cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ትንሳኤ ዘኢትኤል መማሪያ

የአባቶቻችን እና የሀገራችን ታሪክና ጥበብ ግዕዝን, ስለጥንት ነገስታት ታሪክ፣ ስለዕፆች፣ መድሀኒቶች፣ መሰውሮች፣ የደመና ጥበብ ፣ቅርሶች፣ጥንታዊ የብራና መፅሐፍት፣ስነ ፈለክ ፣አክሲማሮስ፣ራዕየ ሳቤላ፣መፅሐፈ ጅማትርያ ፣መፅሐፈ ፓዝዮን፣መፅሐፈ ፀሐይ፣መፅሐፈ ልሳን፣መፅሐፈ ጥበብ፣የመላእክት ቋንቋ ወዘተ ... ለጓደኛ ያስተላልፉ ኢትኤልን ስለመረጣቹ አመሰግናለሁ ይቆየን.. 👳‍♂

Show more
Advertising posts
6 701
Subscribers
-124 hours
-197 days
-8330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሰላም ለሁላችሁም ይሁን ውድ የትንሳኤ ዘኢትኤል መማማሪያ ተከታታዮች ወዳጆቼ የማከብራችሁ እንደምን አላችሁ ብርሀነ ልደቱን በሰላም አሳልፈን ፆሙን በበረከት በረድኤት ጎብኝቶን ለብርሀነ ትንሳኤው ደግሞ እንደቸርነቱ አድርሶናልና የአምላካችን የመድሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ የተመሰገነ ይሁን በእውነት እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን በአሉ የሰላም የጤና የመደጋገፍ የመረዳዳት ይሁንላችሁ ።በፆሙም ከፆሙም ውጪ ቅር የተሰኛችሁብኝ ያስቀየምኋችሁ ሁሉ ይቅር እንድትሉኝ እናንተም ያስቀየማችሁትን ይቅር በሉ ያጠፋውትን ክሳለሁ በፀሎት አስቡኝ እግዚአብሔር አምላክ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን
Show all...
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ #አዝ ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ ማርና ወተትን ለሚመግበው ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው #አዝ አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም #አዝ እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ ሊቀ-መዘምራን ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
ዓርብ ዘጠኝ ሰዓት በዚህች ዕለት በዚህች ሰዓት የዓለም መድኃኒት ጌታችን ኢየሱስ ለአዳም ልጆች ድኅነት በመስቀል ላይ ሆኖ በታላቅ ድምፅ ጮሆ “ኤሎሄ ኤሎሄ” ብሎ “ሁሉ ተፈጸመ” በማለት በባሕርይው ሞት የሌለበት አምላክ ነፍሱን በፈቃዱ ለሞት አሳልፎ ሰጠ። “ቀትር በሆነ ጊዜም በስድስት ሰዓት ፀሐይ ጨለመ፤ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስም ዓለም ሁሉ ጨለማ ሆነ። ፀሐዩም በጨለመ ጊዜ የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከመካከሉ ተቀደደ። ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ድምፁን ከፍ አድርጎ፥ “አባት ሆይ፥ ነፍሴን በአንተ እጅ አደራ እሰጣለሁ”’ ብሎ ጮኸ፤ ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።” (ሉቃ.፳፫÷፵፬-፵፮)
Show all...
ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ አይሁድ አማጽያን ሰቀሉህ ወይ  የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ ሰቀሉህ ወይ /2/  የአዳም በደል አደረሰህ አንተን ለመሰቀል  የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት/2/ አዝ ንጹሕ ክርስቶስ ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለእኛ  መሰቀል አሸክመው አስረው ገፈፉህ እያዳፉህ/2/  አዝ እጅና እግርህን በብረት ተመታ የዓለም ጌታ  የሾህ አክሊል ደፍተህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ/2/ አዝ ግብዞች እንደራሳቸው መስሏቸው  ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ/2/ አዝ  በመሰቀል ላይ ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል  ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው/2/ አዝ ይቅር ባይ ግልጽ በደላችንን ሁሉ ሳታይ  አንተ ይቅር በለን በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/  💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
"ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።" (የሉቃስ ወንጌል 23:46) "ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።" (የማቴዎስ ወንጌል 27:50) "ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።" (የማርቆስ ወንጌል 15:37) "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።" (የዮሐንስ ወንጌል 19:30) 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
ንሴብሖ ንሴብሖ /2/ ለእግዚአብሔር /2/  ስቡሐ ዘተሰብሐ /4  እናመስግነው /2/ እግዚአብሔርን /2/  ምስጉን ነው የተመሰገነ /4/  ባህሩን ተሻግረን ወንዙ ደረቅ ሆነ በጠላታችን ላይ ድሉ የኛ ሆነ ከባርነት ቀንበር ፍፁም ነፃ ወጣን ህይወት የሚሰጠን መና ነው ምግባችን አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር ጉልበታችን ቢዝል መከራም ቢበዛ ሃይላችን ጌታ ነው የዓለም ቤዛ ከአለት ላይ ውሃ ፈልቆ እንደጠጣነው ይህን ታላቅ አምላክ ኑ እናመስግነው ሰዎች ደስ ይበለን ሕይወታችን ድኗል ሰይጣን ጠላታችን አፍሮ ተመልሷል አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር ጉልበታችን ቢዝል ፈተናው ቢበዛ ሃይላችን ጌታ ነው የዓለሙ ቤዛ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺