en
Feedback
ወኔ እና ቅኔ -(ፈይሠል አሚን)

ወኔ እና ቅኔ -(ፈይሠል አሚን)

Open in Telegram

ሐበሻ ቅኔን ያለ ምክንያት አልፈጠረም፤ በወኔ የማይነገሩ ሐሳቦቹን ሊገልጽበት እንጂ! . ዳገት አቀበቱን በወኔው አለፈ፤ ወኔውን ሲነጥቁት ቅኔ ፈለሰፈ!😉

Show more
7 748
Subscribers
-224 hours
-137 days
-8430 days
Posts Archive
የት ነው? . (#ፈይሠል_አሚን) . አምላክ የት ነው ያለው? ምድር ላይ ወይስ በሰማይ ቤት? ብለው ሲጠይቁኝ.... መልስ አለ እኔ ዘንድ በፅኑ የማምነው ጊዜና ሥፍራ ድቅድቅና ብራ ምንም ሳይቀይረው ምንም ሳይወስነው "አምላክ ከኔ ጋር ነው!" . @huluezih @huluezih

የመሐል ሰው . (#ፈይሠል_አሚን) . መንገድ ነን ለአንዳንዱ. . . ወደ አሻው እስኪደርስ፣የሚጠለልበት፤ ከህመሙ እስኪሽር የሚጋደምበት፤ ነደን 'ምናበስለው. . . ከስመን 'ምናበቅለው. . . እኛ ያልጀመርነው፣ እኛ 'ማንጨርሰው፤ መሐሉ ነን ለአንዳንዱ ሰው! ክንፍ እስኪያቆጠቁጥ ከርሞ መዘጋጃ. . . እስኪያሳክከው፣ጥፍሩን መሞረጃ ትያትር ነን ለአንዳንዶች. . . ሕይወትን መልመጃ! . @huluezih @huluezih

እንዲህ ባለ መልኩ ቲክቶክ ላይ ግጥሞቼንና ጽሑፎቼን እየለቀቅኩ ነው:: የሚመቻችሁ መቀላቀል ትችላላችሁ...ሊንኩ እነሆ! https://www.tiktok.com/@huluezih?_r=1&_t=ZS-95G4kqdAgHk

. . .of the day!😎
. . .of the day!😎

ቀጣይ ዓመት ራሴ ላነበው ለራሴ የጻፍኩት (ማንም እንዳያነበው!) . ዕጣ-ፈንታ ዕድሜ ሠጥቶህ ይኽን እንድታነብ ከፈቀደልህ፣ እንደ ለኸድ የጨለመውንና የጠበበውን መንገድ ማለፍህን እንደማትረሳ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ተስፋ መቁረጥ ጥርሱን አግጥጦ የገፋህን ቅጽበት፣ ቀናት ሁሉ በማይገለጥ ሰንኮፍ ተጋርደው አልነጋ ሲሉ፤በአኬልዳማ ተደልድለው መራመጃ የነፈጉህ መንገዶች፤ አቅም ባጣም በሹክሹክታ ‹‹ያልፋሉ!›› ስልህ ከመጣህበት በላይ የምትደርስበትን ጸዳል ጉብታ በከሲታ ተስፋ ውስጥ. . .ተስፋ አድርጌ ነው፡፡ የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ደክሞህ ነበር፡፡ ዕጣ-ፋንታ ጨክኖብህ በሕይወትህ ረግጠህ የማታውቃቸው አዚማም ሥፍራዎች ላይ ቆመሃል፡፡ ፖሊስ ጣቢያ፣ ፍርድ ቤት፣ ወጌሻ ቤት፣ ሐኪም ቤት…ሰው ፊት ሌሎችም፡፡አፈር ልሰህ ወደ ሕልምህ እንዲያቀናህ ያበቀልከውን ፍሬ ሌባ ያለ ኀፍረት ወስዶብሃል፡፡ ድፍረትና ጭስን ተመስለህ በመርፌ ቀዳዳ እንደምትወጣ ፍርሃት በዋጠው ለሆሳስ ነግሬህ ነበር፣ አላሳፈርከኝም…ዛሬ እዚህ ደርሰሃል፡፡ የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ዓለም ተገልብጦብህ ነበር፡፡በደም፣ በሥጋ በመንፈስ የተዛመዱህ ጀርባቸውን እንጂ ፊት አልሠጡህም፡፡የኋላ ታሪክህንና የሚደርስልህ ነገህን ረስተው በቆምክበት ሥፍራ መዝነው አቅልለውሃል፡፡ ይጎትቱኛል ያልካቸው መዳፎች ገፍተው ወደ መቀመቅ እንድትወርድ በይነውብሃል፡፡ ፍርሃት ባደበዘዘው ለሆሳስ ነግሬህ ነበር…..‹‹ያልፋል!›› ብዬ፡፡ የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት…..ደርሶብህ የማያውቀው የመተት ፍላጻ ተወርውሮ ቤትህ ገብቶ ገርበብ ያለ በርህን ዘግቶ፣ ክፍት መስኮትህን ደፍኖ ከሁሉ አራርቆህ፣ የጨበጥከውን ነጥቆ፣ የጎረስከውን አስተፍቶህ ብዙ ቀናትና ወራት ሳይነጉልህ…በድቅድቅ ውስጥ ማንም ሳያይህ ከራስህ ጋር ስትታገል፣ ባልተዘጋጀ ትከሻ ላይ ሲህር ሌላ ሸክም ኾኖ ሲያጎብጥህ፤ ከገጠመህ ይልቅ የሚመጣውን ተዓምር አስቤ ፍርሃት ባደበዘዘው ለሆሳስ ‹‹አይዞህ! ይኽም ያልፋል!›› ብዬህ ነበር፡፡(ይኸው! አለፍከው አይደል?) ‹‹ንገረኝ!›› ሲሉህ እንዴት እንደምትገልፀው ተቸግረህ፣ የምትወደውን ብዕር ጨለማ ውስጥ ጥለህ መናገር ከብዶህ….በዝምታ ከዝምታ ጋር ታግለሃል፡፡ የምትተነፍስበትን ብዕር እንጂ ፈገግታህን እና ጨዋታህን አልጣልክም፡፡ያንኳኳሃቸው በሮች ወቅታቸው ስላልደረሰ እንጂ መከፈታቸው እንደ ቂያማ የማይቀር ቀጠሮ መኾኑን ከሕመሞችህ ልቀው ባይሰ´ሙህም ነግሬህ ነበር፣አላመንከኝም ነበር፡፡ ዛሬ እዚህ ስለደረስክ እኮራብሃለሁ፡፡ ሦስት ነገር አትርሳ….ትንሽ ሻማ ይዘው ጨለማህ ድረስ መጥተው ብርሃናቸውን ያካፈሉህን፣ የተፈጠረው ሳይገባህ፣ የተናገርከው ሳይገባቸው ጆሮ የሠጡህን! ደግሞም ችለው ያልቻሉትን፣ መንገድ መጠቆም ሲችሉ መንገድህን የዘጉትን፣ ጥሩ ቃል እንኳ እንደ መስቀል ወፍ የራቃቸውን፡፡ ሦስተኛ. . .ማን እንደኾንክ አትርሳ፡፡ አሁን ያለህበት ብሩህ ቀን ሲያዘናጋህ ይኽን ጽሑፍ አንብብ፡፡ያለ መሣሪያ ጦርነት ውስጥ ገብተህ የወጣህ፣ ያለ ምሽግ ከፈንጂ ጋር የተጋፈጥክ፣ ራስህን አጥተህ ራስህን ያገኘህ ልበ-ብረት ነህ፡፡ እኮራብሃለሁ! . @huluezih

. . .of the day!😎
. . .of the day!😎

. . .of the day!😎
. . .of the day!😎

. . .of the day!😎
. . .of the day!😎

የእሳት ጠባሳ! . (#ፈይሠል_አሚን) . እሳት ኾንኩ መሰል. . . እንዳልነድ፣እንዳልጠፋ፣ማግዶ እያቆየኝ፤ ከሩቅ የጠራሁት፣በሩቅ ነው የሚያየኝ! . እሳት ኾንኩ መሰል. . . ዝናቡ አባራ፣ ክረምቱም አለፈ፤ ካበሰልኩት ይልቅ. . . ያከሰልኩት ብቻ. . . ለወሬ ተረፈ! . እሳት ኾንኩ መሰል. . . የነደድኩለት ሸሸኝ፣መንገዱን ቀጠለ፣ የነካሁት፤የነካኝ. . .እየተቃጠለ! ሬሳ ትንፋሽ የለው፣አይሞትም አበሳ፤ በገሃድ አያዩትም፣የእሳትን ጠባሳ! . @huluezih @huluezih

. . .of the day!😎 @huluezih
. . .of the day!😎 @huluezih

. . .of the day!😎 . @huluezih
. . .of the day!😎 . @huluezih

ዐውቃለሁ! . ጠፍቼያለሁ። ብዙ ማለት የሚችል ብዕሬ እጄ ላይ ደርቋል። በሕይወት መስመር ላይ ስለምንጋራቸው ነገሮች ልሳን መኾን የለመደ አዕምሮዬ ሐሳብ ማሳለፍ አቅቶታል። "የሐሳብ ቱቦ መጥበብ" እለዋለሁ እኔ! መገኘት ያለብኝን ያክል፣ መጻፍ በምችለው ልክ አይደለሁም! ዐውቃለሁ! . ልቤ ላይ ብዙ ሸክም አለ፣ ምናልባት በጽሑፍ ሊታከም፣ ባይታከም እንኳ ጋብ የሚል ህመም አለ። ለወትሮ እደበቅበት የነበረው ጽሑፍ ከእኔ ተደብቋል። መደበቂያ ያጣ ሰው ወዴት እንደጠፋ በምን ያውቃል? ዐውቃለሁ ይኼ እኔ አይደለሁም! . በጽልመት ፋኖሴ ነበር፣ በማለዳ ስንቄ፣ ጦርነት ላይ ጋሻዬ ኾኗል፣ በሰላሜ ውስጥ ማጌጫዬ! አሁን እንደ ባዕዳ ሩቅ ለሩቅ በትዝብት የምንተያይ እንግዶች ኾንን። ዐውቃለሁ... ስሜት አይሠጥም! . ይኽ ቻናል ዕድሜው ወደ ስምንት ዓመት እየተጠጋ ነው። በነዚህ ዓመታት ውስጥ በብዙ የሕይወት ጉራማይሌ ውስጥ ኾኜ ደስታን፣ኀዘንን፣ ሕመምን፣ትዝታን ናፍቆትንና ሌሎችን የሕይወት አዕማድ ጽፌ ለናንተ አድርሼያለሁ። ደግፋችኋል፣ተቃውማችኋል፣ አስተያየታችሁ ሁሉ ለእኔ ውድ ነበር። . እዚህ ስላላችሁ ላመሠግን ነው አመጣጤ! ከፍታ እና ዝቅታ እንዳለ ሁሉ መንገድ የምንጠፋበት፣ ከራሳችን የምንርቅበት የሕይወት ንፍቀ-ክበብ አለ። ከራሴ የተሰወርኩበት የሕይወቴ ምዕራፍ ላይ ነኝ..ብዙ ወደፊት ምጽፈውን ዛሬ ዐይቼ ዝም እንድል እያስገደደኝ ይኾናል....እየታገልኩ ነው..እየጣርኩ ነው...በቻልኩት አቅሜ ሁሉ ወደ ራሴ እመለሳለሁ በቅርቡ...በጸሎታችሁ አስቡኝ...ሞራል ሁኑኝ! ዐውቃለሁ...የእናንተ ጥሩ ቃላት እኔ ዘንድ ክቡር መኾናቸውን! . (#ፈይሠል_አሚን) . @huluezih

መስከረምን እወዳታለሁ! (7) . (በዓመት አንዴ ብቻ የሚነበበው ታሪክ እነሆ ክፍል 7) . (#ፈይሠል_አሚን) . ሕይወትን እንደአመጣጧ ማስተናገድን ለመልመድ ብዙ ነገሬን ሰውቻለሁ። ልቤን ኮርክሜ አላምጄያለሁ፣ ይሉኝታን ሰብሬ ጥዬ ራሴን አሰልጥኛለሁ። ሲያወሩት እንደሚቀሉ ነገሮች ከባድ እና ውስብስብ ነገር የለም። ልቤን እየሸረፍኩ፣ እምነቴን እያጣሁ፣ ጉጉት ከሕይወቴ እየራቀ...ከነዚህ ጉድለቶች መካከል "ሕይወትን እንደ አመጣጧ" የሚል ፍልስፍና መዝዤ አውጥቼ እየኖርኩት ነው። . መስከረምንም እንደ አመጣጧ እያስተናገድኩ ከረምኩ። ወደ ሞቀበት ስትሮጥ፣ የቀዘቀዘውን ልቤ መግራት እየሞከርኩ፣ ባዶ እጇን ስትቀር ከአፌ እየነጠቅኩ መዳፏ ላይ ያለኝን እያስቀመጥኩ ነበር ዓመቴ የተገባደደው። . ለካ በሕይወት ውስጥ ከሕሊና ወቀሳ መዳኛ መንገድ "አለመጠበቅ"ኖሯል። ሠጥተን ሳንጨርስ የምናገኘውን ምላሽ አዕምሯችን ላይ አኑረን ነው ለህመም ራሳችንን ያጋለጥነው። እንግዲህ ስሠጥ መቀበልን አላስብም፣ ስሸልም ኪሳራን አልፈራም፤ለራሴ ስል፣ለልቤም! . መስከረም ዓመቱን ሙሉ ከዚያ ፓይለት አፍቃሪዋ ጋር ጮቤ ስትረግጥ ነበር የከረመችው። ክረምቱ ላይ ትዳር እንደሚመሠርቱ አውግታኝ ነበር። ገመናን አውጥቼ የምበትን ሰው አልኾንኩም እንጂ ፓይለቷ ፍቅረኛዋ በረራ ላይ ሲኾን እሷም ለጊዜው በፍቅር የምትበርላቸው አላፊ ሰዎች ነበሩ።የሚፈጠረውን ልይ ብዬ አፌን በዝምታ አበስኩ። . ትናንት የሠርግ ጥሪ ደረሰኝ። መስከረም በወርሃ መስከረም ነው የምሞሸረው ብላ ከወዲሁ መጥሪያ ላከችልኝ። ያለፉትን ዓመታት በፍቅሯ ሲሰቃይ እንደከረመ ሰው ልቤ ትንሽ ቅሬታ መቋጠሩ አልቀረም! ግን ደግሞ ሕይወትን እንደአመጣጡ ማስተናገድ ከደሜ ጋር ተዋህዷል፤ "አለመጠበቅ" ሰላም መጠበቂያ መንገድ መኾኑ ተገልጦልኛል። "አበጀሽ" ብዬ ወረቀቱን ተቀበልኩ። . ግራ ያጋባኝ ነገር ግን ቤት ገብቼ ወረቀቱን ማንበብ ስጀምር የምታገባው ፓይለቱን እንዳልኾነ አስተዋልኩ። አፍቃሪዋ በሳምንታት ውስጥ ሥሙን ቀይሮ ነው ወይስ እንደፈራሁት በፍጥነት ተጥዶ በፍጥነት የበሰለ እንጭጭ ፍቅር አልገባኝም። አያገባኝም ብዬ እንዳልደመድም መስከረም እኔ ዘንድ መስከረምነቷ ይደበዝዛል እንጂ ጭራሹኑ አይጠፋም። ደወልኩላት። . እንደፈራሁት በቀናት ትውውቅ ወደ ትዳር የተጣደፈ የአቦሠጥ ውሳኔ ነው። ፓይለቱ አፍቃሪዋ በሥራው ላይ በፈፀመው ተደጋጋሚ የዲሲፕሊን ጥሰት ከሥራ መባረሩን ነግራኝ ከእንግዲህ ያሳለፉት የፍቅር ጊዜያቸው ከሥራው እኩል መክሰሙን አሳወቀችኝ። "ደህና ሥራ አለው፣የተሻለ ነገ ይኖረናል ብዬ እንጂ ሌላ ምን አለው ብዬ መሰለህ የተለጠፍኩበት!" አለች ያቺ ከልጅነቷ የማውቃት መስከረም አፍ አውጥታ!(እሷ ትልቅ ነገር ያላት ይመስል) . አንዳንዴ ፈጣሪ ከመንፈግ ውስጥ ፍቅሩን ይገልጽልኛል። መስከረምን ወድጄ ጨርቅ ለመጣል አንድ ኀሙስ የቀረኝ ጊዜ ታወሰኝ። በግራ ስሔድበት ቀኝ እያመለጠ፣ከላይ ስዘልበት በታች እየሾለከ ከእጄ የወጣው ፍቅሯ ፈጣሪዬ ነበር እንዲያመልጠኝ ሲያግዝ የነበረው። የምወዳት መስከረም ያኔ ፍቅሯን አግኝቼ ቢኾን በክፉ ቀኔ ሰበብ ፈጥሮ እንደሚለየኝ ተገለጠልኝ። ስለ አዲሱ "ፍቅሯ" እየተረከችልኝ ይኽን ሁላ አንሰላስዬ ቀና ብዬ በደመቀው ሰማይ በኩል ለአምላኬ ምስጋናዬን በለሆሳስ ሰደድኩ። . አዲሱ "ፍቅሯ" በከተማችን ከላይ ከተቀመጡ ነጋዴዎች አንዱ ነው። ወደ ሐገር መዓት ነገር ያስገባል፣ ከሐገር የሚወጡ ሐገር በቀል ምርቶችም ብዙዎቹ በእሱ በር በኩል ያልፋሉ።(መስከረም እንደነገረችኝ) . "ታዲያ ነገ የማልቸገርበትን ሕይወት ብኖር አይሻለኝም? እግሬን ሰቅዬ መኖር እየቻልኩ ለምን ትግል ላይ ያለ ሰው ሕይወት ውስጥ እገባለሁ? አማራጭ ባይኖረኝ ፍቅርን መርጬ እሱ እንደኾነው እኾናለሁ...ግን ሕልሜን የማሳካበት፣ሕይወቴን የማቀልበት መንገድ ከታደልኩ ለምን አልጠቀምም? ማንም ሴት ይኽን ዕድል ብታገኝ ትምራለች?" በጥያቄ እያደረገች ውሳኔዋን ገለፀች። . ብዙ ሴቶች ኃብታም መኾኑ እንጂ እጁ ላይ ያለው ኃብት እስከመቼ እንደሚቆይ ከግምት አያስገቡም። የወንድ ድህነቱ እንጂ ወደ ኃብት ማመሰ የሚያንደረድረውን አቅሙንና ተስፋውን አይመዝኑም! ብዙ ኃብታሞች በአንድ ወቅት አንጀቱ የታጠፈ ደሃ ነበሩ። ብዙ እብዶችና ድሆች አንድ ወቅት በታሠረ ብር ንፍጣቸውን የጠረጉ ባለጠጎች ነበሩ። "ነበር" ሁሌም ዛሬ ነው 'ሚጀምረው! . ወስነው ቀጣዩን እርምጃ ለሚነግሩን ሰዎች ምን መልስ ይኖረናል? "አበጀሽ!" አልኳት። . እነሆ ውዷ መስከረም በመስከረም 12 ልትሞሸር ቀጠሮ ይዛለች። ሠርጓን እንደ አመጣጡ ላስተናግድ ግድ ይለኛል። . የዓመት ሰው ይበለን! ምርጥ ዓመት ለሁላችንም! . @huluezih @huluezih

of the day!😎
of the day!😎

የፈራሁት! . (#ፈይሠል_አሚን) . ኦና ለታቀፈ፣ጊዜ ለሰበረው፤ ከተቸረው ሁሉ፣ቅንጣትም ላልቀረው፤ ተስፋ ነው 'ሚገድለው. . . ተስፋ ነው 'ሚያኖረው! . የእኔም ጥያቄ ነው. . . በዚህ ጨለማ ውስጥ፣ ልቤ እየበረታ፣ በተስፋ እያስመኘኝ፤ እንጃ ለምን ይኾን?! የፈራሁት ብቻ ነው ደጋግሞ 'ሚያገኘኝ!! . @huluezih @huluezih

የማለዳ ማስታወሻ #157 . ሔጄ ተመለስኩ። የሔድኩት ወደ 'ማይደሰስ፣ ወደ 'ማይታይ እና ወደ 'ማይጨበጥ ስሜታዊ ሁኔታ ነው። የማላውቀውን የራሴን ስብዕና ዐይቼ ራሴን ያደነቅኩበት፣ ራሴን የጠላሁበት ደግሞ "አገኘሁት" ብዬ የማስበውን ማንነቴን እንደ ጭስ የበተንኩበት ሁኔታ ውስጥ ነው ሔጄ የተመለስኩት። . መማር ከፈለግክ ከሕይወት የተሻለ መምህር የለም። "እንዲህ ዓይነት ሰው ነኝ!" ብለህ ስለ ራስህ እርግጠኛ የኾንክበት እምነትህ የሚናድበት ቀን ይመጣል። አሁን የምታውቀው ማንነትህን ያወቅከው እዚህ ስለኾንክ ብቻ ነው። የነገው ማንነትህ ሕይወት ነገ በምታደርስህ ቦታ እና ሁኔታ ላይ ይወሰ'ናል። . የዛሬው ማንነቴን ትናንት እንደ ነብይ ተንብያችሁ ብትነግሩኝ ኖሮ አላምናችሁም ነበር። "ፈጽሞ አላደርግም!" ያልኩትን አድርጌያለሁ፣ "ብሞት አልኾንም!" ስል የከረምኩትን ኾኜያለሁ። ከሕይወት ገጾች አይገመቴነቷ ይስበኛል። . "ማምለጫ" ብለህ የዘለቅከው በር ወህኒ ቤትህ ኾኖ ይገኛል፣ መሻገሪያ ያልከው "ጀልባ" መስጠሚያህ ይኾናል። ሕይወት የገባህ ቀን በበሩም በጀልባውም አትፈርድም። ያንተም ጥፋት አታደርገውም። ሕይወትን የምታይበት አንፃር(Angle) ያንተ ምርጫ አይደለም። ሕይወት ፐውዛ ያስቀመጠችህ ቦታ ነው ዕይታህን የሚመርጥልህ! . ይልቅ ስሕተትንና መዘዘኛ አጋጣሚን የሕይወት አንድ አካል አድርገህ ተቀብለህ ከሌላኛው ጫፍ ለመነሣት ትሞክራለህ። "ረዥም ዕድሜ እኖራለሁ!" ብለህ እያሰብክ ለውሳኔህ አትዘግይ...ማንም አይኖርልህም፣ ማንም አይሞትልህም....ታዲያ ለምን ሥርዓት፣ ሰዎች አልያም ሆድህ ይወስንልሃል? (ማንምም አይወስንልህ!) . (#ፈይሠል_አሚን) . @huluezih @huluezih

. . . Of the week🙄
. . . Of the week🙄

. . . of the day!😎
. . . of the day!😎