Usmanic Islamic psychology/ ስለ ሰው ልቡና
Open in Telegram
በኢስላማዊ ሳይኮሎጂስት ኡስማን ሙስጠፋ የተመሠረተ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የሙስሊሞች የስነልቦና ህክምና The Virtual Center for Usmanic Islamic Psychology was founded by Usman Mustofa, a psychology student, researcher in Islamic psychology, and writer ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @usmanoman ላይ ያናግሩን።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
585
Subscribers
+1124 hours
+577 days
+19030 days
Posts Archive
#1 ሽልማት የሚያስገኝ ጥያቄ
ደስታ ብለን ሀዘን ካልን ድህነት ብለን
A.ብልፅግና
B.ሀብት
C.መትረፍረፍ
የ 780 ሜ.ባ የኢንተርኔት ፖኬጅ ሽልማት የሚከተለውን ጥያቄ ቀድሞ ለመለሰ
#ከኡስማኒክ_ኢስላሚክ_ሳይኮሎጂ
The final test of freedom is this: can u remain the same person praise, in insult, in gain, and in loss
"ታላቁ የነፃነት ፈተና በአድናቆት በመሰደብ በማጣት ፣ በማግኘት እና በማጣት አንተ ያው መሆን ትችላለህ ወይ? የሚለው ነው።"
አገጋሚነት/ Resiliency
"በመከራዎች ሰርጥ ውስጥ አልፈዋል። ጥልቅ ህመም እና መከራ በሳቸው ላይ ተነባብሮ ሄዷል። ፈተና ረሀብ እና ተቀባይነትን ማጣት መገፋት እና ውድቀት ለሳቸው የነገ ሻማቸውን የሚለኩሱበት የማገገም ሀይላቸው እንጂ ተሽመድምደው የሚወድቁበት ጋሬጣቸው አይደለም።
ጠንክረው አገግመው ይነሳሉ መውደቃቸው የሚበረቱበት ፅናት ነው ትግላቸው ዳግም ህያው የሚያደርጋቸው ብርሀን ነው።
በመሰበራቸው ባህር ውስጥ የፅናታቸውን መርከብ ሰርተዋል። በመውደቃቸው ረጅም መንገድ የማይፈርስን ድልድይ ገንብተዋል"
(ገፅ 32 'ፍፁም ሰው ፍፁም ነቢይ' መፅሀፍ ከ ነቢዩ ስነ ባህሪያት የተወሰደ (ፀሀፊ ኡስማን ሙስጠፋ )
ይህ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ስነልቦናዊ የፅናት ተምሳሌትነት ነው። እኛም ጥንካሬን ከሳቸው እንማር ወድቆ መነሳትን ተሰብሮ መጠገንን ከአርአያችን እንቅሰም።
የጥያቄ ሶስት መልስ ክፍል 1
በጎ ስራዎችን በልቶ የሚጨርሰው ;የልብ በሽታ'
ምቀኝነት/ሀሰድ - (حسد/envy) -: ኢስላማዊ ፍቺው የተመቀኘነው ሰው ያገኘው ፀጋ
እንዲወገድ መመኘት ማለት ነው።
ሀሰድ/ምቀኝነት ወይም መጥፎ ቅናት ብዙ ሰው የሚፈተንበት የቀልብ/የልብ ህመም አይነት ነው።
ነፍሳችን የታችኛው ደረጃ ላይ ሆና (ነፍሱል - አማራ-) መጥፎ ሀሳቦችን ሳታቋርጥ በምታመነጭበት እርከን ላይ የውስጥ መጥፎ (ውስዋስ) ጉትጎታ እና ደመነፍሳዊ ራስን ያለ ቅጥ የመውደድ ሁሉንም ለራስ ብቻ የመከጀል የተዛባ ውስጣዊ ባህሪ ነው።
ጤናማ ቅናት (Benign Envy):- በሀብት እና በእውቀት ከኛ የተሻለ ሰው ጋር ለመድረስ የሚደረግ ጤናማ ውድድር ልኩን እስካላለፈ ድረስ ለእድገት ይጠቅማል። በሁለት የሰው አይነትም መቅናት እንደሚቻል ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ነግረውናል።
እሱም አላህ ሀብት ሰጥቶት በልኩ በሚለግስ ሰው እና እወቀት ተሰጥቶት በስርአት በሚሰራበት ሰው ነው። ይህ ይቅናት አይነትም ለበጎ ምግባር የሚያነሳሳ ነው።
የቅናታችን ደረጃ ልኩን አልፎ ተንኮልን ሲይዝ ወይም የሌላውን ሰው የፀጋ መወገድ ልባችን ሲከጅል አሁን ስሜታችን ከጤነኛ የቅናት ደረጃ ወደ ምቀኝነት ተሸጋግሯል።
ምቀኝነት ሌላው ትርጉሙ አላህ ለሌላ ሰው የመደበው ፀጋ ለሱ አይገባውም ማለት ስለሆነ ከአላህ ውሳኔ/ቀደር ጋር ያላትማል። ስለዚህ ሂስድ- ተውበት/ንስሐ የሚፈልግ ድብቅ ውስጣዊ የወንጀል አይነት ነው።
ነቢዩ ሙሀመድም (ሰ.ዐ.ወ) ከዚህ ነገር ሲያስጠነቅቁ እንዲህ ብለዋል
– "ምቀኝነትን ተጠንቀቁ እሳት ነገራትን አቃጥሎ እንደሚጨርሰው ምቀኝነትም መልካም ስራን ይበላል"።ብለዋል (አቡዳውድ)
(ይህ ስለ ነገሩ አሳሳቢነት ጥያቄውን እንደመነሻ በመጠቀም የቀረበ የክፍል 1 ማስታወሻ ሲሆን ለእህታችን ጥያቄ ቀጥተኛ ምላሽ በክፍል 2 ምላሽ ላይ ይሰጣል)
ኢንሻአላህ
✍️ ኡስማን ሙስጠፋ ከኡስማኒክ ሳይኮሎጂ።
ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @usmanoman ላይ ያናግሩን።
ሀሰድ/ምቀኝነት ወይም መጥፎ ቅናት ብዙ ሰው የሚፈተንበት የቀልብ ህመም አይነት ነው።
ነፍሳችን የታችኛው ደረጃ ላይ ሆና መጥፎ ሀሳቦችን እና ተግባሮችን ሳታቋርጥ በምታመነጭበት እርከን ላይ
'ብቸኝነት' ማለት ምን አልባት ሁልጊዜ ብቻህን መሆን ማለት ላይሆን ይችላል
ብቸኝነት በሰዎች ተከበህ ማንም ውስጥህን እንዳልተረዳው ሲሰማህ ነው።
ብዙ ጊዜ እኛ ግንኙነትን በመልእክት ቅይይሮች ፣ በተከታይ ብዛት እና በውይይቶች እንለካ ይሆናል
ግን 'መገናኘት' እና 'ግንኙነት' የተለያዩ ነገሮች ናቸው ።
anonymous
ኡስማኒክ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ
ሩህ/መንፈስ
وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الرُّوحِ قُلْ الرُّوحُ مِنْ أَمْرِ رَبِّي ۖ وَمَا أُوتِيتُم مِّنَ الْعِلْمِ إِلَّا قَلِيلًا
ስለ ሩህ (መንፈስ) ይጠይቁሀል። "ሩህ (መንፈስ) ከጌታዬ ነገር ነው ከእውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም" በላቸው
ቁርአን ምዕራፍ 17 አንቀፅ 85
ኡስማኒክ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ
4.ከድህነት እና የሰውን እጅ ከማየት ለመጠበቅ የሚባል ዱአ
▪ اللّهُمَّ أَغْنِنِي بِفَضْلِكَ عَمَّن سِوَاكَ
አላሁመ አግኒኒ ቢፈድሊከ አመን ሲዋክ
"አላህ ሆይ ከአንተ ውጪ ከሆነ አካል ከጃይ/ፈላጊ እንዳልሆን በፀጋህ አብቃቃኝ"
የዚህ ዱአ ስነልቦናዊ እና መንፈሳዊ ጠቀሜታዎች
- ከአላህ ውጪ ካሉ አካላት ከጃይ ከመሆን እንጠበቃለን
- አላህ የፀጋዎቹን በሮች ይከፍትልናል
- ባለን ነገር የመብቃቃትን ትሩፋት እናገኛለን
በመጀመሪያ አባትሽ ባያሳድግሽም ቂም እና ቅያሜ ውስጥ ሳትገቢ ዝምድና ለመቀጠል እና ላለመቁረጥ ያሳየሽው ተነሳሽነት የልብሽ መልካምነት እና አላህን የመፍራት ምልክት በመሆኑ በጣም የሚያስደስት እና ተስፋ የሚሰጥ ነገር ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
ሰዎች ከወላጅ አባት ተለይቶ በማደግ ምክንያት የተለያየ ችግር ውስጥ ሰዎች በሚያልፉበት አለም አንቺ መልካም እንጀራ አባት ማግኘትሽ አላህ መልካም ውለታ እንደዋለልሽ እና እድለኛ እንደሆንሽ ማሳያ ነው።እሳቸውንም ለበጎነታቸው ሳላመሰግን አላልፍም።
ወደ ዋናው ያስጨነቀሽ ጉዳይ ከመዝለቃችን በፊት ከአቅም በላይ በሆነ ጉዳይ ተጠምደን ለመልስ በመዘግየታችን ከልብ ይቅርታ እየጠየቅኩኝ ለጥያቄሽ ቀጥተኛ መልስ እንኳን ባይሆን ሀሳብ እና ማብላያ ይሆናሉ ያልኳቸውን ነጥቦች ልጠቃቅስ ኢንሸአላህ!
ወላጅ አባትሽን ለማወቅ እና ለማዋራት ውስጥሽ ሲነሳ ተፈጥሯዊ ማንነትሽን እና መገኛሽን ለማወቅ ካለሽ ተፈጥሯዊ ራስን የማወቅ ጉጉት የመነጨ መሆኑን ማየት ይቻላል። ሰዎች በተሟላ እና ምንም ባልጎደለበት አካባቢ ውስጥ እንኳን እየኖሩ የስጋ ወላጆቻቸውን ፍለጋ ሲባዝኑ መገኝት የሰው ልጅ ባህሪ ነው።
የወላጆቻችን ሀቅ የሚመነጨው እኛን በማሳደጋቸው ብቻ ሳይሆን በተፈጥሯዊ ወላጅነታቸውም ጭምር ነው። እንጀራ አባትሽ ባይወልደሹም በ አባትነት ስላሳደጉሽ ያለብሽ የውለታ እና የፍቅር እዳ መከበር ያለበት እና በጣም በክብር ሊጠበቅ የሚገባው ዝምድና መሆኑ ግን በአፅንኦት ይሰመርበት።
ወላጅሽን በምትፈልጊበት በዚህ ወቅት የአሳዳጊ አባትሽ ቀልብ እንዳይሰበር እና የመተው እና 'አሳድጌ አሳድጌ' ወደ ወላጇ ሄደች የሚል ችላ የመባል ስሜት እንዳይፈጠርባቸው መጠንቀቅ እና በስነስርዓት ቁጭ ብሎ በመነጋገር አባትሽን ማግኘት እና ዝምድናውንም ማስቀጠል እንደምትፈልጊ የማሳመን ስራ የመስራት ሀላፊነት ይጠብቅሻል።
ወላጅሽን መፈለግሽ የነሱን ውለታ መካድ እና መተው አለመሆኑን በሚረዱት ቋንቋ እና በትህትና ንገርያቸው።እንዲያምኑበት የሚወስደውንም ጊዜ በትእግስት ጠብቂ ለሚፈጠርባቸው ግርታ እና ቅሬታ መሠል ሀዘንም ራስሽን አዘጋጂ።
እናትሽን በተመለከተ የሚፈልገው የማሳመን ሂደት እና ሁኔታ ከአሳዳጊ አባትሽ የተለየ እና ጠንካራ ሊሆን ይችላል። እናትነቷ ፣ በሱ ላይ ያላት ቅሬታ ፣ እና አንቺን ያለአባትሽ ድጋፍ ማሳደጓ ስለ ዚህ ጉዳይ ያላትን የማቅማማት ደረጃ ከፍ ያደርገዋል። ይህም የሚጠበቅ ነው።
ከሁለቱም ጋ የመነጋገሩን እና የማሳመኑን ሂደት በአግባቡ ጨርሰሽ አባትሽን ለማወቅ ግንኙነታችሁንም ለማሳመር ሞክሪ አላህ የመልካም ስራሽን ምንዳ ይከፍልሻል ።ኢንሻአላህ!
✍️ ኡስማን ሙስጠፋ ከኡስማኒክ ሳይኮሎጂ።
ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @psychosman1 ላይ ያናግሩን።
ሩህ?
(እስካሁን ካየናቸው የኢልመ ነፍስ/የኢስላሚክ ሳይኮሎጂ ትምህርት ጥያቄ)
The Mere Exposure Effect
(በብዛት በመጋለጥ ምክንያት መውደድ/መልመድ( የ effecቱ ውጤት መላመድ ነው)
ይህን የስነልቦና ዘዴ የማስታወቂያ ድርጅቶች፣ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዲስቶች ፣ ሀሳብ የሚሸጡ የአለም ሴረኞች ይጠቀሙበታል (በተቃራኒው በጎ ሀሳብን ለመትከልም መዋል የሚችል የስነልቦና ዘዴ መሆኑ አይረሳ!)
ይህ ፅንሰ ሀሳብ በአጭር እና በቀላል አማርኛ (exposed) ለአንድ ነገር ተጋላጭ በሆንን መጠንን አንድን ነገር እንለምደዋለን፤ ከዚህ በፊት የምንጠላው ወይም ከእምነታችን ጋር የሚጋጭ ወይም ለህይወታችን የሚያሰጋ ቢሆንም እንኳ። ከዛም የኑሯችን አካል የህይወታችን ተጣማሪ ይሆናል።
ብዙ በመጋለጥ ምክንያት ስንት ነገር ለምደን ይሆን? ነውር ያልነውን ለምደነው ተራ ሆኖብናል አስደንጋጭ የነበረው ቀሎናል።
በተፈጥራዊ የህይወት ዑደት ምክንያት የተላመድነው ነገር ቢኖርም አሁን ግን ለማየት የፈለግነው ይህ ዘመን በማላመድ ሸፍኖ ስለሚሸጥበት መንገድ ነው።
ከተኛንበት ጥልቅ እንቅልፍ ወጥተን በመንፈሳዊነት እንንቃ ከድንዛዜያችንን እንባንን አለምን በኢስላም መነፅር እንያት ከዛ አንድ የማቃናት አሻራችንን እናኑር።
Life is nothing but a constant cycle of reinventing yourself.
"ህይወት ሌላ አይደለችም ቋሚነት ያለው እራስን አፍርሶ የመገንባት ሂደት እንጂ'
