cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ትንሳኤ ዘኢትኤል መማሪያ

የአባቶቻችን እና የሀገራችን ታሪክና ጥበብ ግዕዝን, ስለጥንት ነገስታት ታሪክ፣ ስለዕፆች፣ መድሀኒቶች፣ መሰውሮች፣ የደመና ጥበብ ፣ቅርሶች፣ጥንታዊ የብራና መፅሐፍት፣ስነ ፈለክ ፣አክሲማሮስ፣ራዕየ ሳቤላ፣መፅሐፈ ጅማትርያ ፣መፅሐፈ ፓዝዮን፣መፅሐፈ ፀሐይ፣መፅሐፈ ልሳን፣መፅሐፈ ጥበብ፣የመላእክት ቋንቋ ወዘተ ... ለጓደኛ ያስተላልፉ ኢትኤልን ስለመረጣቹ አመሰግናለሁ ይቆየን.. 👳‍♂

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
6 700
المشتركون
-124 ساعات
-197 أيام
-8330 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ሰላም ለሁላችሁም ይሁን ውድ የትንሳኤ ዘኢትኤል መማማሪያ ተከታታዮች ወዳጆቼ የማከብራችሁ እንደምን አላችሁ ብርሀነ ልደቱን በሰላም አሳልፈን ፆሙን በበረከት በረድኤት ጎብኝቶን ለብርሀነ ትንሳኤው ደግሞ እንደቸርነቱ አድርሶናልና የአምላካችን የመድሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ የተመሰገነ ይሁን በእውነት እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን በአሉ የሰላም የጤና የመደጋገፍ የመረዳዳት ይሁንላችሁ ።በፆሙም ከፆሙም ውጪ ቅር የተሰኛችሁብኝ ያስቀየምኋችሁ ሁሉ ይቅር እንድትሉኝ እናንተም ያስቀየማችሁትን ይቅር በሉ ያጠፋውትን ክሳለሁ በፀሎት አስቡኝ እግዚአብሔር አምላክ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን
إظهار الكل...
​​​​👉 ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት 1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ (ማቴ 27፡46) 2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው (ሉቃ 23፡34) 3. ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር እንድትኖር በእውነት እነግርሃለሁ (ሉቃ 23፡43) 4. እነሆ ልጅሽ አነኋት እናትህ (ዮሐ 19፡26-27) 5. ተጠማሁ (ዮሐ 19፡28) 6. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ (ሉቃ 23፡46) 7. የተጻፈው ሁሉ ደረሰ ተፈጸመ አለ (ዮሐ 19፡30) 👉 ሰባቱ ተዐምራት ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት 1. ፀሐይ ጨልሟል 2. ጨረቃ ደም ሆነ 3. ከዋክብት ረገፉ 4. ዐለቶች ተሠነጠቁ 5. መቃብራት ተከፈቱ 6. ሙታን ተነሡ 7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ 👉 አምስቱ ችንካሮች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ችንካሮች 1. ሳዶር ፦ በሚባል ችንካር ቀኝ እጁን ቸነከሩት 2. አላዶር ፦ በሚባል ችንካር ግራ እጁን ቸነከሩት 3. ዳናት ፦ በሚባል ችንካር ሁለት እግሩን ቸነከሩት 4. አዴራ ፦ በሚባል ችንካር ማሀል ልቡን ቸነከሩት 5. ሮዳስ ፦ በሚባል ችንካር ደረቱን ቸነከሩት 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
إظهار الكل...

ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ አይሁድ አማጽያን ሰቀሉህ ወይ  የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ ሰቀሉህ ወይ /2/  የአዳም በደል አደረሰህ አንተን ለመሰቀል  የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት/2/ አዝ ንጹሕ ክርስቶስ ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለእኛ  መሰቀል አሸክመው አስረው ገፈፉህ እያዳፉህ/2/  አዝ እጅና እግርህን በብረት ተመታ የዓለም ጌታ  የሾህ አክሊል ደፍተህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ/2/ አዝ ግብዞች እንደራሳቸው መስሏቸው  ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ/2/ አዝ  በመሰቀል ላይ ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል  ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው/2/ አዝ ይቅር ባይ ግልጽ በደላችንን ሁሉ ሳታይ  አንተ ይቅር በለን በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/  💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
إظهار الكل...
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
ክርስቲያኖች ሁላችሁ ኑ እናፅናናት "ክርስቲያን ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናፅናናት፤ በልጇ ስቃይ ሆድ ብሷታልና፥ እንባን ከመጠጧ ጋር አመድንም ከምግቧ ጋር ቀላቅላለችና። የተወደደ ልጇ በመስቀል ተሰቅሎ ስታየው አንድ ጊዜ ከእሾህ አንድ ጊዜ ከድንጋይ ላይ እየወደቀች አለቀሰች። ወንድም የሌለው አንድ ልጇ እንዲህ ሲሰቃይ የወለደ አንጀቷ እንደምን ይቻል? ምንስ ብላ ትፅናና? ያፅናኗት ዘንድ ሊቃነ መልአክት በዙሪያዋ መጡ ግን አልተፅናናችም፤ ልጄ እያለ የሚጠራት አባቷ ዳዊትም መጣ ድንግል ግን እርቃኑን የተሰቀለው ልጇን እያየች መሪር እንባን አፈሰሰች። ስለ ልጇ ብዙ መከራ አሳልፋለች፥ ያሁኑ የልጇ መከራ ግን ከሀዘኖች ሁሉ የከፋ ሆነባት። አንድ ልጇ እየሞተ ምን ብላ ትፅናና ? የእናቱን አለመፅናናት ያየ ጌታ ኢየሱስ ከሃዘን ብዛት እንዳትሞት ያፅናናት ዘንድ ቁጽረ ገፅ ለተባለው ለዮሐንስ እነኋት እናትህ አለው። በእውነት እነኋት እናታችን በልጇ ስቃይ ሆድ ብሷታልና ክርስቲያን ሁላችሁ ኑ እናፅናናት።" 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
إظهار الكل...
"ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።" (የሉቃስ ወንጌል 23:46) "ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።" (የማቴዎስ ወንጌል 27:50) "ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።" (የማርቆስ ወንጌል 15:37) "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።" (የዮሐንስ ወንጌል 19:30) 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
إظهار الكل...
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ #አዝ ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ ማርና ወተትን ለሚመግበው ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው #አዝ አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም #አዝ እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ ሊቀ-መዘምራን ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
إظهار الكل...