች ከማመስገን ውስጥ አንዱ ፀጋዎቹን ባግባቡ መጠቀም ነው። ይሄ ከደጋግ የአረሕማን ባሪያዎች መታወቂያዎች ውስጥ ነው። የላቀው ጌታ እንዲህ ይላል፦ { وَٱلَّذِینَ إِذَاۤ أَنفَقُوا۟ لَمۡ یُسۡرِفُوا۟ وَلَمۡ یَقۡتُرُوا۟ وَكَانَ بَیۡنَ ذَ ٰ⁠لِكَ قَوَامࣰا } "እነዚያም በለገሱ ጊዜ የማያባክኑ የማይቆጥቡትም ናቸው፡፡ በዚህም መካከል (ልግስናቸው) ትክክለኛ የሆነ ነው።" [አልፉርቃን፡ 67] ባይሆን አታባክን ማለት ሰስት ማለት አይደለም። አላህ የሰጠንን ፀጋ እሱ በሚወደው ቦታ ላይ ባግባቡ ማውጣት የታዘዝንበት አደራ ነው። ብቻ ሁሉም በልክ ሲሆን ያምራል። { وَلَا تَجۡعَلۡ یَدَكَ مَغۡلُولَةً إِلَىٰ عُنُقِكَ وَلَا تَبۡسُطۡهَا كُلَّ ٱلۡبَسۡطِ فَتَقۡعُدَ مَلُومࣰا مَّحۡسُورًا } "እጅህንም ወደ አንገትህ የታሰረች አታድርግ፡፡ መዘርጋትንም ሁሉ አትዘርጋት፤ የተወቀስክ የተቆጨኽ ትኾናለህና።" [አልኢስራእ፡ 29] = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

🗒የዐሹራእን ፆም የተመለከቱ የተወሰኑ ማስታዎሻዎች! • የዐሹራእ ፆም የሚባለው እንደ ሒጅራ አቆጣጣር የመጀመሪያው የሙሐረም ወር በገባ በአስረኛው ቀን የሚፆም ፆም ነው። ይህ ፆም እጅግ ከተጠኑ የሱና ፆሞች መካከል ከዋናዎቹ ነው። • وعن أبي قتادة -رضي الله عنه-، أنّ النّبي -صلّى الله عليه وسلّم- قال: ( صيامُ يومِ عاشوراء، أحتسب على اللَّه أنْ يُكَفِّرَ السّنة التي قبله ). [أخرجه مسلم] • ከአቡ ቀታዳ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዙ ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) "የዓሹራእ ቀን ፆም ከሱ በፊት የነበረውን ዓመት ወንጀል ያስምራል ብዬ በአላህ ላይ ተስፋ አደርጋለሁ" አሉ። 📗【ሙስሊም ዘግበውታል】 • ዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ሰለ ዐሹራእ ፆም ተጠይቀው እንዲህ አሉ :-  " ነብዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሌሎች ቀኖች አሰበልጠው የሚፆሙበትን ቀን ሲጠባበቁ ከዚህ ቀን ውጪ አላውቅም (የዐሹራእን ቀን ማለቱ ነው።) ወርን ሲጠባበቁ አላየሁም የዚህን ወር ያክል  (የረመዳን ወር ማለቱ ነው።) 📒【ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል】 • የዐሹራእ ቀን የሚባለው የሙሐረም 10 ኛው ቀን ነው።የሙሐረምን 10 ኛውን ቀን በፆም ማሳለፍ ከላይ በሐዲሡ ላይ እንዳየነው ያለፈውን የአንድ አመት ወንጅል ያስምራል። ለሙስሊሞች እሄን ቀን በመፆም እራሳቸውን፣ልጆቻቸውን፣ቤተሰቦቻቸውንና ማሀበረሰባቸውን ሊያነሳሱ ይገባቸዋል። • ማሳሰቢያ:- ያለፈውን የአመት ወንጀል ያስምራል ማለት ትንንሹን ወንጀል ነው እንጅ ትልልቁን ሀጢአት አይደለም ትልቅ ወንጀል ዝሙት፣ህሜት፣ነገረኝነት፣ሪባ እና መሰል ትልልቅ ወንጀሎች  መስፈርቱን ያሟላ እራሱን የቻለ ተውበት ያስፈልጋቸዋል። • በዚህ ቀን ወደአላህ ልንመለስ ካለፈው ወንጀላችን በአጠቃላይ ከትልቁም ከትንሹም በመፀፀት እውንተኛ ተውበትን ልንቶብት ይገባል። ተውበትን አላህ በማንኛውም ጊዜ ቢቀበልም በእንደዚህ ብልጫ ባላቸው ጊዜዎች ከሌላው በተለዬ ጊዜ ይቀበላል። በተለይ እኛ እንደሂጅራ አቆጣጠር አድስ አመትን እየጀመርን ስለሆነ ካለፈው ጥፋታችን በመመለስ በተረፈው በመስተካከል ወደአላህ ልንመለስ ይገባናል። • የዐሹራእ ፆም ምክኒያት:- የዐሹራእን ቀን መፆም ሱና ሁኖ የተደነገገው አሏህ ሙሳንና ህዝቦቾዎን ከፊርዐውን ሰላም ያወጣበት ቀን እንዲሁም ፊርዐውንና ሰራዊቱን ያጠፋበት ቀን ስለሆነ አላህን ለማመስገን ነው። ለዚህም ተብሉ ሙሳ(ዐለይሂ ሰላም) ይህን ቀን ፁመውታል አይሁዶችም ሙሳን ተከትለው ፁመውታል።እኛ ሙስሊሞች ሙሳን በመከተልና በሙሳ ሰላም መውጣት በጠላታቸው መጥፋት በመደሰት ከአይሁዶች የበለጠ የተገባን ነን • ከላይ የጠቀስኩት የዐሹራእ ፆም ምክንያት በዚህ ሐዲሥ ተገልፇል:- عن ابن عباس ((قَدِمَ النَّبِيُّ -صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ- المَدِينَةَ فَرَأَى الْيَهُودَ تَصُومُ يَوْمَ عَاشُورَاءَ فَقَالَ مَا هَذَا؟ قَالُوا: هَذَا يَوْمٌ صَالِحٌ، هَذَا يَوْمٌ نَجَّى اللَّهُ بَنِي إِسْرَائِيلَ مِنْ عَدُوِّهِمْ فَصَامَهُ مُوسَى، قَالَ فَأَنَا أَحَقُّ بِمُوسَى مِنْكُمْ فَصَامَهُ وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ)).  【صحيح البخاري】 • ከኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ:– "ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና በገቡ ጊዜ አይሁዶች የዐሹራእን ቀን ሲፆሙ አዩዋቸው ነቢዩም (ለአይሁዶች) "ይህ (የምትፆሙት) ምንድነው?" አሉዋቸው ይህ ምርጥ ቀን ነው ይህ ቀን አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው ሰላም ያወጣበት ቀን ነው። ስለዚህ ሙሳ ፆሞታል። አሉ ነቢዩም "እኔ ለሙሳ ከናንተ የበለጠ የቀረብኩኝ(የተገባሁኝ) ነኝ ብለው ፆሙት እንዲፆምም አዘዙ።" 📒【ቡኻሪ ዘግበውታል】 • ከአስረኛው ቀን በስተፊት ያለውን ማለት የዘጠነኛውን ቀን አብሮ መፆም ይወደዳል። ኢብኑ ዐባስ(ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዲህ ይላሉ:- "ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዐሹራእን በፆሞና እንዲፆምም ባዘዙ ጊዜ (ሱሐቦች) የአላህ መልእክተኛ ሆይ እርሱኮ አይሆዶችና ነሷራዎች የሚያከብሮት ቀን ነው አሏቸው። ነቢዩም (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) «አሏህ ካለ በቀጣይ አመት የዘጠነኛውን ቀን እንፆማለን» አሉ (ኢብኑ ዐባስ) "የቀጣዩ አመት አልመጣም ነቢዩ(አለሂሶላቱ ወሰላም) የሞቱ ቢሆን እንጅ" አለ 📒【ሙስሊም ዘግበውታል】 ስለዚህ ለዚህ ሐዲሥ ሲባል ዘጠነኛውን ቀን ከአስረኛው ጋር አብሮ መፆም ይወደዳል። • « አስረኛውን ብቻ በፆም መለየት ከአይሁድ ጋር እንዳይመሳሰል ከሙሐረም ዘጠኝና አስርን አብሮ መፆምን ብዙ ዐሊሞች ይወደዳል ብለዋል (ከነርሱም መካከል) ኢማሙ ማሊክ፣ኢማሙ ሻፊዒይና ኢማሙ አሕመድ» 📁ምንጭ【ሶሒሁ ፊቂሂ ሱናህ (2/121)】 • ከላይ ያሳለፍነው ሐዲሥ ከከሀዲዎች ጋር መመሳሰል በሸሪዓችን ክልክል እንደሆነ  መረጃ ነው።ሸሪዓ እንድህ በዒባዳቸው እንኳ እንዳንመሳሰል ይከለክለናል ዛሬ የሚያሳዝነው ብዙው ወጣት በሚሰሩት ሀራም እና ፀያፍ ተግባራቸው ሳይቀር ይከተላቸዋል ውርደት ማለት እሄነው። አላህ ከውርደት ይጠብቀን። • ቀደምቶቻችን የዐሹራእን ፆም  በአስቸጋሪ ሆኔታ እንኳ ቢሆኑም ይፆሙት ነበር። • ኢማም ዙህርይ ሙሳፊር(መንገደኛ) ሁነው ሳለ የዓሹራን ፆም ፆሙ ለርሳቸውም "አንቱ በመንገድ ላይ ስትሆኑ ከረመዳን ፆም እያፈጠርኩ ለምን (በመንገድ ላይ ስትሆኑ) ዓሹራን  ትፆማለሁ" ተባላቸው "ረመዷን በሌላ ቀን (የቀዷ ማውጫ) ግዜ አለው ዓሹራእ ግን ያልፋል (የማካካሻ ቀን የለውም) በማለት መለሱ። • 【ሲየሩ አዕላሚ ኑበላእ (5/342)】 • በዚህ የዐሹራ ቀን ሁለት ቡድኖች ተሳስተው ጠመዋል የመጀመሪያዎቹ:- ዓሹራእን ልክ እንደ ዒድ ወን አድርጎ በመያዝ በዚህ ቀን አድስ ልብስ ይልብሳሉ የተለየ ምግብ ያዘጋጃሉ እንድሁም በመኳኳልና በመቀባባት ይበጃጃሉ አንዳንዶቹም መውሊድ በማድረግ ይደግሳሉ ይህ ሁሉ ረሱል(ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንድንሰራው ያላዘዙን ጥመትና ቢድዓ ነው። ከእንድህ አይነት ጥፋት እኛም ቤተሰቦቻችንም ልንርቅ ይገባናል። ሁለተኞቹ:- አንጃዎች ደግሞ እሄን ቀን ሑሰይን ኢብኑ ዐሊይ(ረዲዬሏሁ ዐንሁ) የተገደለበት ቀን ነው በማለት  የአዘን እና የለቅሶ ቀን አደረጉት በዚህቀን አዝነው ተግዘው ሲያለቅሱ ሌሎችም የጃሂልያ ተግባር ሲያደርጉ ይውላሉ ይህም በሸሪዓ ያልተደነገገ ጥመት ነው። አሏህ በእነዚህ ሁለት የጠፉ አንጃዎች መካከል አህሉሱኖችን ለቀጥተኛው መንገድ መራቸው እሄንቀን ረሱል (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዳዘዟቸው በመፆም እና ሌሎችንም የተደነገጉ ዒባዳዎች በማድረግ ያሳልፉታል። የዐሹራእ ፆም ትሩፋቱና ምክኒያቱ እሄን ይመስላል  ወሏሁ አዕለም! ✍ ወንድማችሁ ኢብኑ ሙሐመድዘይን (ሙሐረም 8 /1441) t.me/IbnuMuhammedzeyn t.me/IbnuMuhammedzeyn