en
Feedback
የቀጠናው ተመልካች

የቀጠናው ተመልካች

Open in Telegram

በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
4 330
Subscribers
-624 hours
-317 days
-7230 days
Posts Archive
🇺🇸❌🇮🇷 – የአሜሪካ CENTCOM ሁለት የኢራን ታንከሮችን (M/T Downy እና M/T Stark 1) አበላሽቶ ሦስተኛውን (M/T Kylo) ማስጠሙን ተናገረ። ይህም IRGC በቀጠናው ውስጥ በሁለት የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የባሊስቲክ ሚሳይል በመተኮሱ የተወሰደ የበቀል እርምጃ ነው። ከእነዚህ መርከቦች አንዱ የአውሮፕላን ማጓጓዣ መርከብ ነበር። የአሜሪካ ማዕከላዊ ኮማንድ (CENTCOM) ኃይሎች ዛሬ ቀደም ብሎ ሦስት የኢራን ድፍድፍ ነዳጅ ታንከሮችን አጥቅተዋል፣ ይህም IRGC በቀጠናው ውሃዎች ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ሁለት የአሜሪካ የባሕር ኃይል የጦር መርከቦች ላይ የፀረ-መርከብ ባሊስቲክ ሚሳይሎችን ከተኮሰ በኋላ ነው። ሦስተኛው የኢራን መርከብ በኦማን አቅራቢያ ሰጥሟል።

🇺🇸🇮🇷⚡- ሁለት የኢራን ነዳጅ ታንከሮች፣ በባሕረ ሰላጤው ውስጥ በሚገኘው የኢራን የካርግ ደሴት የባህር ዳርቻ አካባቢ፣ በአራት የአሜሪካ ሚሳይሎች ተመትተዋል። ታስኒም ኒውስ እንደዘገበው፣ ሠራተኞቹ መርከቡን እየለቀቁ ናቸው።

🇺🇸🇮🇷⚡- ሁለት የኢራን ነዳጅ ታንከሮች፣ በባሕረ ሰላጤው ውስጥ በሚገኘው የኢራን የካርግ ደሴት የባህር ዳርቻ አካባቢ፣ በአራት የአሜሪካ ሚሳይሎች ተመትተዋል። ታስኒም ኒውስ እንደዘገበው፣ ሠራተኞቹ መርከቡን እየለቀቁ ናቸው።

🇺🇦🇷🇺🇺🇸 የሩሲያው መሪ የፕረስ ፀሐፊ ፔስኮቭ፣ ፑቲን ለሦስት ቀናት በኪየቭ ላይ ጥቃት እንዳይደረግ አዝዟል። በኪየቭ ላይ ጥቃቶች መታገዳቸው የተከሰተው የአሜሪካ ልዑካኖች የዩክሬን ዋና ከተማን በመጎብኘታቸው ነው። ዛሬ፣ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ዊትኮፍ እና ኩሽነርን ይቀበላል።

🇷🇺🇺🇸 ከድሜትሪቭ፣ ዊትኮፍ እና ኩሽነር ጋር ያለው የፎቶው ምርጥ ክፍል ራሱ ምግብ ቤቱ ነው፣ "ሁሉም ነገር ለድል!" (ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር እንደማለት ነው)፣ በመግቢያው በላይ ባለው
🇷🇺🇺🇸 ከድሜትሪቭ፣ ዊትኮፍ እና ኩሽነር ጋር ያለው የፎቶው ምርጥ ክፍል ራሱ ምግብ ቤቱ ነው፣ "ሁሉም ነገር ለድል!" (ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር እንደማለት ነው)፣ በመግቢያው በላይ ባለው መስታወት ላይ ተጽፎ ይታያል። *-*-** ባለፈው እዛ እያለሁ አይቼዋለሁ፣ አሪፍ ሬስቶራንት ነው፣ በተለይ ፍርፍሩና እንጀራ በፓስታው በጣም ምርጥ ነው። በላ በላ አድርገው ሆዳቸውን ከሞሉ በኋላ ነው መነጋገር። ቀሽር ሻይም አላቸው።

🇮🇱❌🇮🇷 — የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ስለ ኢራን፦
እኛን ሊያጠቁን ይችላሉ፣ እኛም ምላሽ እንሰጣለን። ኢራን በሁሉም ሀገሮች ላይ እየተኮሰች መሆኗን አስተውላችኋል? በማን ላይ የማይተኩሱት? በእስራኤል ላይ ብቻ! ለምን? ምክንያቱም እኔ ጠቅላይ ሚኒስትር እስከሆንኩ ድረስ፣ በዝርዝር ለመግለጽ እንኳን የማልፈልገው፣ ክፉኛ የሚሰባብራቸው ጥቃት ይደርስባቸዋል፣ የምለውን በትክክል ስለሚረዱኝ — ቀድሞውኑ ተዘጋጅቷል።


🇮🇱❌🇵🇸🇮🇷 — የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ፦
በኦክቶበር 7 ክስተት ምክኒያት የመካከለኛው ምሥራቅን ገጽታ እንለውጣለን ብሎ ማን ያምን ነበር? እኔ አምኛለሁ፣ አሳክቼዋለሁ። ዓላማዬ በመጨረሻ የኦክቶፐሱ ጭንቅላት ከሆነችው ከኢራን ጋር መጋጨት፣ እና ክንዶቿን መቁረጥ፣ ማጽዳት እና "የክፋት ዘንግ"ን (axis of evil) ማዳከም ነበር፣ እናም አደረግነው።


🇮🇱❌🇶🇦 — የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በኳታር ላይ፦
ኳታርን አጥቅቻታለሁ — በጦርነቱ ወቅት እንዲሁም በቦንብ ደብድቤያታለሁ፣ በደንብ ነው የመታናት። እነሱ (የእስራኤል የፖለቲካ ተቀናቃኞቹ) ለዚህ አጠቁኝ። ይህ ሁሉ የኳታር ጉዳይ አንድ ትልቅ ግነት ነው። ኳታር ጠላት ሀገር ነች። ምንም ማድረግ የማትችል ሀገር ናት። በዚህ ጉዳይ የምታዝዘው ምንም ነገር የለም። ማዘዝ የማትችል ሀገር ናት።


+1
🇮🇱❌🇱🇧 — የእስራኤል ኃይሎች በደቡብ ሊባኖስ በባኒ ሃያን ውስጥ ግዙፍ የመንደር ማፍረስ ሥራዎችን እያካሄዱ ነው። የጦሩ ቃል አቀባይ፣
ነዋሪው ወደ እነዚህ ሥፍራዎች እንዳይመለስ ነው።

🇺🇦🇷🇺⚡️የትራምፕ ልዑኮች፣ ኩሽነር እና ዊትኮፍ፣ በሞስኮ ደርሰዋል።
+1
🇺🇦🇷🇺⚡️የትራምፕ ልዑኮች፣ ኩሽነር እና ዊትኮፍ፣ በሞስኮ ደርሰዋል።

🇺🇦⚡️🇷🇺 የአሜሪካ መንግሥት ወደ ሩሲያና ዩክሬን ሊልክ ላሰበው የአደራዳሪዎች ቡድን ሲባል በሁሉም ግንባሮች ለሦስት ቀናት የሚቆይ የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ከሰዓታት በፊት ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆ
🇺🇦⚡️🇷🇺 የአሜሪካ መንግሥት ወደ ሩሲያና ዩክሬን ሊልክ ላሰበው የአደራዳሪዎች ቡድን ሲባል በሁሉም ግንባሮች ለሦስት ቀናት የሚቆይ የተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ከሰዓታት በፊት ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆንምና ዩክሬን ያንን እንደምትተገብር ብትናገርም፣ ሩሲያ የተኩስ አቁሙን ችላ ብላ በአሁኑ ሰዓት፣ ኪየቭ ላይ ትኩረቷን አድርጋ፣ በከፍተኛ ሁኔታ ዩክሬንን እየደበደበቻት ትገኛለች።

🇰🇷🇺🇸⚡🇮🇷 ደቡብ ኮሪያ በሆርሙዝ ወሽመጥ ውስጥ ወታደሮቿን ለማሰማራት እያቀደች ነው። የደቡብ ኮሪያ ሚዲያ የሀገሪቱን የመከላከያ ሚኒስቴር ባለሥልጣናትን በመጥቀስ፣ ሲኦል አሜሪካን ለመደገፍ
🇰🇷🇺🇸⚡🇮🇷 ደቡብ ኮሪያ በሆርሙዝ ወሽመጥ ውስጥ ወታደሮቿን ለማሰማራት እያቀደች ነው። የደቡብ ኮሪያ ሚዲያ የሀገሪቱን የመከላከያ ሚኒስቴር ባለሥልጣናትን በመጥቀስ፣ ሲኦል አሜሪካን ለመደገፍ የባሕር ኃይሎቿን ወደ ሆርሙዝ ወሽመጥ ለማሰማራት እያሰበች መሆኑን ዘግቧል። * ኢራን፣ ደቡብ ኮሪያ ይህን ካደረገች መዘዝ እንደሚያጋጥማት አስጠንቅቃለች። *-*-*- ለዚህ የደቡብ ኮሪያ ድንፋታ አንድ የኢራን ባለሥልጣን በሰጠው ምላሽ፡
ጃፓንስ እሺ ካራቴ ታውቃለች፣ ሰሜን ኮሪያም ኒውክሊየር አላት፣ አንቺ… ቆይ እስኪ፣ ምን ይዘሽ ልትመጪ ነው ወደ ሜዳው ኮሪያ? እስኪ ልጠይቅሽ፣ ሆንዳሽን እየሰራሽ በሠላም አትኖሪም?

🇮🇷⚡️🇺🇸 'የአሜሪካ ህዝብ በኢራን ላይ ለውጥ (Resolution) መቼ ይጠብቅ?' ትራምፕ፦ 'ነውጥ (Revolution)?' 'ለውጥ' ትራምፕ፦ 'እኔ ነውጥ የበለጠ አስደሳች ነው ብዬ አስባለሁ።'

🇺🇦🇷🇺⚡️ — የዩክሬን ወታደሮች በመላው የጦር ግንባሮች ከሴፕቴምበር 5 እኩለ ሌሊት (ከ17 ደቂቃዎች በፊት) እስከ ሴፕቴምበር 8 ምሽት 11:59 ድረስ የተኩስ አቁም ትዕዛዝ እንዲያከብሩ ታዝ
🇺🇦🇷🇺⚡️ — የዩክሬን ወታደሮች በመላው የጦር ግንባሮች ከሴፕቴምበር 5 እኩለ ሌሊት (ከ17 ደቂቃዎች በፊት) እስከ ሴፕቴምበር 8 ምሽት 11:59 ድረስ የተኩስ አቁም ትዕዛዝ እንዲያከብሩ ታዝዘዋል፣ እንደ ዩክሬንስካ ፕራቭዳ ዘገባ። ጊዜያዊ የውጊያ ማቆም የመጣው የአሜሪካ መልዕክተኞች ስቲቭ ዊትኮፍ እና ጃሬድ ኩሽነር በሚቀጥሉት ቀናት ኪየቭ እና ሞስኮን ለመጎብኘት በዝግጅት ላይ ባሉበት ወቅት ነው። *-*-*- በሩን ከፈት ከፈት አድርጉላቸው፣ አሜሪካዊያን እየመጡ ነው።

+3
🇺🇦🇷🇺⚡️የSBU (የዩክሬን የደህንነት አገልግሎት) ማዕከላዊ ሕንፃ፣ ከጥቃት በኋላ በኪየቭ በእሳት እየተቃጠለ ነው። ሩሲያ፣ የዩክሬን የደህንነት ኃላፊን ቢሮ፣ ኃላፊው ወደ ቢሮው ከገባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ በድሮን ጥቃት ሰንዝራበታለች ተብሏል። እስካሁን ይኑር ይሙት አልታወቀም። ▪️ዘሌንስኪ የሩሲያ ድሮን የSBUን ማዕከላዊ ሕንፃ መምታቱን እና፣ በተለይም የኤጀንሲውን ኃላፊ ዒላማ ማድረጉን በጽኑ አውግዟል። ለዚህ ጥቃት ሩሲያ እስካሁን ሃላፊነቱን አልወሰደችም። ዩክሬናዉያን አክቲቪስቶች በበኩላቸው፣ ጥቃቱ በሩሲያ ሳይሆን በዩክሬን ሌላኛው የደህንነት ተቋም (GUR) አባላት የተፈጸመ ነው በማለት ላይ ናቸው። ይህን እያሉ ያሉት ከሰሞኑ በሁለቱ ተቋሞች መካከል በኪየቭ በመሳሪያ ጭምር በተነሳ ግጭት ከሁለቱም ወገኖች በኩል በርካታ አባላቶች መገዳደላቸውን በመጥቀስ ነው።

⚡️🇮🇱⚡️🌎 የቀድሞው የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤኔት፦
ሙሉ በሙሉ የወደመውን ዓለም አቀፋዊ ገጽታችንን ማስተካከል እፈልጋለሁ። እዚህ ጠዋት ሲነቁ ውሾች እንደሚያገቡ ራባዮች (የአይሁድ የሐይማኖት አባቶች) እብድ ነገሮችን የሚናገሩ ሚኒስትሮች አሉን።

🇸🇦🇾🇪🇺🇸 የመን፦ የሳዑዲ ተቀጣሪ ወታደሮች እና ቤተሰቦቻቸው፣ የሁቲ አንሳር አላህ ቁጥጥር ከወሰደባቸው በኋላ፣ ከማድሪያ እና ከማቅባና ከተሞች እንዲሁም በታይዝ ግዛት ከሚገኘው ከካዳ አካባቢ እየሸሹ ነው።

🇺🇸🇸🇦የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፦
ለሳዑዲ አረቢያ $1 ቢሊዮን ዶላር ተተኳሽ ጥይት ለመሸጥ ፈቃድ ተሰጥቷል።
*-**** አሜሪካኖች ጠባያቸው፣ መሳሪያ ልግዛችሁ ብለህ ስትላቸው አይሸጡልህም። ብዙ ደጅ ያስጠኑሀል። ለግዢው ልታወጣ ካሰብከው በላይ እነሱን በማሳመን ዙሪያ ለኽድሚያው የምታወጣው ወጪ የትየለሌ ነው። የበጉ፣ የፍየሉ ዋጋ ሳይደመር ለጫት የምታወጣው ወጪ ብቻ ይነቅልሃል።

🇺🇸🇸🇾⚡️ — ፕሬዝዳንት ትራምፕ፦
በአሁኑ ጊዜ የቧንቧ መስመሮች እየተገነቡ ነው። በሶሪያ የሚያልፈው መንገድ እየተገነባ ነው፤ በእውነቱ ክፍት ነው። ሰዎች በሶሪያ በኩል የጭነት መኪናዎችን እየወሰዱ ነው — ዘይት የያዙ ግዙፍ የጭነት መኪናዎች። ለሆርሙዝ ወንዝ ብዙ አማራጮች እየተሰሩ ነው። የሆርሙዝ መተላለፊያ መንገድ እንደበፊቱ አይደለም።

🫂 🇸🇾 በሶሪያ ውስጥ ስኬታማ ወደ ሀገር ፍልሰት ከውጭ የተመለሱ ሶሪያውያን 1,795,641 (ከዲሴምበር፣ 2024 ጀምሮ) ከቱርክ 704,378 እስከ ሴፕቴምበር፣ 2026 ድረስ። በአውሮፓ የሚገኙ
🫂 🇸🇾 በሶሪያ ውስጥ ስኬታማ ወደ ሀገር ፍልሰት ከውጭ የተመለሱ ሶሪያውያን 1,795,641 (ከዲሴምበር፣ 2024 ጀምሮ) ከቱርክ 704,378 እስከ ሴፕቴምበር፣ 2026 ድረስ። በአውሮፓ የሚገኙ ሶሪያዊያን በቅርቡ ከፍተኛ የመመለስ ዝንባሌ አሳይተዋል። *-*-** ሀገሩ ሠላም ከሆነለት መመለስ የማይፈልግ ማንም እንደሌለ ሶሪያ ማሳያ ናት። የማግኘት የማጣት ጉዳይ አይደለም ቁም ነገሩ። ቁም ነገሩ ተኝቶ ማደር፣ ወጥቶ መግባት ነው፣ ሠላም ነው! በለውጥ ሠላም እንደሚገኝም ሶሪያ አሳይታለች!