የቀጠናው ተመልካች
Open in Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
4 308
Subscribers
No data24 hours
-227 days
-8530 days
Posts Archive
4 307
🇮🇷 ሰበር ዜና፡ በመሽሃድ፣ በቃም እና አሁን ደግሞ በዋና ከተማው ቴህራን፣ ነገ ይደረጋል የተባለውን ስምምነት በተቃወሙ አጥባቂ ሰልፈኞች እና በፀጥታ አካላት መካከል ግጭቶች እየተደረጉ እንደሆነ ተገለፀ።
4 307
🇮🇷⚡️በኢራን ጎዳናዎች ላይ፣ አያቶላህ ሙጅተባ ኻሚኒይ፣ ዝምታውን እንዲሰብር የሚያስጠነቅቁ መፈክሮች ታይተዋል።
ዛሬ በተፈጥሮ ቀን ዛፍ እንድንተክል መልዕክት ያስተላለፈልን ክቡር አያቶላህ፣ ምነው ስለ ድርድሩ አንድ ቃል አልተነፈሰም? አያቶላህ ተናገር!
4 307
🇮🇷🇺🇸⚡️ በኢራን፣ የነገውን ስምምነት በመቃወም ምሽቱን ለነገ ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅቶች ታይተዋል። በየ ጎዳናው፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩን አራግቺንና፣ የፖርላማ ቃል አቀባዩን፣ ቃላቢፍን፣ የሚያወግዙ ቃላቶች እና መፈክሮች ከሰልፈኞች ሲሰሙ አምሽቷል።
በቀል ብቻ! ድርድር፣ ስምምነት፣ አንፈልግም። የአያቶላህ ኻመኒይን ደም ማስመለስ እንጂ፣ መፈራረም አንፈልግም!የሚሉ ድምፆች በመሰማት ላይ ናቸው። ሌሎች፣ ይህ ሕዝባዊ አቋም፣ የነገውን ስምምነት እስከ ወዲያኛው እንዳያደናቅፍ፣ ስጋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው።
4 307
🇮🇷 ትናንት ያልኳችሁ ሆነ፣ — የእስላማዊ ሪፐብሊክ ኢራን አጥባቂ ደጋፊዎች፣ ዛሬ በቴህራን ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ከአሜሪካ ጋር የሚደረግን ማንኛውንም ድርድር ተቃውመዋል። በመፈክሮቻቸውም፣ የኢራኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ሰይድ አባስ አርጋቺን እንዲህ ሲሉ በክፉ አውግዘዋል።
አሳልፎ ለሰጠን እና ለተደራደረብን አራግቺ፣ ሞት የተገባው ይሁን!
4 307
+1
🇺🇸⚡️የኦባማ ላይብረሪ ከዛሬ አሥር ዓመት በኋላ አሜሪካን ለሚጠሉት "መካ" ይሆናል ---- ፕሬዝዳንት ትራምፕ
*-*-*-
በችጋጎ የተገነባው የኦባማ ላይብረሪ፣ አምስት ዓመት ከፈጀ ግንባታ እና $850 ሚሊዮን ዶላር ከወጣበት በኋላ፣ እንደፈረንጆች በሚቀጥለው ዓርብ፣ June 19, 2026, ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ይሆናል።
የሕንፃው ዲዛይን በብዙ የግንባታ ባለሙያዎች ዘንድ ሲኮነን የቆየ ቢሆንም፣ በግንባታው በዓለም የታወቁ ገንቢዎች ከዲዛይን ጀምሮ የተሳተፉበት ነበር።
4 307
🇮🇱🇺🇸🇮🇷 ⚡️ — ከፍተኛ የእስራኤል ባለስልጣን ለቻናል 12 የኢራንን እና የአሜሪካንን ስምምነት በተመለከተ፡
This is a shit deal.
4 307
🇮🇷🤝🇺🇸 ቀን ተቆርጦለታል፣ እሁድ፣ በዕለተ -ሠንበት፣ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ እና እስላማዊ የኢራን ሪፐብሊክ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ በርቀት ሆነው፣ ጦርነቱን የማቆም ስምምነት፣ በፓኪስታን አሸማጋሊነት፣ ይፈራረማሉ። AXIOS
4 307
የሊባኖስ መንግሥት ጦር ሽሽት፣ የአሁኑን ጊዜ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊትን አቋም ያስታውሳል። እነሱስ እሺ፣ በዓለም ስመ ጥር ጦር ሰራዊት ከሆኑት መካከል አንዱ ከሆነው ከእስራኤል ጦር ነው የሚሸሹት። ወቅታዊው የኢትዮጵያ ጦር ግን ከደቡብ ሱዳን አማፂያንም ይሮጣል። ለዚያም ነው፣ ሙሉ ዞን የሚያህል ስፋት ያለው መሬት፣ 'ደቡብ ምዕራብ ክልል' ከሚባለው የኢትዮጵያ ግዛት የተቀደደ ሱሪ እና ሁለት ዓይነት የተቦረተፈ ጫማ ያደረጉ አማፂያን ወቅታዊውን የኢትዮጵያን ሰራዊት አባረው እስከዛሬ እንደያዙ ያሉት።
4 307
የሊባኖስ መንግሥት ጦር ሽሽት፣ የአሁኑን ጊዜ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊትን አቋም ያስታውሳል። እነሱስ እሺ፣ በዓለም ስመ ጥር ጦር ሰራዊት ከሆኑት መካከል አንዱ ከሆነው ከእስራኤል ጦር ነው የሚሸሹት። ወቅታዊው የኢትዮጵያ ጦር ግን ከደቡብ ሱዳን አማፂያንም ይሮጣል። ለዚያም ነው፣ ሙሉ ዞን የሚያህል ስፋት ያለው መሬት፣ 'ደቡብ ምዕራብ ክልል' ከሚባለው የኢትዮጵያ ግዛት የተቀደደ ሱሪ እና ሁለት ዓይነት የተቦረተፈ ጫማ ያደረጉ አማፂያን ወቅታዊውን የኢትዮጵያን ሰራዊት አባረው እስከዛሬ እንደያዙ ያሉት።
4 307
የሊባኖስ መንግሥት ጦር ሽሽት፣ የአሁኑን ጊዜ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊትን አቋም ያስታውሳል። እነሱስ እሺ፣ በዓለም ስመ ጥር ጦር ሰራዊት ከሆኑት መካከል አንዱ ከሆነው ከእስራኤል ጦር ነው የሚሸሹት። ወቅታዊው የኢትዮጵያ ጦር ግን ከደቡብ ሱዳን አማፂያንም ይሮጣል። ለዚያም ነው፣ ሙሉ ዞን የሚያህል ስፋት ያለው መሬት፣ 'ደቡብ ምዕራብ ክልል' ከሚባለው የኢትዮጵያ ግዛት የተቀደደ ሱሪና ሁለት ዓይነት የተቦረተፈ ጫማ ያደረጉ አማፂያን የኢትዮጵያን ሰራዊት እስከዛሬ የያዙት።
4 307
🇮🇱⚡️🇱🇧 እስራኤል ትናንት ምሽት በደቡብ ሊባኖስ ወታደራዊ የእግረኛ ዘመቻ መጀመሯን ተከትሎ፣ የሊባኖስ መንግሥት ጦር ደቡብ ሊባኖስን በመልቀቅ ላይ ነው።
ኢራን፣ ሊባኖስ የስምምነቱ አካል መሆን እንዳለባት በተደጋጋሚ ስትገልፅ ቆይታለች።
4 307
🇵🇰🇮🇷🇺🇸 የፖኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ዋና አደራዳሪ፣ ሻባዝ ሸሪፍ፣ በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ፣ ስንለፋበት የቆየነው መቋጫውን ያገኛል ብለን እናስባለን እና እንረጋጋ እያለ ነው።
ፖኪስታን የፊርማውን ሥነ ስርዓት በዲጂታል እንደምታሳልጥም ተናግሯል። በአካል ተገኝቶ የሚፈረም ነገር አይኖርም። ከዚያም የ60ው ቀን ድርድር በይፋ ይጀመራል።
4 307
🇮🇷⚡️🇺🇸 የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ሰይድ አባስ አራግቺ፣ በኢራን መገናኛ ብዙሃን በLive ቃለ-መጠይቅ በማድረግ ላይ ነው።
የኢራን ሕዝብ ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ ለተከታታይ ቀናቶች፣ አሁን መቶኛ ቀኑን ተሻግሯል፣ በአደባባይ ጦሩን በመደገፍ መሰለፉን ቀጥሏል። እንደሚሰማው ከሆነ፣ ሚንስትሩ፣ ሊፈረም ጫፍ የደረሰው ስምምነት ለኢራን ትልቅ ድል እንደሆነ በመናገር ላይ ይገኛል። አሁን ላይ በስምምነቱ ውስጥ ስላሉ ነጠቦች ብዙ ብዥታዎች እና ግልፅ ያልሆኑ ነገሮች ያሉ መሆኑና የትኛውም ሀገር ግልፅ ለማድረግ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ እየታየ ነው። ጋዜጠኛው፣ አስር ግዜ አራግቺ የስምምነቱን ዝርዝሮች እንዲናገር ቢገፋፋውም፣ ሚንስትሩ ለመናገር ፍቃደኛ እንዳልሆነ ይሰማል።
4 307
🇮🇷🇺🇸 The New York Times አሁን እንደዘገበው፡ የኢራኑ የበላይ መሪ፣ አያቶላህ ሙጅተባ ኸመነይ፣ የስምምነቱን ረቂቅ ከከፍተኛ አማካሪዎቻቸው ጋር እያጤኑት ይገኛል፣ ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል።
4 307
🇺🇸 ኢላን መስክን እንኳን ደስ ያለህ እንበለው ሄደን፣ የዓለም የመጀመሪያው ትሪሊየነር ሆኗል። የዓለም የመጀመሪያው ቢሊየነር አሜሪካዊው ራከፊለር በ1916 ነበር -- The New York Times
4 307
+3
🇪🇹 በአርሲ ኢትዮጵያ ውስጥ፣ በመንግሥት የሚደገፉ ናቸው በተባሉ ታጣቂዎች የተጨፈጨፉት የንፁሃን ሲቪሊያኖች ፎቶ፣ በሶሻል ሚዲያዎች እየወጣ ነው።
ከዚህም በተጨማሪ፣ የመንግሥት አካላት የሆኑ ባለስልጣኖች፣ ለእነዚህ ታጣቂዎች ሕዝቡን ሳይመርጡ በጅምላ እንዲገድሉ ትዕዛዝ ሲሰጡ የሚያሰማ የድምፅ ቅጂም በሚዲያዎች ሲዘዋወር ታይቷል።
በርካታ ሴቶችና ሕፃናት ያለቁበት ይህ ጭፍጨፋ፣ ብሔር እና ሃይማኖት ተኮር ጭፍጨፋ ሲሆን፣ የዐማራ ተወላጆችን እና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮችን ዒላማ ያደረገ እንደነበር የዓይን እማኞች ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ፣ በተለይ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ፣ የንፁሐን ሕዝብ ጭፍጨፋ እየተበራከተ የመጣ ሲሆን፣ እንደ ቀጠናው ተንታኞች፣ እነዚህ ግድያዎች የተቀነባበሩና የገዢው መንግሥት እጅ በስፋት የሚታይባቸው ናቸው ይላሉ።
4 307
🇮🇷🇦🇪ሮይተር ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገው፡
ኤሜሬት ለኢራን $10 ቢሊዮን ዶላር ለመልቀቅ የተስማማች ሲሆን፣ 3 ቢሊየን ዶላሩን በአይሮፕላን ጭና ለኢራን አራግፋለች።
ኤሜሬት፣ የሮይተርን ዘገባ፣ መሠረተ ቢስ እና ውሸት ስትል አጣጥለዋለች።
