en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Students' Union

Open in Telegram

This is official , Ethiopian Higher Education Institutions Students' Union channel. Right info will be posted here. "we serve students!"

Show more
4 873
Subscribers
-324 hours
-117 days
-4730 days
Posts Archive
#Urgent በራያ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በሚዛን ቴፒ እና በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመድባችሁ የተመረቃችሁ ተማሪዎች ስልክ ቁጥራችሁ ስለተፈለገ እ
+1
#Urgent በራያ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በሚዛን ቴፒ እና በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተመድባችሁ የተመረቃችሁ ተማሪዎች ስልክ ቁጥራችሁ ስለተፈለገ እስከ ጥቅምት 16/2016 ዓ.ም ድረስ በተከታዮቹ ስልክ ቁጥሮች 0920478530 / 0914750148 ላይ በመደወል እንድታስመዘግቡ ራያ ዩኒቨርሲቲ አሳስቧል። (ዩኒቨርሲቲው ያወጣው የተማሪዎች ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።) @tikvahuniversity

#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጄና አማካኝነት ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ደብዳቤ በ2016
+1
#MoE የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በአካዳሚክ ጉዳዮች ዋና ሾል አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጄና አማካኝነት ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው ደብዳቤ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ ለሚሰጠው የመውጫ ፈተና ዝግጅት ለማድረግ እንዲቻል ለፈተናው የሚቀመጡ ተማሪዎች መረጃ በአስቸኳይ እንዲላክለት ጠይቋል። ሚኒስቴሩ ፤ ተቋማት መረጃው እጅግ ቢዘገይ እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲልኩ ያሳሰበ ሲሆን የማያሳውቅ ዩኒቨርሲቲ " ተፈታኝ ተማሪ የለውም " በሚል ተይዞ የሚታቀድ መሆኑን በጥብቅ አስገንዝቧል። በ2015 ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰጠው የመውጫ ፈተና በመንግስት ተቋማት ለፈተናው ከተቀመጡት 77,981 ተማሪዎች ውስጥ 50 እና ከዚያ በላይ በማምጣት ያለፉት 48,632 ተማሪዎች ወይም 62.37 በመቶ መሆናቸው አይዘነጋም። በግል ተቋማት ደግሞ ለፈተና ከተቀመጡት 72,203 ተማሪዎች ውስጥ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተው ያለፉት 12,422 ተማሪዎች ወይም 17.2 በመቶ ብቻ ነበሩ። በድምሩ ከአጠቃላይ 150,184 የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ፈተናውን ያለፉት 61,054 ብቻ ወይም 40.65 በመቶ ናቸው። የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና አስተዳደር መመሪያ እንደሚያሳየው ከሆነ ፈተናው በዓመት ሁለት ጊዜ ይሰጣል። የመጀመሪያው በአመቱ መጨረሻ ሲሆን ሁለተኛ በአመቱ አጋማሽ ነው። የመጀመሪያውን የመውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች በዚህ አመት አጋማሽ ላይ በሚዘጋጀው ሌላ ፈተና መፈተን የሚችሉ ሲሆን ከዚህ ቀደም ትምህርት ሚኒስቴር  ተፈታኞች ዳግም ፈተና ለመውሰድ መጀመሪያ ሲማሩበት ወደነበረበት ተቋም መሄድ ሳይጠበቅባቸው ባሉበት አካባቢ ባሉ ተቋማት ፈተናውን እንደሚወስዱ የሚደረግበት ስርዓት እንደሚዘረጋ መግለፁ አይዘነጋም (በዚህ ጉዳይ ወደፊት የሚወጣ መረጃ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን)። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ፣ ተመራማሪና ተጋባዥ መምህር የሆኑት ፕ/ር ገቢሳ ኤጀታ የአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል። ፕ/ር ገቢሳ ሽልማታቸውን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እጅ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ፣ ተመራማሪና ተጋባዥ መምህር የሆኑት ፕ/ር ገቢሳ ኤጀታ የአሜሪካ ብሔራዊ የሳይንስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል። ፕ/ር ገቢሳ ሽልማታቸውን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እጅ ተቀብለዋል። በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ዘርፍ እጅግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ የአሜሪካ ዜጎች በሚሰጠው በዚህ ሽልማት 19 ሰዎች የተካተቱ ሲሆን የፐርድ ዩኒቨርሲቲ ባልደረባው ፕ/ር ጋቢሳ አንዱ ሆነዋል። ፕ/ር ጋቢሳን ለሽልማቱ ያበቃቸው በከፍተኛ የምርምር ሥራቸው የእፅዋት ዘረመል ምህንድስና በመጠቀም በረሃማ የአየር ንብረትና ነፍሳትን የሚቋቋሙ የአዝርዕት ዘሮችን በማግኘታቸው እና በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ ዋስትና ለማረጋግጥ ያደረጉት አበርክቶ መሆኑ ተገልጿል። ፕ/ር ገቢሳ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ባከናወኗቸው የምርምር ሥራዎች የዝናብ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች በአነስተኛ እርጥበት በአጭር ጊዜ ብዙ ምርት የሚሰጡ የማሽላ ዝርያዎችን በማውጣት ለአርሶ አደሮች እንዲደርስ በማድረግ አስተዋፅዖ አበርክተዋል። በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለአየር ንብረት ተስማሚ የግብርና ቴክኖሎጂና የብዝሀ ህይወት ጥበቃ የአፍሪካ የልህቀት ማዕከል እንዲቋቋም ከፍቸኛ አስተዋፅዖ ማድረጋቸው ከዩኒቨርሲቲው የተገኘ መረጃ ያሳያል። የዓለም ሎሬት ፕ/ር ገቢሳ ኤጄታ በምግብ ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ከዚህ በፊት ከዓለም የምግብ ፕሮግራም ሽልማት የተበረከተላቸው መሆኑ ይታወቃል። የአርሶ አደሮችን ህይወት ለመቀየር በኢትዮጵያ ውስጥ ላበረከቱት አስተዋፅዖ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት እንዳበረከተላቸው ይታወሳል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
#GAT የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። " 62 እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ / 80 ፐርሰንታይል ያገኙ በሚፈልጉበት ተቋም ገብተው መማር ይችላሉ " የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች
+1
#GAT የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። " 62 እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ / 80 ፐርሰንታይል ያገኙ በሚፈልጉበት ተቋም ገብተው መማር ይችላሉ " የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ የአገራዊ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (National GAT) የመቁረጫ ነጥብ አሳውቋል። በዚህም መሠረት ፤ አጠቃላይ ከተፈተኑት ጥያቄዎች ውስጥ 62 (50%) እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ ወይም 80 ፐርሰንታይል (80 Percentile) ያገኙ ተፈታኞች #ብቻ ለመማር በሚፈልጉበት ተቋም አመልክተው መማር የሚችሉ እንደሆነ ተገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመልካቾች ለማመልከት ሲመጡ ውጤታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus በመግባት እና የተማሪውን የመግቢያ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) በመጠቀም ማረጋገጥ ይቻላሉ ተብሏል። * ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከላይ ተያያዘውን ደብዳቤ ከትምህርት ሚኒስቴር አመራር ማረጋገጡ በዚሁ አጋጣሚ ያሳውቃል። @tikvahuniversity

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለትም
+1
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዓሉ ከፈጣሪ ረድኤት በረከት የሚገኝበት የደስታ፣ የሰላም እና የጤና እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልፃል። በአሁን ወቅት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለምትገኙ በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ ተማሪዎች፣ የተማሪ ህብረት አመራሮችና አባላት መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ አብዝተን እንመኛለን።        ✝✝ መልካም የመስቀል በዓል ✝✝   @EHEISUOfficialChannell

እንኳን ለ1ሺህ 498ኛው የነብዩ መሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላም አደረሳችሁ! ********************* የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ት
እንኳን ለ1ሺህ 498ኛው የነብዩ መሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) በሰላም አደረሳችሁ! ********************* የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም በዓሉን ለምታከብሩ የእስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ እያለ በዓሉ ከፈጣሪ እዝነት የሚገኝበት የሰላም፣ የጤና እና የበረካ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልፃል። በአሁን ወቅት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለምትገኙ በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ ተማሪዎች፣ የተማሪ ህብረት አመራሮችና አባላት መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ አብዝተን እንመኛለን።          â˜Şď¸áˆ˜áˆáŠŤáˆ በዓል!!!🔯   @EHEISUOfficialChannell

. 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 እንኳን ለ2016 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት
+2
.      🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼       áŠĽáŠ•áŠłáŠ• ለ2016 ዓ.ም አዲስ ዓመት                   በሰላም አደረሳችሁ!        🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን በሙሉ አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የደስታ፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የበረከት፣ የእርቅ፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ፣ ሰላም የሚሰፍንበት፣ የጦርነት ዜናዎችን የማንሰማበት የመማር ማስተማር ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ ሆኔታ የሚፈፀምበት ብሎም ውቢቷ ሀገራችን ኢትዮጵያ የሀዘን ጊዜዋ አብቅቶ መልካም መፃይ እድሏ የሚረጋገጥበት እንዲሁም ያቀዳችሁትን ሁሉ የምታሳኩበት፤ የስኬት፣ የውጤት እና የሙላት ዘመን እንዲሆንላችሁ ከልብ ይመኛል። በአሁኑ ወቅት በአንዳንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመማር ላይ ያላችሁ የጤና ተማሪዎች፣ ባለፉት አመታት በጦርነት ምክንያት ከት/ት ገበታች ተለይታችሁ የነበራችሁ እንዲሁም ሌሎች á‰ á‹“ሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ ተማሪዎች፣ የተማሪ ህብረት አመራሮችና አባላት መልካም አዲስ ዘመን እንዲሆንላችሁ አብዝተን እንመኛለን።                   đŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒť              መልካም አዲስ አመት!!!        đŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒť @EHEISUOfficialChannell

.      🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼    áŠĽáŠ•áŠłáŠ• ለ2016 ዓ.ም አዲስ ዓመት               በሰላም አደረሳችሁ!        🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ ለትምህርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን በሙሉ አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የደስታ፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የበረከት፣ የእርቅ፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ፣ ሰላም የሚሰፍንበት፣ የጦርነት ዜናዎችን የማንሰማበት የመማር ማስተማር ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊ በሆነ ሆኔታ የሚፈፀምበት ብሎም ውቢቷ ሀገራችን ኢትዮጵያ የሀዘን ጊዜዋ አብቅቶ መልካም መፃይ እድሏ የሚረጋገጥበት እንዲሁም ያቀዳችሁትን ሁሉ የምታሳኩበት፤ የስኬት፣ የውጤት እና የሙላት ዘመን እንዲሆንላችሁ ከልብ ይመኛል። በአሁኑ ወቅት በአንዳንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመማር ላይ ያላችሁ የጤና ተማሪዎች፣ ባለፉት አመታት በጦርነት ምክንያት ከት/ት ገበታች ተለይታችሁ የነበራችሁ እንዲሁም ሌሎች በዓሉን ከቤተሰቦቻችሁ ርቃችሁ ለምታከብሩ ተማሪዎች፣ የተማሪ ህብረት አመራሮችና አባላት መልካም አዲስ ዘመን እንዲሆንላችሁ አብዝተን እንመኛለን።                   đŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒť              መልካም አዲስ አመት!!!        đŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒťđŸŒť @EHEISUOfficialChannell

Repost from Tikvah-University
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ በመኪና አደጋ ለተጎዱ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች አድርጓል፡፡ የዩኒቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎች ከሚቀርብላቸው ምግብ በመ
+2
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ በመኪና አደጋ ለተጎዱ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች አድርጓል፡፡  የዩኒቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎች ከሚቀርብላቸው ምግብ በመቀነስ ብር 1,274,324.96 በመኪና አደጋ ለተጎዱ የተቋሙ ሰራተኞች ድጋፍ አድርገዋል። በሌላ በኩል በአዲስ አበባ የባሌ ተወላጆች መረዳጃ ማህበር በመኪና አደጋው ለተጎዱ ወገኖች የ500 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል። ዩኒቨርሲቲው ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በመኪና አደጋ ለተጎዱ ሰራተኞቹ ማሰባሰቡን ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል። @tikvahuniversity

Repost from Tikvah-University
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ በመኪና አደጋ ለተጎዱ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች አድርጓል፡፡ የዩኒቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎች ከሚቀርብላቸው ምግብ በመ
+2
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ከ1.2 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ በመኪና አደጋ ለተጎዱ የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች አድርጓል፡፡  የዩኒቨርሲቲው መደበኛ ተማሪዎች ከሚቀርብላቸው ምግብ በመቀነስ ብር 1,274,324.96 በመኪና አደጋ ለተጎዱ የተቋሙ ሰራተኞች ድጋፍ አድርገዋል። በሌላ በኩል በአዲስ አበባ የባሌ ተወላጆች መረዳጃ ማህበር በመኪና አደጋው ለተጎዱ ወገኖች የ500 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል። ዩኒቨርሲቲው ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በመኪና አደጋ ለተጎዱ ሰራተኞቹ ማሰባሰቡን ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል። @tikvahuniversity

ከምርቃት እና የምረቃ መርሀግብር ተሳትፎ ጋር በተገናኘ በቅርቡ የኢት/ከፍ/ት/ተቋ/ተ/ህብረት መግለጫ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መግለጫ ከምርቃት ፕሮግራም ጋር በተያያዘ የተነሳውን ሀሳብ በተመለ
ከምርቃት እና የምረቃ መርሀግብር ተሳትፎ ጋር በተገናኘ በቅርቡ የኢት/ከፍ/ት/ተቋ/ተ/ህብረት መግለጫ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መግለጫ ከምርቃት ፕሮግራም ጋር በተያያዘ የተነሳውን ሀሳብ በተመለከተ ማስተካከያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል። በመሆኑም ሁሉም ተማሪ ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃውን ከማግኘቱ አስቀድሞ የመውጫ ፈተናን ማለፍ የሚጠበቅበት ሲሆን የምርቃት መርሀ-ግብር ተሳትፎን በተመለከተ በተቋማት ሴኔት ብቻ የሚወሰን መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ሀምሌ 05/2015 ዓ.ም አዲስ አበባ

ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የተሰጠ መግለጫ በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁ ማሟላት የሚጠበቅባችሁን አሟልታችሁ ለዚህ ለበቃችሁ ውድ እጩ ምሩቃን እና ክቡራን የምሩቃን ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በዚህ አመት በሁሉም የትምህርት ክፍሎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና፤ ተመራቂ ተማሪዎች ያላቸውን ብቃት ለመለካት የተዘጋጀ እና ለት/ት ጥራት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ቢሆንም የነበሩ ክፍተቶችን እና በቅድሚያ መሟላት የነበረባቸው ሁኔታዎችን በዝርዝር በማስቀመጥ ቢያንስ ቁጥራቸው በዛ ያሉ ተመራቂዎች በሚገኙባቸው የት/ት ፕሮግራሞች በዚህ አመት እንዲጀመር አልያም በሙከራ ደረጃ እንዲሰጥ ያላሳለሰ ጥረት አድርገናል። ሆኖም የት/ት ጥራትን ለማምጣት በሁሉም የት/ት ክፍሎች እንዲጀመር በመወሰኑ፤ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት በትግበራው ተማሪው ተጎጂ እንዳይሆን እያደረግን ቆይተናል። በቅርቡ በተሰጡት የመለማመጃ እና የሙከራ ፈተናዎች ወቅት የነበሩ ክፍተቶችን ከየዩኒቨርሲቲው የተማሪ ህብረቶች በመሰብሰብ እና በዋናው ፈተና ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በመለየት እንዲስተካከሉ ለት/ት ሚኒስቴር ከወዲሁ አሳውቀናል። በተጨማሪም ምርቃት እና የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ከት/ት ሚኒስቴር ጋር በነበረን ቅድመ ውይይት የምረቃ መርሀ-ግብር ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎችን በተመለከት ዩኒቨርሲቲዎች የቀደመ አሰራራቸውን መከተል እንደሚችሉ ስምምነት ላይ ደርሰን የነበረ ቢሆንም፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ “የመውጫ ፈተናን ያላለፉ ተማሪዎች የምርቃት ፕሮግራም ላይ አይሳተፉም” በማለት በድንገት አሳውቆ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ውሳኔው ከተገለፀበት እለት ጀምሮ እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ጉዳዩ አግባብነት የሌለው፣ በህግ ለተቋማት ሴኔት በተሰጠ ስልጣን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያለ አግባብ ጣልቃ መግባቱን እንዲሁም ውሳኔው ከ4-7 አመታት የተማረው ተማሪን ብቻ ሳይሆን የሀገር መሰረት የሆነውን ቤተሰብንም ጭምር የሚጎዳ፤ ለት/ት ጥራቱም ምንም ፋይዳ የሌለው መሆኑን በመግለፅ በተደጋጋሚ ውይይት ያደረግን ሲሆን በዚህም መሰረት ት/ት ሚኒስቴር በግብታዊነት ያስተላለፈውን ውሳኔ በማሻሻል ወደቀድሞ ሀሳብ ተመልሷል። ለዚህም በተመራቂ ተማሪዎች ስም ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምስጋናችንን እናቀርባለን። በዚህም መሰረት በሀገራችን የሚገኙ ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድ/ሁለት ያልተሟላ ውጤት ኖሯቸው ከግማሽ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጤት(CGPA>=2.00) ያላቸውን ተማሪዎች የምርቃት መርሀ-ግብር እንዲሳተፉ አድርገው ሲያሟሉ ዲግሪ የሚሰጡ ሲሆን አሁንም በተመሳሳይ የመውጫ ፈተናውን የማያልፍ ተማሪ ካለ የምርቃት መርሀ-ግብር ላይ በመሳተፍ ለምዘናው ብቁ በሆነ ጊዜ በየሶስት ወሩ በሚሰጠው ፈተና ያለገደብ መመዘን ብሎም ድጋሚ የመፈተን ፍላጎት የሌለው እጩ ምሩቅ በደረጃ ዝቅ ያለ የት/ት ማስረጃ መውሰድ እንደሚችል በመመሪያ ተቀምጧል። በመሆኑም ውድ እጩ ምሩቃን በምርቃት መርሀ-ግብር ዙሪያ ሲነሱ የነበሩ ነገሮችን ታግሳችሁ ከሚመለከታቸው አካላት መልስ እስኪሰጥ በትግስት ስለጠበቃችሁ ምስጋናችንን እያቀረብን ጥያቄያችን መልስ አግኝቶ ሁሉም ተመራቂ ተማሪ የምርቃት መርሀ-ግብር ላይ የሚሳተፍ በመሆኑን እንገልፃለን። በተያያዘም የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በትምህርት ማስረጃቸው ላይ ከ100 ያመጡት ውጤት የሚገለፀው በጊዜያዊው ማስረጃቸው(Tempo) ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ማለትም የወጪ መጋራታቸውን ከፍለው ሲያጠናቅቁ በሚሰጣቸው፤ የወሰዱትን የት/ት አይነቶች ከነውጤታቸው በሚያሳየው ማስረጃ ላይ መሆኑን እየገለፅን መንግስት አዲስ ቅጥር ማቆሙን ካሳወቀ 2 አመታት ያለፉ ቢሆንም በግሉ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በመንግስት መስሪያ ቤቶችም የተለያዩ አዲስ ቅጥሮች ሲፈፀሙ የቆዩ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። በመጨረሻም ክቡራን እጩ ምሩቃን፦ 1) የምትፈተኑበት ኮምፒውተር ፈተና ከመጀመሩ በፊት ሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ፈትሻችሁ እንድትቀመጡ፤ 2) ፈተናውን በምትሰሩበት ወቅት የኮምፒውተር ገመዶች በሰውነታችሁም ሆነ በሌላ ነገሮች እንዳይነኩ እና እንዳይቋረጡ ጥንቃቄ እንድታደርጉ፤ 3) ወደ መፈተኛ ክፍሎች ስትገቡ እና ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ መመሪያዎችን እንድታከብሩ፤ 4) ምዘናው በበይነመረብ የሚሰጥ እንደመሆኑ በፈተናው ወቅት ችግሮች ካጋጠሙም ወድያው መፍታት ስለሚቻል እንከን ሲያጋጥማችሁ በየመፈተኛ አዳራሹ ለተመደቡ የአይሲቲ ባለሙያዎች በፍጥነት እንድታሳውቁ እንዲሁም የሚያጋጥሟችሁን የትኛውም ተግዳሮቶች በግቢያቹ ላለው ህብረታችሁ በማመልከት ከግቢው ከአቅም በላይ ከሆነ በእኛ በኩል በሚመለከተው አካል እንዲፈታ የምናደርግ መሆኑን እየገለፅን በቅርቡ በተሰጠው የሙከራ ፈተና ልክ በመዘጋጀት ያለምንም ፍርሀት እና ጭንቀት የፈተና ስነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ እንድትፈተኑ አደራ እያልን መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ስም አብዝተን እንመኛለን። መልካም እድል! የኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት @EHEISUOfficialChannell

የመውጫ ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት የሚኖሩ ዲስፕሊንና የምንከተለው ፕሮቶኮል👆 ©ት/ት ሚኒስቴር

@ማስታወቂያ የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ረሜዲያል ተጠቃሚ ተማሪዎች ፈተና ትናንት ሰኔ 26/2015 ዓ.ም በዩኒቨርስቲዎች መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል። ይሁን እንጂ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክን
@ማስታወቂያ የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ረሜዲያል ተጠቃሚ ተማሪዎች ፈተና ትናንት ሰኔ 26/2015 ዓ.ም በዩኒቨርስቲዎች መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል። ይሁን እንጂ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር የሚከተሉትን ውሳኔዎች ያሳለፈ መሆኑን እንገልጻለን። 1) ሰኔ 26/2015 የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ 2)ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ተሻሽሎ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ ካምፓስ ያላቸውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈተና ቀርቶ ወደ ፊት በሚወሰን አግባብ ፈተናው በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም እንዲሰጥ 3)በመንግስት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑትን ተማሪዎች በተያዘው ፕሮግራም መሰረት የሚሰጥ መሆኑን እንገልጻለን። የትምህርት ሚኒስቴር!