en
Feedback
ከቃሉ ማዕድ

ከቃሉ ማዕድ

Open in Telegram

☀️ ክርስቶስን መስለን በመኖር ፣ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በመፀለይ ፣ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ የሚፈልገውን እግዚአብሔርን የሙጥኝ የምንልበት ቻነል ነው። 1ጢሞ 2:1-4 ☀️ ደግሞም አብ የሰጠንን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በልተን ደግሞም ጠትተን ዕለት ዕለት ደግሞ 💥በሁለንተናችን የሚያሳድገንን የቃሉን🎯 ማዕድ የምንቆርስበት ትምህርታዊ እና መንፈሳዊ ቤት ነው። ዮሐ6:35

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
322
Subscribers
No data24 hours
+67 days
+6630 days
Posts Archive
#ቅድምያ_ላልተደረሱት! በትንሹ 3,200,000,000 በላይ የሆነ ሰው ኢየሱስን እንደማያውቅ ያውቃሉ???
#ቅድምያ_ላልተደረሱት! በትንሹ 3,200,000,000 በላይ የሆነ ሰው ኢየሱስን እንደማያውቅ ያውቃሉ???

"ሰው በሁለት አይነት መንገድ ራሱን ሊያታልል ይችላል ፤ አንደኛው እውነት ያልሆነውን ነገር በማመን ሲሆን ፤ ሁለተኛው ደግሞ እውነት የሆነውን ነገር ለማመን አሻፈረኝ ብሎ ሲል ነው።" ሶረን ኪርከጋርድ
የዮሐንስ ወንጌል ፩:፲፪ --- ፲፪፤ ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤
@kekalu_Maid

🧬 እንደ ጸጋ እንጂ እንደ ደሞዝ ያልተሰጠ ክፍያ፥ 🧬 ይገባኛል የሌለበት ኩራት፥ 🧬 ተወድጃለው የሚቀድምበት መውደድ፥ 🧬 ለጽድቅ የመገዛት ነጻነት፣ 🧬 እደርሳለው የሚያስብል ጸጋ፥ 🧬 ተፈጥሮአችን ስም ቢሰጠው "ፍቅር የሌላቸው" የተባልንበትን እድፋም ማንነት፥ ቀዳሹ ከእኛው ወገን ሆኖ፥ በነገር ሁሉ ተፈትኖ #ፍቅርን_ሲተገብር፥ በመንፈሱ ማህተም የእግዚአብሔር ናችሁ ተብለን #ለእግዚአብሔር_የተቀደስንበት ሕይወት
ቤተክርስትያን ውስጥ ብዙ ዘመን ስንቆይ በሚሰጠን የአባትነት ማእረግ የማይጣፋ ማእረግ #ልጅነት
እንደ ልጅ #መጠየቅ እንደ ልጅ #መውደድ እንደ ልጅ #መኖር እንደ ልጅ #መመላለስ እንደ ልጅ #መነጋገር... #እንዳልበሰለ_ህጻን_ሳይሆን፥ #እንደተወደደ_ልጅ መኖር ይሁንልን!!!
“እንግዲህ #እንደ_ተወደዱ_ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥”   — ኤፌሶን 5፥1
ውለታም እኮ ምላሽ አለው! ግን ምን ጎሎት ምን እንሰጠዋለን??? ባሳየን መስመር ከመጓዝ ውጪ ደስታም ምላሽም #የለም!!! ✍ #Mesay 📝 ¶Join | Follow | Share 🚩 @Kekalu_Maid

            💢ኢየሱስም  'እኔ' ፧፦
> እኔ ከላይ ነኝ  ዮሐንስ 8፥23
 
> የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ  ዮሐንስ 10፥36
> የዓለም ብርሃን ነኝ።  ዮሐንስ 9፥5
> እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።  ዮሐንስ 14፥6
> የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምን ሁል ጊዜ ከቶ አይጠማም።  ዮሐንስ 6፥35
> በሩ እኔ ነኝ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል...  ዮሐንስ 10፥9
ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል።  ዮሐንስ 11፥25
> መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ።  ዮሐንስ 13፥13
> እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤  ዮሐንስ 15፥1
> አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ....  ራእይ 1፥8
> ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ....  ራእይ 1፥17
💥 ሕይወት ለማግኘት ከፈለጉ ኢየሱስ በመስቀል ላይ እንደሞተና እንደተነሳ በልብዎ ያምኑ ጌታም እንደሆነ በአንደበትዎ ይመስክሩ።  📌 <<ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።>> ሮሜ 10፥10 #የኢየሱስ_እኔዎች #ከቃሉ_ማዕድ Join | follow | share @kekalu_Maid ══════════════☦☦☦═════════════

የአብርሃም ዕምነት ክፍል 1 || ስለ እውነት......ሙሉ ቪዲዮውን በዩትዩብ ገፃችን ያገኙታል 👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/D_aYjQZBgyE Follow TESFA on Faceboo
የአብርሃም ዕምነት ክፍል 1 || ስለ እውነት......ሙሉ ቪዲዮውን በዩትዩብ ገፃችን ያገኙታል 👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/D_aYjQZBgyE Follow TESFA on Facebook | Tik tok | Telegram | Instagram

🔆 በቅርቡ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በጋራ መፀለይ እንጀምራለን። 📌ዝግጁ ናችሁ???
Anonymous voting

👉 አፋር ህዝብ የካም (የኖህ ልጅ) ዘሮች እንደሆነ ይናገራሉ። በምስራቅ አፍሪካ ጅቡቲ፣ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ውስጥ ይገኛሉ። "ደናኪል" የሚለው የዐረብኛ ቃል ለነሱ ጥሩ ስሜት የሚሰጥ ቃል ስላልሆነ አፋር መባልን ይመርጣሉ። የሰውን ጥንካሬ እና ጀግንነት በማጉላት ኩሩ ህዝብ ነው። 👉 አብዛኛው አፋር በጎች፣ ፍየሎች፣ ከብቶች እና ግመሎቻቸውን እየጠበቁ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ናቸው። የሰው ሀብት የሚለካው በመንጋው መጠን ነው። ነገር ግን ሁሉም አፋሮች እረኞች አይደሉም። በደናኪል ዲፕሬሽን ውስጥ የሚሰሩት ብዙዎቹ በደረቅ ወቅት ጠንካራ የጨው ድንጋዮችን ይጭናሉ፣ ጥቅም ላይ ለመዋል  ዝግጁ የሆነ ጨው በድፍድፍ ብሎኮች ያቀርባሉ። ይህ የዕለት ተዕለት ህይወታቸው የሆኑ ሰዎች ቤተክርስትያን የመታደም ሆነ  የማየትም እድልን አያገኙም። 💥 አፋሮች ከጥቂት ፐርሰንት በስተቀር ሙስሊም የሚኖርበት  ስፍራ ነው ፣ እስልምና በባህልና ማንነታቸው ላይ ጠለቅ ያለ ስፍራ የሚሰጠው ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ እና አዳኝ አድረጎ ለማየት የልባቸው አይኖች ይከፈቱ ዘንድ እንጸልይ (2ኛ ቆሮንቶስ 3፡14-16)። 💥 መንፈስ ቅዱስ በህልም እና በራዕይ በሀይል እንዲንቀሳቀስ እንለምነው፣ እራሱን ለአፋር ወንዶች፣ ሴቶች  ልጆች በሚረዱት መንገድ ይገልጣል፣ ልክ እንደ ቆርኔሌዎስና ጴጥሮስ። ለመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት እንጸልይ!
“ልባቸው እንዲጸናና፥ በፍቅርም ተባብረው በማስተዋል ወደሚገኝበት ወደ መረዳት ባለ ጠግነት ሁሉ እንዲደርሱ የእግዚአብሔርንም ምሥጢር እርሱንም ክርስቶስን እንዲያውቁ እጋደላለሁ።”   — ወደ ቆላስይስ 2፥2
👇👇👇👇👇👇👇👇👇 🔆 በቅርቡ ላልተደረሱት የሕዝብ ክፍሎች በጋራ መፀለይ እንጀምራለን። 📌ዝግጁ ናችሁ??? 👇👇👇👇👇👇 🔅 VOTE ያድርጉ!🙏 #ቅድሚያ_ላልተደረሱት #ከቃሉ_ማዕድ Join | follow | share @kekalu_Maid

photo content

🔆 እርሱ (ኢየሱስ ክርስቶስ)፦ 📌 መላእክት 👉 መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና  ሉቃስ 2፥11 📌 ጠቢባን 👉 ልንሰግድለት መጥተናል  ማቴዎስ 2፥2 📌 እግዚአብሔር 👉 በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት  ማቴዎስ 17፥5  📌 ማርያም 👉 የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ ዮሐንስ 2፥2 📌 ነቢያት 👉 በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት ይቀበላል። የሐዋርያት ሥራ 10፥43 📌 ሰይጣን 👉 አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ  ማርቆስ 3፥11 📌 መጽሐፍ ቅዱስ 👉 ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው።  1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15 📌ሐዋርያት👉 በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም  ሮሜ 10፥11 እርስዎስ ለሕይወትዎ ዋስትና ወዴት ይጠጋሉ? ማንንስ ይመርጣሉ? 
ምርጫዎትን ያስተካክሉ ከትናንት ስህተት ተምረው ነገ የማይፀፀቱበትን ውሳኔ ዛሬ ይወስኑ!!!
💥 ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ዘላለምም ያው ነው። ዕብራውያን 13፥8 #የክርስቶስ_ማንነት #ከቃሉ_ማዕድ

እነዚህ “የእግዚአብሔር ክብር ባለጠግነት” ምንድን ናቸው? በኃጢአተኛ ተፈጥሮ፣ በሥጋ ምኞትና በዚህ ዓለም አስጨናቂ ኃይላት ላይ እንዲበረቱ ወይም "በመንፈሱ በኃይል እንዲበረቱ ነው።" ይህ የሚሆነው በእግዚአብሔር መንፈስ ነው። ነገር ግን ሰዎች በእግዚአብሔር መንፈስ የሚበረቱትና የሚጸኑት እንዴት ነው? "ክርስቶስ በውስጣዊ ሰው ውስጥ በማደሩ" ነው ይላሉ:: ክርስቶስ በነፍሳችን ውስጥ መኖር ሲጀምር ሰዎች በመንፈስ በኃይል ይበረታሉ። በዚህ መንገድ የጥላቻ ተፈጥሮ ያለው ነገር ሁሉ ይባረራል። - ጋይየስ ማሪየስ ቪክቶሪነስ የቀድሞ የቤተክርስቲያን አባት📌 @kekalu_Maid

#ክርስቶስን_በእምነት_በልብ_ማኖር ወደ ኤፌሶን ሰዎች ፫:፲፬-፲፰ ------------------ ፲፬፤ ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ ፲፮፤ በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ፲፰፤ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ። ▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿ 🎯 በዚህ ክፍል ላይ የተጠቀሰልን በኤፌሶን ደብዳቤ ሁለተኛው የጳውሎስ ፀሎት ሲሆን...የመጀመሪያውን ፀሎት፦ ኤፌ 1:15-21 ላይ እናገኘዋለን። እንግዲህ ሐዋርያው ጳውሎስ በመልዕክታቱ፦ 💥በቆላስይስ ፪፡፪ 👉 እጋደላለሁ 💥በገላትያ ፬:፲፱ 👉 ምጥ ይዞኛል 💥ወደ ሮሜ ሰዎች ፩:፱ 👉 ሳላቋርጥ አሳስባለሁ ... የሚላቸው ቃላት ሁሉ የጳውሎስን ጭንቀት አመልካች ቃላት ሳይሆኑ እርሱ በእግዚአብሔር ፊት ምን ያህል በፀሎት እንደሚጋደል እና ዘወትር የሚያሳስበው የአማኞች ጉዳይ እነደሆነ አመልካች ነው። ፪ ቆሮ ፩፩፡፪፰ 📌 ሐዋርያው ጳውሎስ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 18 ላይ የቆሮንቶስን አገልግሎት ጨርሶ ወደ ኤፌሶን በምዕራፍ 19 ላይ ይመጣል። 👉ከግሪክ(Greek) ወደ እስያ(Minor-Asia) ማለት ነው። 📌በዚያም የመጥመቁ ዮሐንስን ደቀመዛሙርት አገኘ ፤ መንፈስ ቅዱስን ተቀብላችኋል? ሲላቸው "ማነው?" አልተቀበልንም ቢሉት ጳውሎስም "እጁን ጫነባቸው" ➔ "ሁሉም ተቀበሉ " ➔ "በልዩ ልዩ ቋንቋ ተናገሩ ፣ አንዳንዶቹ ትንቢትን ተናገሩ" 📌 በየዕለቱ!!! 2 አመት ከ 3 ሳምንት ያህል ቁጭ አድረጎ አስተማራቸው። 🔅 ኤጻፍራ የተማረው እዚሁ ነበር። የሚያምነውን ልጁን ጢሞቴዎስን የዚች ቤተክርስቲያን መጋቢ አድርጎ ሲሾመው እንመለከታለን። 📌 ከጥቂት አመታት በኃላ ሮም እስር ቤት እያለ በ 60 ዓ.ም እያለ ነው ይህንን ደብዳቤ የፃፈው። 📌የኤፌሶን ቤተከርስቲያን አማኞች ሐዋሪያ ሳይሆኑ ነን የሚሉትን ለይተው ያውቃሉ! ራዕ ፪:፪ ኤፌሶን 3:14-21 ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ 💥የጳውሎስ መንበርከክ አንገብጋቢ የሆነ ጉደይ እንዳለ አመልካች ነው። ለምሳሌ፦ ሙሴ፣ ዕዝራ፣ ዳንኤል ፣ ሕዝቅኤል ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በጌቴሴማኒ ፣ መግደላዊት ማርያም ተንበርክከው መፀለያቸውን እንመለከታለን። 📌በሮም ማመርታይን በሚባል እስር እስር ቤት "Dungeon" በሚባል ከመሬት በታች በሆነ ቀዝቃዛ ጉዱጓድ ውሰጥ መንበርከክ እንኳ ለአንድ መከራ ለጠገበ ሰው ለብርቱ ሰው እንኳ በጣም አሰቸጋሪ በሆነበት ጳውሎስ ግን ከነ-ሰንሰለቱ(ኤፌ 6:19-20) እንዲንበረከክ ያደረገው ምንድነው? ✨ "ራሰ በራ ፣ እግሩ እንደ ደጋ ሰው እግር የነበረ" ደማስቆ ብሎ መናገር ሲጀምር የመነካቱ ልክ በነገስታት ፊት ቆሞ መናገርን እግዚአብሔር ድፍረትን ያገኘ አገልጋይ እንዲህ ሲል ተናገረ፦ 🎯 16-17 በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ 🔆 "ክርስቶስን በልባችሁ በእምነት እንዲኖር" ማለት ዘላቂና ቀጣይነት ያለውን ህብረት ማለትም ፦ 👉በመከራ 👉በጭንቀት 👉በስደት 👉በራብ 👉በራቁትነት 👉በፍርሃት 👉በሰይፍ 👉ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን 👉መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን የማችል ሆኖ መጣበቅራስን መካድና መስቀልን ተሸክሞ መከተል ማለት ክርስቶስን በልብ በእምነት ማኖር ነው።❤️‍🔥 ይቀጥላል•••••❣ 〰〰〰〰〰〰ከ⃠ቃ⃠ሉ⃠ማ⃠ዕ⃠ድ⃠〰〰〰〰〰〰 #ክርስቶስን_በእምነት_በልብ_ማኖር Join | follow | share @kekalu_Maid

╭ከ╮╭ቃ╮╭ሉ╮◂▸╭ማ╮╭ዕ╮╭ድ╮ ▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿▵▿▵▿▵▿▿▵▿▵▿ "አመንዝራዋ ላይ ድንጋይ መወርወር መቻል በሰዎች ዘንድ ያስጨበጭብልን ይሆናል እንጂ፣ በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አያሰጠንም።" እነእንትና ከምስባኩ ሳይርቁ ከእግዚአብሔር ልብ ስለራቁ፥ #በእነርሱ_የውድቀት_ጥልቀት_የተከደነችውን_የኛን #የጓዳ_እሾህ ማን ባወጣልን?😭 ጉድፋቸውን ማየት ችለናል ማለት የእኛ አይን ውስጥ ግንድ የለም ማለት አይደለም!!! ትንኝ ሲውጡ😞 ማየት ያልተሳነው ዓይናችን ምናለ እኛው ግመል ስንውጥ ወቅሶ በመለሰን😭😭!!! 👉አንዳንዶቻችን ደግሞ ተደፍተን እየተንከባለልን ንስሀ በገባንበት ውድቀት ሌላው ሲገኝ፣ መንከባለሉስ ይቅር፥ ቆመን እንኳን ማረው አላልንም፤ ይልቅስ እኛን የማረን ጌታ ለዚያ ሰው ዲን ቢያወርድበት ተመኘን እንጂ።
"የኛ ስራ መውደድ፣ የመንፈስ ቅዱስ ስራ መለወጥ፣ መፍረድ ደግሞ የእግዚአብሔር ስራ ነው!" ቢሊ ግራሃም
👉ባደግኩባት ከተማ ማቅናት ያልመራው ምክር ከቤተክርስቲያን ያራቃቸውን ብዙ ልጆች አይቻለሁ ያልታወቀባቸው ኃጢአተኞች በታወቁት ኃጢአተኞች ላይ የሚቀስሩት ጣት ቤተክርስትያንን የግብዞች መናኸሪያ አድርጓታል። ኃጢአተኛን እያጨበጨቡ ማበረታታትም ሆነ በዝምታ መተው፥ ሁለቱም ኃጢአት ናቸው፤ ትልቁ ኃጢአት ግን የሰውን ድካም በማጉላት የራስን ውድቀት ለመሸፈን መሯሯጥ ነው! 📌እስቲ ወደ ራሳችን እንመልከት! ጌታ ሆይ ማረን!! ✍ #Mesay 📝 ¶Join | Follow | Share 🚩 @Kekalu_Maid

#ከቃሉ_ማዕድ Join|Follow|Share¶ @Kekalu_Maid https://youtu.be/N1KpDViHk0w?is=v4-qxQJxd6QSJb5f

❤🎼Our favorite Hymns🎬❤ 📌 #ፊትህን_አሰሻለሁ መንገድህን አስተምረኝ የቀናውን ጎዳና ህይወቴም እንዲታደስ በቃልህ እንድጸና ነፍሴ የምትፈልገው ሁልጊዜም ምለምነው በመገኘትህ ውስጥ መኖር ክብርህንም ማየት ነው ነፍሴ የምትፈልገው ሁልጊዜም ምለምነው እንደቃልህም መኖር አንተን ደስ ማሰኘት ነው ፊትህን አሻለሁ | 2x | ፊትህን እፈልጋለሁ ሃይልህን አሻለሁ | 2x | ሃይልህን እፈልጋለሁ ፊቴን ፈለጉ ባልህ ጊዜ ነፍሴ ፊትህን አሻለሁ አለች ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ ቃልህን በልቦናዬ አኖራለሁ #ከቃሉ_ማዕድ  @Kekalu_Maid https://youtu.be/h6EYiXgqgaQ?si=GyzsXHQh_IHUP_P9

መዝሙር 103:4-5
📌" ሕይወታችንን ከጥፋት የሚያድናት፥ በምሕረቱና በቸርነቱ የሚከልለን፥ ምኞታችንን ከበረከቱ የሚያጠግባት፥ ጕልማስነታችንን እንደ ንስር ያድሳል።" 🙌ብሩህ ቀን ይሁንላችሁ❣ #ከቃሉ_ማዕድ
ጌታ ቢፈቅድ እና ብንኖር በቀጣይ በአዳዲስ አርዕስቶች እንገናኛለን...