Usmanic Islamic psychology/ ስለ ሰው ልቡና
Ir al canal en Telegram
- እውነተኛ የህይወት ታሪኮች - ኢስላማዊ የስነልቦና ምክሮች ፣ ጥያቄዎች እና አገልግሎቶችን ያገኛሉ። - ስለ ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ ይማራሉ። - ሳምንታዊ ሽልማቶች ለሁሉም በማጋራት የሙስሊሙ ኡማ ጤና የሚጠበቅበትን ይህን ቻናል እናሳድግ ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @usmanoman ላይ ያናግሩን።
Mostrar másEl país no está especificadoLa categoría no está especificada
756
Suscriptores
+3124 horas
+1487 días
+33830 días
Archivo de publicaciones
አሸናፊ የሆነው ተሸላሚው የሚለይበት ሰአታት እየተቃረቡ ነው።
መራጮች ምርጡ ተመራጮች አስመርጣችሁ አጠናቅቁ።
ሁላችንም እየጠበቅንህ ነው ጌታዬ 🙏። ሀጃችን ብዙ ነው ወደ አንተ የሚያመላልሰን 🔄።
በቅፅበት ሁሉንም ልታሳካልን ሳይሳንህ ግን ፍቅርህ ነው ❤️ እና ከደጅህ የምንመላለስበትን ጉዳይ እልፍ አደረከው ✨
ምኞቶቻችን ወደ አንተ የሚያቀርቡን ፀሎት ናቸው 📿። ህልማችን ዘውትር አንተን በትህትና እንደንጠይቅህ የሚያስችሉን ተስፋዎቻችን ናቸው 🌟።
በራህመትህ ጎብኘን አዛኙ ጌታ ሆይ! 🙏
'አላህ የወሰነው' እና 'አላህ የፈቀደው'
-ነፃ - ፍቃድ/ free will -
ሁሉም ነገር የሚሆነው በአላህ ፍቃድ ሲሆን በተሰጠን ነፃ ፍቃድ ውስጥ ሁሉንም ነገር የምንወስነው/የምንመርጠው ግን እኛ ነን።
አላህ እንዲሆን የፈቀደው ማለት አላህ የወሰነው (predestined) ማለት አይደለም።
እኛ ነን ምንናገረውን የምንወስነው ፣ እኛ ነን ጓደኞቻችን እነማን መሆን እንዳለባቸው የወሰነው። እኛ ነን ተግባሮቻችንን ስራዎቻችንን....የምንመርጠው የምነወስነውም።
ሰዎች በራሳቸው ስህተት እና አላህ የሰጣቸውን አቅል/የማገናዘብ አቅም በቅጡ ሳይጠቀሙ ህይወታቸው ላይ ለሰሩት ስህተት አላህ ወስኖብኝ/ሽቶብኝ ነው ይላሉ። አዎ ያለ አላህ ፍቃድ ያን ነገር መፈፀም አይችሉም ነበር ግን ነፃ ፍቃዳቸውን ተጠቅመው የተሻለ ነገር ላይ የመድረስንም ሰበብ ማድረስ ይችሉ ነበር።
አላህን ሰበብ እያደረጉ መቆዘም የቀደር ግንዛቤ ድክመት ነው።
ሁሉም ነገር (አተነፋፈሳችን ፣ ጠብ የምትለው ውሀ ፣ አይምራችን ሊረዳቸው የማይቻሉ ደቂቅ ነገሮች ሁሉ አስቀድመው የተፃፉ ናቸው)
ምድር እና ሰማይ ከመፈጠራቸው 50ሺ አመታት በፊት ነገራት በሙሉ ለህወል መህፉዝ ላይ ሁሉን አዋቂ በሆነው ጌታ የተከተቡ ናቸው።
የምናደርገው ነገር ይታወቃል ማለት የማድረግ ነፃ ፍቃዳችን ተፅእኖ ስር ነው ማለት አይደለም ከጊዜ እና ከቦታ ገደብ ውጪ የሆነው ጌታ አላህ ግን ምን እንደምንወስን እና እንደምናደርግ ከእኛ የማሰብ አቅም ውጪ በሆነ መንገድ ቀድሞ ያውቃል።
ይህ ደግሞ ሀኪም/ጥበበኛ እና አዚም/ታለቅ የመሆኑ ሚስጥር ነው።
#ስለ_ቀደር
#usman_mus ✍️
ኡስማኒክ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ
#2 ሽልማት የሚያስገኝ ሀሳብን በፅሁፍ የመግለፅ ውድድር 5 የመጨረሻ ዙር ተፋላሚዎች ተለይተዋል።
ከታች በሰማያዊ የተፃፉትን የተወዳዳሪዎች ቅደም ተከተል በመንካት እና በመግባት ኮሜንት ውስጥ ከ የወደዳችሁት ተቀ ፅሁፍ ላይ ሪአክት በማድረግ እንዲያሸንፉ አግዟቸው። ብዙ ሪአክሽን ያገኘ የማሸነፍ እድሉ ከፍ ይላል።
የህዝብ ድምፅ 40% የዳኛ 60% ድርሻ ይይዛል።
ፀሀፊዎችም ሊንኩን በመላክ ሪአክት ማስደረግ ይችላሉ።
መልካም እድል
አንደኛ ተወዳዳሪ
ሁለተኛ ተወዳዳሪ
ሶስተኛ ተወዳዳሪ
አራተኛ ተወዳዳሪ
አምስተኛ ተወዳዳሪ
5,ተስፋ መቁረጥ ሲሰማን ይህን ዱአ በማለት የአላህ ምራቻ እንጠይቅ
اللهم إني أسألك رحمةً من عندك وعملًا صالحًا تقربني إليك.
አላህ ሆይ ምህረትህን እንዲሁም ወደ አንተ የምታቀርበኝን መልካም ስራ ትለግሰኝ ዘንድ እጠይቅሃለሁ።
የዚህ ዱአ ስነልቦናዊ ጠቀሜታዎች
- በጎ የማድረግ ሞራላችን ያነቃቃል
- በአላህ በመመራት እና በመመካት ውስጥ መስከን ውስጥ እንገባለን።
ፅሁፉን የማስገቢያ ጊዜ የመግሪብ አዛን ላይ ይጠናቀቃል። መሳተፍ የምትፈልጉ የቀሩትን ሰአታት ተጠቀሙበት።
ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ/ኢልመ- ነፍስ
ክፍል 4. አቅል
-ፊጥራ
-ነፍስ
-ሩህ
-አቅል/አይምሮ
-ቀልብ/ልብ
-ተዝኪየቱ ነፍስ/ራስን ከወንጀል ማፅዳት
ለዛሬ አቅልን በጣም በአጭሩ እናያለን ኢንሸአላህ!
አቅል ምንድነው?
የአቅል (عقل) (mind) ስርወ - ቃል መሠረተ ትርጉም መገንዘብ ፣ መረዳት ፣ ማወቅ የሚል ትርጉም አለው።
ይህ የሰው ልጅ በምክንያት/አምክንዮ የሚያስብበት ክፍል ሲሆን ፥ እውነትን ከውሸት የሚለይበት ፍጥረተ አለሙ የሚረዳበት እና የሚገነዘብበት የማስተዋያ ክፍሉ ነው።
አቅል እስካሁን ካየናቸው የሰው ልጅ መሰረታዊ የማንነት ክፍሎች አንዱ ሲሆን ስለራሱ ስለሰዎች እና ስለፈጣሪው በትክክል እና በጥራት እንዲያስብ የሚያደረገው መሣሪያ ነዉ
አቅል በኢስላሚክ ሳይኮሎጂ ጥናት ውስጥ
በኢስላሚክ/በኡስማኒክ ሳይኮሎጂ ውስጥ አቅል መስታወት ሆኖ ሰው አለምን የሚያይበት የመመልከቻ መነፅሩ ነወ።
በተለያዩ ምክንያቶች የእውነት እና የፍትህ ሚዛኑ የተዛባ አይምሮን እና በሀቅ ላይ ቆሞ በጥራት ህይወትን መገንዘብ ያቃተውን አይምሮ በማገዝ የሰዎችን የማመዛዘን ተፈጥሯዊ ማንነት የማስመለስ ህክምናዊ እና ስነዘዴያዊ መንገዶችን ይከተላል።
ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ መፅሀፍ
አዘጋጅ እና ፀሀፊ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂስት ኡስማን ሙስጠፋ)
ኢንሻአላህ ይቀጥላል...
#2 ሽልማት የሚያስገኝ ሀሳብን በፅሁፍ የመግለፅ ውድድር
ርእስ እና የመወዳደሪያ መንገድ :- ምድር ላይ የሰው ልጅ ስለሚያጋጥመው ፈተና እና ተስፋ ከ 4-7 መስመር ባልበለጠ በጥሩ አገላለጽ እና ሳቢ የአፃፃፍ ስልት ኮሜንት መስጫው ላይ በማስቀመጥ ተወዳደሩ!
አሪፉ ፅሁፍ ታይቶ አሸናፊው ሽልማቱን ይወስዳል።ኢንሻአላህ!
ሽልማቱ:- የ ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ መፅሀፍ እና የሳምንታዊ 780 ሜ.ባ የኢንተርኔት ፖኬጅ
#ከኡስማኒክ_ኢስላሚክ_ሳይኮሎጂ
መልካም እድል!
ጥያቄ 3
ልማር ወይስ ላቁም?
እኔ የ18 ወጣት ስሆን ቀጣይ አመት የ 12ተኛ ክፍል ተፈታች ነኝ። ትምህርት የሚሆንልት አይነት ሰው ብሆንም ታላላቆቼ ተምረው ያሰቡትን ማሳካት አለመቻላቸውን ሳይ እና 'ትምህርት አያሳልፍልህም አርፈህ ተፍ ተፍ በል' የሚሉ መሰል ተደጋጋሚ ምክሮችን ስሰማ ተስፋ ስለቆረጥኩኝ።
የ ቀጣይ አመት የ12ተኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ወስጄ የትምህርት አለምን ልሰናበት ወይ? በሚል ጥያቄ ራሴን እያፋጠጥኩኝ አለው። እባክህን ለኔ እና ለመሰል ጓደኞቼ በትምህርት ጉዳይ ያለህን አቋም ብታሳውቀን። አመሠግናለሁ።
(መልስ እሰኪሰጥ ድረስ አስተያየታችሁን ታች አሰፍሩ)
-ናፍቆት'
ወዳለፈው ዘመን የሚጎትት የኋሊት ሀዲድ ነው። በትዝታ ተሳፍረን ትናንትናችንን ልንጎበኝ የምንሄድበት የምልሰት ኑሮ።
የናፍቆት ወላፈን በልጅነታችን ካለፍንባቸው መንገዶች ፣ ከወላጆቻችን አልባሳት ፣ ቤታችን ውስጥ ከቆመችው የዛፍ ጥላ ፣ ከእህት ወንድሞቻችን ድምፅ እየተነሳ ወደ ህሊናችን ይተናል።
ናፍቆት የሰው ልጆች የማያመልጡት ያለፈ ታሪካቸው ዶሴ ላይ የተፃፈ ሰቀቀን ፣ የትካዜ ሀገራቸው መሠደጃ ነው።
"መነገር ያለበት ሁሉ አስቀድሞ ተነግሯል። ግን ማንም ሰው ስለማያዳምጥ፣ ሁሉም ነገር እንደገና መነገር አለበት።"
- copy
ሂስድ/ምቀኝነት መንስኤዎች እና መዳኛዎቹ
መልስ/ ክፍል ሁለት (የማጠቃለያ መልስ)
የሰው ልጅ ትልቁ ፈተናው በነፍሱ ጉትጎታ ወንጀል ለመስራት ሲፈተን ባለው ትግል ውስጥ ነው።ይህን ሀሳብም ይበልጥ ግልፅ የሚያደርግ ዘውትር የምንሰማው ወይም የምንለው ግን ትርጉሙን ብዙም ያላስተዋልነው ታላቅ ዱአ አለ።
أعوذ بالله من شرور أنفسنا ومن سيئات أعمالنا
ትርጉሙም 'ከነፍሳችን ሸር እና ከመጥፎ ስራችን ውጤት ወይም ህይወታችን ላይ ከሚያስከትለው ተፅእኖ በአላህ እንጠብቃለን' ማለት ነው።
የሰው ልጅ ትልቁ ጀሀዱ/ትግሉ ከሌሎች ጋር አይደለም። ከውስጣዊ መሻቱ እና ከተፈጥሮው መጥፎ ዝንባሌ ጋር የሚያደርገው እንጂ።
ሰው በብስጭት ፣ በዝሙት በስርቆት እና በብዙ እኩይ የተግባር ዝንባሌዎች እንደሚፈተነው ሁላ በምቀኝነት/ሌሎችን በመመቅኘት ሊፈተን ይችላል።
እህቴም ያጋጠማት ተመሳሳይ የችግር አይነት ነው።ይህ በሽታም ነፍስን ሳያቋርጡ በመፈተሽ ፣ በማፅዳት ፣ እና በመመርመር ወደ አላህ በተውበት በመመላለስ የሚድን የልብ ህመም ነው።
እህቴ አንቺ የተፈተነሽበት ጉዳይ የአለምን ህዝብ እና የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) ኡማ እየተገዳደረ ያለ የብዙ ቤተሰቦችን ህብረት የበጠሰ ለበርካታ ወንጀሎች መንስኤ በሆነው ነገር ነው።
እህት እህቷን በመመቀኝነት ምክንያት ጎድታለች ፣ እናት እና ልጅ በዚህ ምክንያት ተቆራርጠዋል ፣ ልጅ አባቱን ገድሎ ወደ ዘላለማዊ የህሊና ወህኒ እና ለምድር እስር ቤት ተዳርጓል ፣ ወንድም ወንድሙ ላይ ተነስቷል ጓደኛማችነት ፈርሷል።
የብዙ ሲህር የማድረግ መሠረታዊ መንስኤ ከስሩ ያልታከመ ምቀኝነት እንጂ ሌላ አይደለም። ቅናት የወለደው መጠላለፍ የሰው ልጆች የተተበተቡበት የፅልመት ድር ነው።
እንዳንቺ የነፍሱን እኩይ ባህሪ ለይቶ እና አውቆ ፣አምኖ የሚፀፀት ሰው ጥቂት ነው። ይልቅስ ራሱን በማፅደቅ እና ነፍሱን ከእንከን የጠራች አድርጎ የሌሎችን ጎዶሎ ለማየት ሁሉም በሚጥርበት አለም ያንቺ ራስን የመፈተሽ አቅም እና እንከንን ለራስ ሳያደሉ ከነፍስያ መንቀስ መቻል ትልቅ የሚደነቅ ባህሪ ስለሆነ ቀጥይበት ለማለት እወዳለሁ።
ለዛሬ ግን ለብዙ ቀናት ያንከባለልነውን ጥያቄ መፍትሔዎቹ ያልናቸውን የተወሰኑ ነጥቦች በመጥቀስ እናጠቃልላለን።
1ኛ, ይህ ስሜት ሲሰማሽ 'አኡዙቢላሂ ሚነሸይጧን ረጂም' (ከሰይጣን ተንኮል በአላህ እጠበቃለው) በማለት እኩይ የሆነውን የሰይጣን አላማ ቶሎ አክሽፊበት
2ኛ, እኛን ሊያስቀናን የሚችል ፀጋን ሰዎች ዘንድ ስናይ 'ማሻአላህ' ወይም 'ተባረከላህ' ማለት መርሳት የለብንም አላህ የተባረከ እና ብሩክ ነገሮችም በሙሉ ከሱ መገኘታቸውን እውቅና መስጠት እና የፀጋውን ምንጭ ወደሱ በመመለስ አስገኚውን ማክበር በማድነቅ እና በማመስገን ልብን በአላህ ውሳኔ ማረጋጋት ያስችላል ።
3ተኛ, ምንም ነገር ላንቺ ተፅፎልሽ የቀረ ወይም የሚቀር አለመኖሩን አስታውሺ በቀደር ያለሽን እምነት አዳብሪ።
4ተኛ, የዚችን አለም ማጣት እና ማግኘትም ፈተና ብቻ እንደሆኑ አውቀሽ የተመኘሽው ፀጋ ወዳንቺ ቢመጣ ምንአልባት ከአላህ ጎዳና የሚያርቅ እና ለሁለት አለም ኪሳራ ሊዳርግ በሚችል ፊትና ልትወድቂ ስለምትችይ አላህ ጠብቆሽ ሊሆን እንደሚችል በማስታወስ አላህን ማመስገን እና ውሳኔውን መውደድን ልመጂ።
5,ካንቺ በታች ያሉትን ሰዎች አስታውሺ። አንቺ ያለሽን ነገር ዘወትር እንዲያገኙ አላህን በሚማፀኑ ሰዎች እና አንቺ ያገኘሽውን ፀጋ ላንዳፍታ ቢያገኙ ትልቁ ህልማቸው እንደተሳካ በሚያልሙ ሚሊዮን የአለም ህዝቦች ጎን እራስሽን አስተያዪ።
6, ይህን ስሜት እንዲያጠፋልሽ አላህን በመጠየቅ በዱአ በርቺ።
7,የጠዋት እና የማታ አዝካሮችን አዘውትሪ። በተለይ ከሸር እና በሂስድ የሚታደጉትን ሁለቱን አያ አዘውትሪ :- ቁል አኡዙ ቢረቢናስ እና ቁልአኡዙ ቢረቢል ፈለቅ
✍️ ኡስማን ሙስጠፋ ከኡስማኒክ ሳይኮሎጂ።
ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @psychosman1 ላይ ያናግሩን
