en
Feedback
HaroTube

HaroTube

Open in Telegram

መረጃዎችን ለመላክ @harotubeinfo

Show more
9 518
Subscribers
-424 hours
-547 days
-22030 days
Posts Archive
ቡና ከፈንድሻ ጋር ለምን ይቀርባል? ☕🍿 በባህላዊ የቡና ስነ-ስርዓታችን ላይ ከቡናው ጎን የሚቀርበው ፈንድሻ እንዲሁ ተራ መክሰስ ብቻ አይደለም። ፈንድሻ ለማዘጋጀት ቀላል፣ ለመካፈል አመቺ እና ከጠ
ቡና ከፈንድሻ ጋር ለምን ይቀርባል? ☕🍿 በባህላዊ የቡና ስነ-ስርዓታችን ላይ ከቡናው ጎን የሚቀርበው ፈንድሻ እንዲሁ ተራ መክሰስ ብቻ አይደለም። ፈንድሻ ለማዘጋጀት ቀላል፣ ለመካፈል አመቺ እና ከጠንካራ ቡና ጣዕም ጋር ፍጹም የሚዋሃድ ሲሆን፣ ስነ-ስርዓቱን ይበልጥ ትርጉም ያለው ያደርገዋል። ቡናው ሰዎችን ወደ ማዕድ ሲጠራቸው፣ የቡናው ዝግጅትና ጨዋታው ደግሞ አብረው እንዲቆዩ ያደርጋቸዋል፤ ዋናው ነገር ቡናው ብቻ ሳይሆን አብሮነቱ ነው! ✨ ምንጭ፡ thehabeshabarista

ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በአንስቴዥያ በትምህርት ክፍል በ3.92 ውጤት የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኖ ተመርቆ ላለፈው አንድ ዓመት ሥራ አጥቶ የነበረው ጎበዙ ወጣት ይበልጣል፣ የሥራ ዕድል ተፈጠረለት። የኢሊት
ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በአንስቴዥያ በትምህርት ክፍል በ3.92 ውጤት የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኖ ተመርቆ ላለፈው አንድ ዓመት ሥራ አጥቶ የነበረው ጎበዙ ወጣት ይበልጣል፣ የሥራ ዕድል ተፈጠረለት። የኢሊት የአንገት በላይ ቀዶ ሕክምና ማዕከል እና ታዋቂው ስፔሻሊስት ዶክተር አብይ ታደሰ ለወጣቱ የሥራ ዕድሉን የፈጠሩለት ሲሆን፣ ማዕከሉ የላቀ ብቃት ያላቸውን ወጣቶች መደገፍ እንደሚያስፈልግ ገልጿል። ይህ አርአያነት ያለው ተግባር ለሌሎች ተስፋ የሚሰጥና በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈ ሆኗል።

መልካም ልደት እና 11ኛው የጋብቻ በዓል ለሰይፉ ፋንታሁንና ለባለቤቱ ቬሮኒካ! 🎉💍 ተወዳጁ የሚዲያ ሰው ሰይፉ ፋንታሁን በዛሬው ዕለት የልደት ቀኑን እንዲሁም ከባለቤቱ ቬሮኒካ ጋር 11ኛ ዓመት የ
መልካም ልደት እና 11ኛው የጋብቻ በዓል ለሰይፉ ፋንታሁንና ለባለቤቱ ቬሮኒካ! 🎉💍 ተወዳጁ የሚዲያ ሰው ሰይፉ ፋንታሁን በዛሬው ዕለት የልደት ቀኑን እንዲሁም ከባለቤቱ ቬሮኒካ ጋር 11ኛ ዓመት የጋብቻ በዓሉን በጥምር ደስታ እያከበረ ይገኛል። በሙያው በርካቶችን ያፈራውና በደግነቱ የሚታወቀው ሰይፉ፣ በአራት ልጆች የተባረከውን ያማረ የትዳር ህይወቱን እያጣጣመ ይገኛል። ለጋዜጠኛ ሰይፉ እና ለባለቤቱ መልካም የጋብቻ በዓልና የልደት ቀን ይሁንላችሁ እንላለን! ❤️✨

በአገራችን ሙዚቃ ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያላቸው ድምፃውያን ማሚላ እና ኪቺኒ፣ ለ12 ዓመታት ያህል የቆየውን አለመግባባት በመተው ታርቀዋል። እርቁ የተፈጸመው በጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን 50ኛ የልደት
በአገራችን ሙዚቃ ውስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያላቸው ድምፃውያን ማሚላ እና ኪቺኒ፣ ለ12 ዓመታት ያህል የቆየውን አለመግባባት በመተው ታርቀዋል። እርቁ የተፈጸመው በጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን 50ኛ የልደት በዓል ላይ ሲሆን፣ በርካታ የጥበብ ሰዎችም ለእርቁ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አድርገዋል። ሁለቱ አርቲስቶች በቅርቡ በሀዋሳ በሚካሄድ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ በጋራ ወደ መድረክ እንደሚመለሱ ታውቋል።

ከ10 ቀናት በፊት በETFC 2 የውድድር መድረክ ላይ ከባድ ፍልሚያ ሲያደርጉ የቆዩት ጆኒ ሴዶ እና ተጋጣሚው፣ በጥሬ ሥጋ ግብዣ ባህላዊ እርቅ ፈጽመዋል። ሁለቱ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ወቅት የነበረውን
ከ10 ቀናት በፊት በETFC 2 የውድድር መድረክ ላይ ከባድ ፍልሚያ ሲያደርጉ የቆዩት ጆኒ ሴዶ እና ተጋጣሚው፣ በጥሬ ሥጋ ግብዣ ባህላዊ እርቅ ፈጽመዋል። ሁለቱ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ወቅት የነበረውን ቅሬታ ወደ ጎን በመተው በስፖርታዊ ጨዋነት እና በፍቅር አብረው አምሽተዋል። «በውድድር መድረክ ተጋጣሚ፣ በምግብ ጠረጴዛ ደግሞ ወንድማማች» በሚል መንፈስ የተከናወነው ይህ ስብሰባ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን አትርፏል።

የኃዘን መርዶ፦ ታዋቂዋ አንጋፋ ድምፃዊት ኤልፍነሽ ቀኖ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ! በአፋን ኦሮሞ ባህላዊ ሙዚቃ እድገት ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉት አንጋፋዋ ድምፃዊት ኤልፍነሽ ቀኖ ህልፈተ ህይወት ተ
የኃዘን መርዶ፦ ታዋቂዋ አንጋፋ ድምፃዊት ኤልፍነሽ ቀኖ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ! በአፋን ኦሮሞ ባህላዊ ሙዚቃ እድገት ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉት አንጋፋዋ ድምፃዊት ኤልፍነሽ ቀኖ ህልፈተ ህይወት ተሰምቷል። ድምፃዊቷ በካሴት ዘመን ባበረከቷቸው ድንቅ ስራዎች ባህልን፣ ትዝታን እና ማንነትን በማስተሳሰር ለትውልዶች የማይረሳ ጥበባዊ ቅርስ ጥለው አልፈዋል። ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለመላው የሙዚቃ አፍቃሪዎች መጽናናትን እንመኛለን። ነፍሳቸው በሰላም ትረፍ! 🙏

የ2026 ዳይመንድ ሊግ የዙር ውድድር ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል በ 8:08.67 በሆነ ሰዓት አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል። ገመቹ የሞሮኮውን የዓለምና የኦ
የ2026 ዳይመንድ ሊግ የዙር ውድድር ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል በ 8:08.67 በሆነ ሰዓት አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል። ገመቹ የሞሮኮውን የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ሱፊያን ኤል ባካሊን በማስከተል ቀዳሚ ሆኖ ያጠናቀቀ ሲሆን፣ ከፍሬወይኒ ኃይሉ በመቀጠል ሁለተኛው ኢትዮጵያዊ አሸናፊ ለመሆን ችሏል። በሌሎች ውድድሮች በ 800 ሜትር ሳይዳ ፀሀዬ 3ኛ እንዲሁም በ 5ሺህ ሜትር ቢኒያም መሀሪ 4ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።

ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ ወደ ስራ መመለስ ወይም መቀመጥ የተለመደ ቢሆንም፣ ከ 2 እስከ 15 ደቂቃ ያህል በእግር መጓዝ ለጤናችን ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው የጤና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ከምግብ በኋላ በእ
ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ ወደ ስራ መመለስ ወይም መቀመጥ የተለመደ ቢሆንም፣ ከ 2 እስከ 15 ደቂቃ ያህል በእግር መጓዝ ለጤናችን ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው የጤና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ከምግብ በኋላ በእግር መጓዝ በደም ውስጥ ያለውን የስኳር መጠን ለማስተካከል፣ የምግብ መቃጠል ሂደትን ለማፋጠን፣ የሆድ እብጠትን ለመቀነስ እና የደም ዝውውርን ለማሻሻል ይረዳል። በተጨማሪም የልብ ጤንነትን ለመጠበቅ እና የድብርት ስሜትን ለመቀነስ የሚረዳ ሲሆን፣ በቀን ውስጥ ተጨማሪ እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ቀላሉ መንገድ ነው። ከምግብ በኋላ አጠር ያለ ፈጣን እርምጃ ማድረግ ለጤናችን ትልቅ ለውጥ ያመጣል።

ዛሬ የ2018 ዓ.ም አሥራ ሦስተኛዋ ወር ጳጉሜ 1 በመንፈሳዊ በረከት እና በእሁድ ዕለት እረፍት ተጀምራለች። ጳጉሜ ያለፈውን ዓመት የምናመሰግንበት እና አዲሱን ዓመት በፍቅርና በተስፋ የምንቀበልበት
ዛሬ የ2018 ዓ.ም አሥራ ሦስተኛዋ ወር ጳጉሜ 1 በመንፈሳዊ በረከት እና በእሁድ ዕለት እረፍት ተጀምራለች። ጳጉሜ ያለፈውን ዓመት የምናመሰግንበት እና አዲሱን ዓመት በፍቅርና በተስፋ የምንቀበልበት የሽግግር ጊዜያችን ናት። ይህች ዕለት ለሁላችሁም የሰላም፣ የጤና እና የደስታ ይሁንላችሁ! መልካም የጳጉሜ 1 እሁድ ይሁንልን!

አርቲስት ኤደን ሽመልስ ከኮሜዲያን አንድነት አያሌው ከተላከላት የሽምግልና ጥያቄ «እሺ» ማለቷ ተገለጸ። በርካታ ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት የሽምግልና ሥርዓቱ በደስታ የተፈጸመ ሲሆን፣ ለጥንዶቹ ያማ
አርቲስት ኤደን ሽመልስ ከኮሜዲያን አንድነት አያሌው ከተላከላት የሽምግልና ጥያቄ «እሺ» ማለቷ ተገለጸ። በርካታ ታዋቂ አርቲስቶች በተገኙበት የሽምግልና ሥርዓቱ በደስታ የተፈጸመ ሲሆን፣ ለጥንዶቹ ያማረ የፍቅርና የትዳር ዘመን ተመኝተናል። (ፎቶ፦ Chere Wedding Photographer)

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 "ሸማ ተራ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ያጋጠመው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ። የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ስጋት አመራር ኮሚሽን
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 "ሸማ ተራ" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ያጋጠመው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ። የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ስጋት አመራር ኮሚሽን ባለሙያዎች ከስፍራው ነዋሪዎች ጋር በመቀናጀት አደጋውን በፍጥነት ለመቆጣጠር ችለዋል። በአሁኑ ወቅት የአደጋው መንስኤ እና የደረሰው ቁሳዊ ጉዳት መጠን በባለሙያዎች እየተጣራ ይገኛል።

በዓለም ዙሪያ ሲጠበቅ የቆየው 75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World 2026) ፍጻሜ አግኝቶ የዶሚኒካን ሪፐብሊክ ተወዳዳሪ የአሸናፊነቱን ዘውድ ተቀናጅታለች። በውድድሩ የስፔን ተወዳዳሪ 2
በዓለም ዙሪያ ሲጠበቅ የቆየው 75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World 2026) ፍጻሜ አግኝቶ የዶሚኒካን ሪፐብሊክ ተወዳዳሪ የአሸናፊነቱን ዘውድ ተቀናጅታለች። በውድድሩ የስፔን ተወዳዳሪ 2ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ የማሌዢያ ተወዳዳሪ ደግሞ 3ኛ ደረጃን በማግኘት አጠናቀዋል። በሕዝብ ድምፅ አሸንፋ ወደ Top 6 ያለፈችው የኤርትራ ተወካይ እና የደቡብ አፍሪካ ተወዳዳሪ ድንቅ የውድድር ጊዜን አሳልፈዋል።

በ75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World 2026) ወደ Top 6 ማለፍ የቻሉ የመጨረሻዎቹ ሀገራት ዝርዝር ይፋ ሆኗል። በዚህም መሰረት ኤርትራ፣ ማሌዢያ፣ ቬትናም፣ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ፣ ስፔ
በ75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World 2026) ወደ Top 6 ማለፍ የቻሉ የመጨረሻዎቹ ሀገራት ዝርዝር ይፋ ሆኗል። በዚህም መሰረት ኤርትራ፣ ማሌዢያ፣ ቬትናም፣ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ፣ ስፔን እና ደቡብ አፍሪካ ወደ መጨረሻው ዙር አልፈዋል። የኤርትራ ተወካይ በከፍተኛ የህዝብ ድምፅ (People's Choice Vote) አሸናፊ በመሆን ቀጥታ ወደ Top 6 መግባት የቻለች ሲሆን፣ ከስድስቱ ምርጥ ተወዳዳሪዎች መካከል ሁለቱ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው።

በ75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World 2026) ኢትዮጵያን ወክላ የተሳተፈችው ሩት ይርጋለም ወደ Top 40 ሳታልፍ የቀረች ሲሆን የውድድር ጉዞዋም በዚህ አብቅቷል። በሌላ በኩል የኤርት
በ75ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር (Miss World 2026) ኢትዮጵያን ወክላ የተሳተፈችው ሩት ይርጋለም ወደ Top 40 ሳታልፍ የቀረች ሲሆን የውድድር ጉዞዋም በዚህ አብቅቷል። በሌላ በኩል የኤርትራዋ ተወዳዳሪ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችላለች። ሩት ሀገሯን ወክላ ላሳየችው ድንቅ ብቃት፣ ባህልን የማስተዋወቅ ጥረት እና ላስመዘገበችው ስኬት ትልቅ ምስጋና ይገባታል።

ተወዳጁ በጎ አድራጊ ማስተር አብነት ለማህበረሰቡ እያከናወነ ለሚገኘው የበጎ አድራጎት ሥራ ዕውቅና የሚሰጥ የክብር ዲፕሎማ ከዳማት ሆቴልና ቢዝነስ ኮሌጅ ተበርክቶለታል። ይህ ዕውቅና በበጎ አድራጎት ዘ
ተወዳጁ በጎ አድራጊ ማስተር አብነት ለማህበረሰቡ እያከናወነ ለሚገኘው የበጎ አድራጎት ሥራ ዕውቅና የሚሰጥ የክብር ዲፕሎማ ከዳማት ሆቴልና ቢዝነስ ኮሌጅ ተበርክቶለታል። ይህ ዕውቅና በበጎ አድራጎት ዘርፍ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ የሞራል ጥንካሬ እንደሚሆነው ማስተር አብነት ገልጿል። ሽልማቱ ላለፉት ዓመታት ላከናወናቸው ተግባራት የተሰጠው ሁለተኛው ከፍተኛ ዕውቅና ሲሆን፣ የደግነት ሥራው ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግሯል።

ዛሬ ነሐሴ 30 ቀን 2018 በቬትናም በሚካሄደው 73ኛው የሚስ ወርልድ (Miss World 2026) የፍጻሜ ውድድር ላይ ሩት ይርጋለም ኢትዮጵያን ወክላ ወደ መድረክ ትወጣለች። ባለፈው ዓመት ሐሴት የ
ዛሬ ነሐሴ 30 ቀን 2018 በቬትናም በሚካሄደው 73ኛው የሚስ ወርልድ (Miss World 2026) የፍጻሜ ውድድር ላይ ሩት ይርጋለም ኢትዮጵያን ወክላ ወደ መድረክ ትወጣለች። ባለፈው ዓመት ሐሴት የ'ሚስ ወርልድ አፍሪካ'ን ዘውድ በመቀናጀት ታሪክ መስራቷ የሚታወስ ሲሆን፣ ዛሬ ደግሞ ሩት ያንን ታሪካዊ ድል ለመድገም ዝግጁ ሆናለች። የፍጻሜ ውድድሩ በቀጥታ ስርጭት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚ አስተላለፍ ይሆናል።

ተመድ የአፍሪካን እውነተኛ ስፋት የሚያሳይ አዲስ የዓለም ካርታ አጸደቀ! የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ለዘመናት የአፍሪካን የቆዳ ስፋት አሳንሶ ሲያሳይ የቆየውን የካርታ አሰራር የሚቀይ
ተመድ የአፍሪካን እውነተኛ ስፋት የሚያሳይ አዲስ የዓለም ካርታ አጸደቀ! የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ለዘመናት የአፍሪካን የቆዳ ስፋት አሳንሶ ሲያሳይ የቆየውን የካርታ አሰራር የሚቀይር ታሪካዊ ውሳኔ በ164 ሀገራት ድጋፍ አጽድቋል። በውሳኔው መሰረት፦ - አፍሪካ ከግሪንላንድ በ14 እጥፍ እንደምትበልጥ የሚያሳየው ትክክለኛ ካርታ ተግባራዊ ይደረጋል - በትምህርት ቤቶች፣ በመገናኛ ብዙሃን እና በዲጂታል መተግበሪያዎች ጥቅም ላይ እንዲውል ጥሪ ቀርቧል ይህ እርምጃ የታሪክና የስነ-ልቦና እይታን የሚያስተካክል ትልቅ ድል መሆኑ ተገልጿል።

የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር አልጄሪያ ለዜጎቿ የዘረጋችው አስደናቂ የማህበራዊ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመላው አፍሪካ ከፍተኛ አድናቆትን እያተረፈ ይገኛል። ሀገሪቱ ስራ ለሌላቸው ወጣቶች ስራ እስኪያገ
የሰሜን አፍሪካዋ ሀገር አልጄሪያ ለዜጎቿ የዘረጋችው አስደናቂ የማህበራዊ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመላው አፍሪካ ከፍተኛ አድናቆትን እያተረፈ ይገኛል። ሀገሪቱ ስራ ለሌላቸው ወጣቶች ስራ እስኪያገኙ ድረስ በወር 96 ዶላር ድጋፍ እና ነፃ የጤና መድህን አገልግሎት መስጠት ጀምራለች። በተጨማሪም አነስተኛ የደመወዝ ወለልን ወደ 170 ዶላር ከፍ ያደረገች ሲሆን፣ በወር ከ 216 ዶላር በታች የሚያገኙ ዜጎች ምንም አይነት የገቢ ግብር እንዳይከፍሉ አድርጋለች። በተጨማሪም አልጄሪያ ግዙፍ የሃይል አቅሟን በመጠቀም ለ 100 በመቶ ዜጎቿ ነፃ እና ተራሽ የሆነ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ማድረስ ችላለች።

በስራ ቦታዎ ወይም በመኖሪያ ቤትዎ ለረጅም ሰአታት መቀመጥ ለጤናዎ ከፍተኛ አደጋ እንደሚያስከትል ያውቃሉ? በቢሮ ውስጥ የሚሰሩ፣ በኮምፒውተር የሚሰሩ ወይም በታክሲና በባስ ረጅም መንገድ የሚጓዙ በርካ
በስራ ቦታዎ ወይም በመኖሪያ ቤትዎ ለረጅም ሰአታት መቀመጥ ለጤናዎ ከፍተኛ አደጋ እንደሚያስከትል ያውቃሉ? በቢሮ ውስጥ የሚሰሩ፣ በኮምፒውተር የሚሰሩ ወይም በታክሲና በባስ ረጅም መንገድ የሚጓዙ በርካታ ኢትዮጵያውያን በቀን እስከ 15 ሰአታት በመቀመጥ ያሳልፋሉ። ይህ ረጅም ሰአት ተቀምጦ ማሳለፍ ለልብ ህመም፣ ለስኳር፣ ለወገብ ህመም እና ለአእምሮ ድካም በሽታዎች እንደሚያጋልጥ ጥናቶች ያመለክታሉ። ከስራ በኋላ እንቅስቃሴ ማድረግ እንኳን የረጅም ሰአት መቀመጥ የሚያመጣውን ጉዳት ሙሉ በሙሉ ሊከላከለው አይችልም። ጉዳቱን ለመቀነስ በየ 30 ደቂቃው ወይም በየ 2 ሰአቱ ተነስተው ለ 3 ደቂቃ ያህል መንቀሳቀስ ይመከራል። ከአሳንሰር ይልቅ ደረጃዎችን መጠቀም፣ በምሳ ሰአት ጥቂት ደቂቃ በእግር መጓዝ እና የሻይ እረፍቶችን በመጠቀም አካልን ማነቃቃት ለጤናችን ትልቅ ለውጥ ያመጣል።

በሰላም ወደ አዲስ አበባ የተመለሰችው ህፃን ፊዮና ሰለሞን፣ በአዲስ አበባ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ በቤተሰቦቿ እና በወዳጅ ዘመዶቿ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላታል። የህፃኗ እናት ወ/ሮ ሄለን ልጃቸውን
በሰላም ወደ አዲስ አበባ የተመለሰችው ህፃን ፊዮና ሰለሞን፣ በአዲስ አበባ ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ በቤተሰቦቿ እና በወዳጅ ዘመዶቿ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላታል። የህፃኗ እናት ወ/ሮ ሄለን ልጃቸውን በሰላም በማግኘታቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው፣ ፍለጋውን ባከናወኑት የፖሊስ አባላትና የፀጥታ አካላት ላይ ያላቸውን አክብሮትና ምስጋና አቅርበዋል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ፖሊስ ረዳት ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ፣ ወላጆች ለልጆቻቸው ደህንነት ልዩ ትኩረትና ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል። (ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ)