en
Feedback
መጽሐፉ ይናገር | Official

መጽሐፉ ይናገር | Official

Open in Telegram

መጽሐፉ ይናገር ክርስቲያናዊ አገልግሎት በወንጌላዊያን አማኞች የነገረ መለኮት ተማሪዎችና የቃሉ አገልጋዮች በ2013 ዓ.ም የተመሠረተ ተቋም ሲሆን አሁናዊ መስኮቹ፦ 🔘 የመጋቢያንና መሪዎች ስልጠና 🔘 የመጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጅ (Gateway) 🔘 የቲቪ ፕ/ም በተስፋ TV ቅዳሜ 9-10 🔘 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኅብረቶች ሊንክ፦ @metsihafuyinager በውስጥ፦ @adfontess ☎️ +251947424046

Show more
340
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+1230 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+1
in 0 channels
August '26
+25
in 1 channels
Get PRO
July '26
+327
in 1 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
01 September+1
Channel Posts
የመጀመሪያው የውይይት ጥያቄ ላይ እየተነጋገርን ነው! ➊ "ለፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሾልከው ገብተዋል" (ቁ4) የሚለውን አይተናል፣ "የተጻፉ" ሲል የለፍርድ የጻፋቸው ማነው? ይህ ነገር ወደ Double predestination ሊወስደን የሚችል ነው ወይስ? እግዚአብሔር የሚድኑትን ሲመርጥ የሚጠፉትንም ወስኗል ማለት ነው? https://vt.tiktok.com/ZS9BspkKRu42M-qa7wc/ የምትችሉ በሊንኩ በኩል ተቀላቀሉን!!

2
የተወደዳችሁ ከላይ Pin ያደረግነው ዛሬ ምሽት 3:00-4:30 ቲክቶክ ላይ በሚኖረን የጋራ ጊዜ የሚዳሰሱ ከይሁዳ መልእክት ጥናት የቀረቡ ጥያቄዎች ናቸው። ተጨማሪ ጥያቄዎች ካላችሁ በውስጥ አድርሱን። 👉 @metsihafuyinager
46
3
እግዚአብሔር ማንንም ስለማይፈራ "አካላዊ ጡንቻችሁን አፈርጥሙልኝ!" አይላችሁም። የሰውን ልጅ ልቦች ሁሉ እርቃናቸውን ስለሚያውቅ በስወር የሥጋ ትምክህት አትሸውዱትም! ------------ Join Us & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
58
4
ውድ ቤተሰቦቻችን ዛሬ አመሻሹን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና (Entrance) የተለቀቀ በመሆኑ Internet በብዙ የአገሪቱ ክፍሎች መጨናነቁን አስተውለናል፣ ስዚህም ዛሬ የሚኖረን ጊዜ ወደ ቀጣይ ሳምንት ተሸጋግሯል። ጸጋው ከቤተሰባችን ጋር። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
92
5
ዛሬ ምሽት በቲክቶክ ገጻችን! ----------- ባለፉት ስድስት ወራት ከነበረን የይሁዳ ጥናት መካከል የተነሱ ጥያቄዎችን ባለፈው ሳምንት ማየት ጀምረናል። ዛሬ ምሽትም ቀጣዮቹ የውይይት ጥያቄዎች ላይ እንነጋገራለን። ጥያቄዎች፦ ➊ "ለፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሾልከው ገብተዋል" (ቁ4) የሚለውን አይተናል፣ "የተጻፉ" ሲል የለፍርድ የጻፋቸው ማነው? ይህ ነገር ወደ Double predestination ሊወስደን የሚችል ነው ወይስ? እግዚአብሔር የሚድኑትን ሲመርጥ የሚጠፉትንም ወስኗል ማለት ነው? ➋ ቁ5 ላይ "ሕዝቡን ከግብጽ አድኖ ግን በረሃ ላይ አጠፋቸው!" የሚል Claim እናነባለን፤ ስለዚህ የሚያድን የሚያጠፋም ራሱ እግዚአብሔር ነው ማለት እንችላለን? እግዚአብሔር ሰዎችን ያጠፋል? ------- በቲክቶክ፦ መጽሐፉ ይናገር ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00-4:30 ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
101
6
የእረኝነት ወጉ መንጋ መመገብና ከነጣቂ ተኩላ መጠበቅ ነው። ዘንድሮ የብዙዎቹ እረኝነት ግን መንጋውን ለገዛ ጥቅማቸው የመሸለት ሆኗል። የእረኞቹ አለቃ ሥራቸውን ሊመዝን ይመጣ የለ? ያኔ ማን ምን ሲሠራ እንደከረመ በሁሉ ፊት ይመሰክራል። ------------ Join Us & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
183
7
በዚህ ወቅት በአያት Center የቆላስይስን መልእክት እያጠናን እንገኛለን። ባለፈው ሳምንት ቆላ 1:3-8 የጀመርን ሲሆን ክፍሉ አንድ ረጅም ዐረፍተ ነገር ተብሎ የሚታወቅ እንደሆነ አይተናል። ለመረዳት እንዲያግዘን Exegetical Diagram ሠርተንለት ነበርና ከዚህ በታች አስቀምጠናል። ዛሬ ምሽት ደግሞ ባለፈው በDiagram መልክ ያየናቸውን የክፍሉን አንጓዎች በጸሐፊውና በመልእክቱ ተቀባዮች መካከል በተደረገ ጭውውት መልክ (Dialogue format) በጥልቀን እንመረምረዋለን። ጸሐፊው ጳውሎስና የመልእክቱ ተደራሲያን ሲያወሩ እዩልን። ደስ አይሉም? ዛሬ ምሽት በጭውውታቸው መድረክ እኛም ወንበር ስበን እንቀመጥና እንታዘባቸዋለን፣ እንማርባቸዋለንም። ቤተሰቦቻችን በደንብ አይታችሁት ኑ! ለሌሎችም አጋሩ። እግዚአብሔርን እናመሰግናለን! (ቆላ 1:3-8) መቼ?           ➘ ሁልጊዜ! ሁሌ ማለት?                   ➘ ስለ እናንተ ስንጸልይ ሁሉ! ለምን?             ➘ ስለ ሰማነው ዜና! ምን ሰማችሁ?              ➘  ስለ እምነታችሁ!                            🔘 በክርስቶስ ያላችሁ!               ➘  ስለ ፍቅራችሁ                               🔘 ለቅዱሳን ያላችሁ! ከየት የመጣ ነው አሉ?                               ➘ ከተስፋችሁ! የትኛው ተስፋ?                  ➘ በሰማይ የተዘጋጀላችሁ! እንዴት ነበር ያገኘነው?                                  ➘ ሰምታችሁ! ከየት?            ➘ ከእውነቱ ቃል! ደግሞ ምንድነው እርሱ?                                 ➘ ወንጌሉ! እርሱስ እንዴት ተዋወቀን?                              ➘  ወደ እናንተ መጥቶ! እና አሁን ምን እየሆነ ነው አሏችሁ?                                                      🔘 እየበዛ /እየጨመረ                             🔘 ፍሬ እያፈራ ታድሎ! የት ጋር?                         ➘  በእናንተ መካከል! ሆ! ቆይ ከመቼ ጀምሮ?                      ➘ ከሰማችሁበት እና                 ➘  ከተረዳችሁበት ቀን አንስቶ! ቆይ የሰማነው ምን ነበር?                            ➘  የእግዚአብሔርን ጸጋ! ኧረ! በምን በኩል?                       ➘  በእውነቱ (በወንጌሉ) ማን ነበር የነገረን?                           ➘  ኤጳፍራ! እርሱ ደግሞ ማን ይሆን?                             ➘  ታማኝ አገልጋይ በምን አወቃችሁ?                   ➘ ያኔ ወንጌሉን ለእናንተ ነገራችሁ!                   ➘ አሁን ስለ እናንተ ሁሉን አሳወቀን! ሌላስ ምን ነገራችሁ?                   ➘  በመንፈስ ስለሆነ ፍቅራችሁ! ------------ Join & Share!!! @metsihafuyinager ------------ በውስጥ፦ @adfontess
187
8
https://vt.tiktok.com/ZS9kXxqMejVV6-hiq18/
140
9
ዛሬ ምሽት በቲክቶክ ገጻችን! ----------- ላለፉት ስድስት ወራት የይሁዳን መልእክት ስናጠና መቆየታችን ይታወቃል። የቁጥር በቁጥር ጥናቱን ባለፈው ሳምንት ያጠቃለልን ሲሆን ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ደግሞ በጥናታችን መካከል የተነሱ ግን በቂ ጊዜ ሰጥተን ያልዳሰስናቸውን ጥያቄዎች ማየት እንጀምራለን። በጥናት ጊዜው የክፍለ ምንባባቱን ዐውዳዊ ትርጓሜ ገለጻዎችን (presentations) ሲያቀርቡ የነበሩት ሸዋ እና ባርኒ ናቸው። ከዚህ በታች የምናቀርብላችሁ ጥያቄዎች ደግሞ በሌሎች አጥኚዎች (ቤተሰቦቻችን) በውስጥ መስመር የቀረቡ ሲሆኑ በዋናነት ጥያቄዎቹን የሚመሉት Presentation ያቀረቡ ወንድሞቻችን ይሆናሉ። ጥያቄዎች፦ ➊ ቁ3 ላይ "አንድ ጊዜ ስለተሰጠ ሃይማኖት" የሚለውን ሌሎች ትርጉሞች "እምነት" ይላሉ እምነትና ሃይማኖት interchangeably አገልግሎት ላይ ሊውሉ የሚችሉ ቃሎች ናቸው ማለት ነው? ልዩነታቸው ምንድነው? ወይስ አንድ ናቸው? ➋ ይሁዳ "ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ ተግቼ ሳለሁ... ስለ እምነታችሁ መጋደል እንዳለባችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ" (ቁ3) ማለቱን አይተን ነበር፤ ይህን መልእክት ያስቀየረው መንፈስ ቅዱስ ነው ወይስ ይሁዳ? በዚህ ዘመን "እግዚአብሔር መልእክት አስቀይሮኝ ነው!" የሚሉ ሰዎች እውነት አላቸው ማለት ነው? ወይስ የይሁዳ ዐውዳዊ ትርጉም ይህን አይመለከትም? ➌ "ለፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሾልከው ገብተዋል" (ቁ4) የሚለውን አይተናል፣ "የተጻፉ" ሲል የለፍርድ የጻፋቸው ማነው? ይህ ነገር ወደ Double predestination ሊወስደን የሚችል ነው ወይስ? እግዚአብሔር የሚድኑትን ሲመርጥ የሚጠፉትንም ወስኗል ማለት ነው? ------- እነዚህ ዛሬ የምንመልሳቸው ጥያቄዎች ናቸው፣ እናንተም ከጥናታችን (ከይሁዳ) ያላችሁን ጥያቄ በውስጥ መስመር አድርሱንና በቀጣይ ጊዜያት እንመለከታለን። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
155
10
እንደ ምህረቱ ብዛት! 🔥 ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል። (1ጴጥ 1:3-5) ትሩፋቶቹ፦ ➘ ሕያው ተስፋ ➘ ርስት 😎 ምን አይነት ርስት? ➢ የማይጠፋ ➢ እድፈት የሌለበት ➢ የማያልፍ እና ምን ይሁን? 🎯 እንደ ምንህረቱ ብዛት ዳግመኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ!!!! ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
187
11
ዛሬ በአያት ኅብረት  -----🎻--------- የቆላስይስ መልእክት ጥናት (ወንጌሉና አስከትሎቱ/ፍሬው) ጳውሎስ ስለ ቆላይስይ አማኞች ያመሰግናል። ▣ ስለ እነርሱ በሚጸልይበት ጊዜ ሁሉ! የምስጋናውም ሰበብ ስለነርሱ የሰማው መልካም ዜና እንደሆነ ክፍሉ ያትታል። 🎻 ወንጌሉ በእነርሱ ፍሬ እያፈራ ነው። በእነዚህ ቁጥሮች ስለ ወንጌሉና ስለ አስከትሎቱ (effect of it) በግልጽ የተቀመጡ እውነታዎች ምን ምንድናቸው? እንዴት እንረዳቸው? ----------- ⏰ ከ11:30-1:30 📍አያት ባቡር ጣቢያ ጋር Ayat Shopping Mall 4th Flor ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
190
12
https://vt.tiktok.com/ZS4oN2T4p/ "ክርስትና ከአስተምህሮቶቹ አንዱን ሰበዝ (ክር) ተነክቶ (ወጥቶ) ክርስትና እንዳለ መሆን አይችልም። ከመሠረታዊ አስተምህሮዎቹና እሳቤዎቹ አንዱ ገመድ (ስር) ወጥቶ ቤቱ እንዳለ መቆም (መቀጠል) አይችልም። ምክንያቱም መሠረቱ ተነክቷልና።" መጋቢ ጆን ስቶት የተናገሩትን አማኒ paraphrase አድርጎ ሲያቀርበው። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
186
13
ከእግርህ ስር ሆኜ ልማር ቃልህን፣ ከእግርህ ስር ሆኜ ልወቅ ቃልህን፣ ረቢ ሆይ ና አስተምረኝ ከቃልህ፣ መንገዴን አቅና ከሕይወት ቃልህ። ቃልህ ለመንገዴ ለሕይወቴ ብርሃን ነው፣ ይህን ክፉ ዘመን የማልፈው ባንተ ነው፣ በሚገባኝ መንገድ ና አስተምረኝ፣ የሕይወትን መንገድ አቅጣጫ አሳየኝ። ቃልህ ይብራልኝ ጌታ፣ (2×) እንድኖር ሁሌም በእርጋታ፣ ቃልህ ይብራልኝ ጌታ። ቃልህን ያወቀ ልቡናው ይበራል ጥበብ እያበዛ በክብር ይዘልቃል ጥፋት ያገኘው ሕይወት የሚገታ ርስቱን ይወርሳልጨየማታ የማታ ቃልህ ይብራልኝ ጌታ፣ (2×) እንድኖር ሁሌም በእርጋታ፣ ቃልህ ይብራልኝ ጌታ። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
216
14
https://vt.tiktok.com/ZS9kdHmQpTstH-0njvb/
159
15
በእግዚአብሔር ፍቅር ራሳችሁን ጠብቁ! (ቁ21) ያለው ይሁዳ "ሳትሰናከሉ በክብሩ ፊት እንድትቆሙ ሊጠብቃችሁ ለሚቻለው ለርሱ ክብር ይሁን" (ቁ24) ሲል እንመለከታለን። ከላይ "ራሳችሁን ጠብቁ" ብሎ ከታች ባለው ቁጥር ደግሞ "እግዚአብሔር ይጠብቃችኋል" ይላቸዋል። ይህ እርስ በርሱ የሚጋጭ አይደለምን? መጽናት የአማኙ ሥራ ነው ወይስ የሚያጸናቸው ራሱ እግዚአብሔር ነው? ዐውዳዊ ምላሹን ዛሬ በቲክቶክ ገጻችን 3:00 በሚኖረን የይሁዳ መልእክት ጥናት ላይ የምንመለከት ይሆናል። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
168
16
ዛሬ ምሽት በTiktok ገጻችን! -------🔥------------ የይሁዳ መልእክት ጥናት! 📖 እለቱ፦ ማክሰኞ ምሽት ሰዓቱ⏰፦ 3:00-4:30 ቤቱ፦ መጽሐፉ ይናገር የጥናቱ ክፍል፦ ቁ24-25 ሁላችንም በመገኘት እናትርፍ!! ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
181
17
በሰፊው ጎዳና ትውልድ ሲተራመስ፣ የልቡ ላይሞላ ያሰበበት ላይደርስ፣ በቀጭኑ መንገድ ጌታን ብቻ ይዞ፣ ወደ እረፍት ይገባል ተጉዞ ተጉዞ!። ይታወቅልኝ....!😊 ምርጫዬ ጌታነው! እኔም የርሱ ነኝ። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
199
18
ነፍሴ ሆይ... እግዚአብሔር አምላክ ነውና ስገጂለት መሐሪው ጌታዬ ምስጋና ይብዛለት... በሕይወቴ ሁሉ እኔም ልቀኝለት ቸርነቱን ልንገር ምህረቱን ልዘምር፣ ቅኔን ልቀኝለት... ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
164
19
ቤተ ክርስቲያንን ስታስቡ ጥንቅቅ ያለ ፕሮግራም ተካፍሎ ስለመመለስ፣ ከዐውድ ያላፈነገጠ ትምህርትና ስብከት ተካፍሎ ስለመምጣት አስባችሁ ከሆነ የነገረ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረታችሁ ችግር ገጥሞታል። ቤተ ክርስቲያን ፕሮግራም ተካፍሎ ለመመለስ የሚኬድበት ቦታ ሳይሆን ሕይወት ለመካፈል (ለመቀበልና ለመስጠት) የሚኬድበት ሕያው የሆነ የወንድሞች ኅብረት ነው። ሕያውነቱ አንዱ ሰው በሌላው ውስጥ በመኖሩ የሚረጋገጥ ነው። ወደ ቅዱሳን ጉባኤ ኺዱ፤ በፍጹም አትቅሩ። ዛሬ ጠዋት በኼዳችሁበት ጉባኤ በስንት ወንድምና እህቶች ልብ ውስጥ በቋሚነት አላችሁ? ስንት ሰዎች actively በሕይወያችሁ ውስጥ መብትና ኃላፊነት አላቸው? እንደርሱ ካልሆነ የኼዳችሁት ወደ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን ወደ አንድ ቆንጆ ማኅበራዊ ክለብ ነው። ------------ Join Us! & Share!!! @metsihafuyinager @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
805
20
ቃለ እግዚአብሔርን የንግግሮችህ ማጠናከሪያ አድርገህ ከመጠቀም ተቆጠብ። ይልቅ ገና ከመነሻው እንደ እግዚአብሔር ቃል ተናገር። "ማንም የሚናገር እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር" የተባለውን አትዘንጋ። መጽሐፍ ቅዱስ አንተ ብዙ ካወራህ በኋላ ንግግሮችህ እግዚአብሔራዊ እንደሆኑ የምታስረዳበት ሰነድ ሳይሆን ምን፣ መቼና የት መናገር እንዳለብህ ታውቅ ዘንድ የተሰጠህ መመሪያ ነው። ስለዚህ ረጅም አውርተህ ይህ ንግግር እንደ እግዚአብሔር ቃል ነው? ከምትል ከቃሉ ጋር ረጅም ቆይተህ ጥቂት ብታወራ ይሻልሃል። ------------ Join & Share!!! @metsihafuyinager ------------ ወደ ውስጥ፦ @adfontess
185