en
Feedback
LOGOS

LOGOS

Open in Telegram

🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
262
Subscribers
+324 hours
+137 days
+2830 days
Posts Archive
sticker.webp0.28 KB

💥 ከማክስ ሉካዶ መፅሀፍ አንድ ሃሳብ ወስጄ ላካፍላችሁ፡ 👉 እስቲ ዛሬ ኢየሱስ እኔን ቢሆን ብላችሁ አስቡ‼️ ለ24 ሰዐታት ኢየሱስ እኔን ሆነ ወይም የእኔ ልብ በእርሱ ልብ ተተካ ብላችሁ አስቡ። አስተውሉ፡ በህይወታችሁ ሌላ ምንም አልተቀየረም፡ የእናንተ አለቃ የእርሱ አለቃ ሆኗል፣ የእናንተ ቤተሰብ የእርሱ ቤተሰብ ሆኗል፣ የሚያማችሁ ከሆነም የተቀየረ ነገር የለም፣ የዛሬ እቅዳችሁ እንዳለ ነው፣ ቀጠሮዎቻችሁ አልተቀየሩም። ብቻ ምንም ከህይወታችሁ አልተቀየረም። የተቀየረው አንድ ነገር ብቻ ነው.. የእናንተ ልብ ወጥቶ የኢየሱስ ልብ ገብቶላችኋል። ስለዚህ የእርሱን ሃሳብ ብቻ እየኖራችሁ ነው። 👉 በዚህ ቀን በህይወታችሁ ምን አይነት ለውጥ የሚመጣ ይመስላችኋል? ኢየሱስ ከጓደኞቻችሁ፣ ከቤተሰቦቻችሁ፣ ከስራ አጋኖቻችሁ ጋር የተለየ አይነት ግንኙነት ይመሠርት ይሆን? ይቅር ያላላችኋቸውን ይቅር ይል ይሆን? እነርሱስ ለውጥ ያስውሉባችሁ ይሆን? ከዛሬ እቅዶቻችሁ የትኞቹን ይተው ይሆን? ከያዛችኋቸው ቀጠሮዎችስ የቱን ይሰርዝ ይሆን? ወይስ መያዝ የነበረባችሁ ያልያዛችሁትን እቅድ ይጨምር ይሆን? መንገዳችሁ እንዴት ይሆን ይሆን? * እስቲ ቆም ብላችሁ በህይወታችሁ በእናንተ ቦታ ኢየሱስ ቢሆን ኖሮ የማይኖራቸውን ሰዐታት፣ የማያስባቸውን ሃሳቦች፣ የማያደርጋቸውን ድርጊቶች፣ የማይናገራቸውን ንግግሮች፣ የማይሰማቸውን ወሬዎች አስቡ። 👉ኢየሱስን መምሰል እኮ ይሄ ነው! ኢየሱስ የማይኖራቸውን ህይወቶች ከውስጣችን ማስወገድ። ህይወታችንን ኢየሱስ እንደሚኖረው አድርጎ በጥንቃቄ መኖር። ❤ 📖📖 1 ቆሮንቶስ 2:16 📖📖❤ “... እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።” ✍️https://t.me/mere_protestantism

👉🏻“ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን፤”   — 1ኛ ዮሐንስ 1፥2             ፨ኢየሱስ 📌ፍጥረት እግዚአብሔር ማን እንደሆነ ያውቅ ዘንድ 📌የፍጥረት በኩር ወደ ፍጥረት ዘለቀ ፣ 📌ሕይወት ወደ ጊዜ ገባ ፣ 📌ዘለዓለም በጠባብ ደረት ፣ በአጭር ቁመት ተወሰነ ፣ 📌ብርሃን ስጋ ለበሰ ፣ 📌የእግዚአብሔር ማዳን ተገለጠች ፣ 📌የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ መጣ ፣ 📌በፅድቁ ፅድቅ በረታች ፣ 📌የገቡበት ሁሉ የሚያርፉበት የበጎች በር ተከፈተ ፣ 📌የተጠጉትን ሕያዋን የሚያደርግ ሕያው ድንጋይ ታየ ፣ 📌የንጋቱ ኮከብ አበራ ፣ 📌 የሀጢአ ተኞች ወዳጅ ቀረበ ፣ 📌ከስሞች ሁሉ በላይ ስም ተሰየመ ፣ 📌የማይፈርስ ቤተመቅደስ ቆመ ፣ 📌የማይሻር መስዋዕት ቀረበ ፣ 📌ከአብ ዘንድ ያለልን ጠበቃ ታወቀ ፣ 📌በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህን ታወጀ ፣ 📌የእግዚአብሔር ክብር ማንፀባረቅ ወረደ ፣ 📌የባህሪው ምሳሌ መልክ ያዘ ፣ 📌የማይታይ አምላክ ምሳሌ ታየ ፣ 📌የፅድቅ ፀሐይ ወጣ ፣ 📌 እግዚአብሔርን የመምሰል ምስጢር ተገለጠ ፣ 📌ወደ አብ የሚያደርስ መንገድ ተሰጠ ፣ 📌የፍጥረት ደራሲ ስጋ ሆነ ፣ 📌ከርሱ የጠጣ የማይጠማበት የዘለዓለም ውሃ ፈለቀ ፣ 📌የሕይወት እንጀራ ከሰማይ ወረደ ፣ 📌የአለምን ሀጢአያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ መጣ ፣ 📌ታርዶ የቆመ በግ ተገለጠ ፣ የኃጢኣታችን ማስተሰሪያ ታተመ ፣ 📌 ሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ ። 📌የእግዚአብሔር ልጅ ፣ የሰው ልጅ ፣ ፃድቅ ፈራጅ ፣ 📌የማዕዘን ራስ ፣ የይሁዳ አንበሳ ፣ የሰላም ልዑል ፣ 📌ፃድቅ መካር ፣ ሃያል አምላክ ፣ የዘለዓለም አባት የሰላም  አለቃ ፣ 📌 የእግዚአብሔር ጥበብ ተገለጠ።               

Story

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1:21 ​"ከፍተኛው የብስለት ደረጃ ከክርስቶስ ውጪ ሌላ ምንም ፍላጎት፣ ምንም ሀሳብ፣ ምንም ምኞት ሳይኖርክ ሲቀር ነው፤ ለክርስቶስ ሲባል መሞት ታላቅ ደስታ እንደሆነ ሲሰማክ ለክርስቶስ ሲባል በድህነት፣ በስቃይ፣ በንቀትና በመከራ ውስጥ መኖር ጣፋጭ ሆኖ ሲታይክ፣ ጌታህ እስከከበረ ድረስ በአንተ ላይ ምን እንደሚደርስ ግድ ሳይሰጥህ ሲቀር እንዲሁም እንደደረቀ ቅጠል በነፋስ ብትወሰድም የጌታ እጅ እንደ ፈቃዱ እየመራክ መሆኑን እስካወክ ድረስ ወዴት እየሄድክ እንደሆነ ግድ በማይሰጥህ ሁኔታ ውስጥ ስትሆን ነው።"         ቻርለስ ሰፐርጀን

ቅዱስ አውግስጢኖስ "ኀጢአት ማለት ቅደም ተከተሉ የተዛባ ፍቅር ነው" ብሎ እንደተረጐመው፣ ቅድስና ማለትም ቅደም ተከተሉን የጠበቀ ፍቅር ነው። ርሱ አስቀድሞ ወድዶኛልና እኔም ደግሞ እወደዋለሁ የምንልበት የፍቅር ቋንቋችን ቅድስና ይባላል። ቅድስና የሌለው ፍቅር ዱዳ ነው። ፍቅር የሌለው ቅድስናም ግብዝነት ነው። ✍️ ምናሴ ይርጉ ቆላስይስ 2:20-23 20-21 #ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ #ከክርስቶስ ጋር #ከሞታችሁ፥ 22 እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት፦ #“አትያዝ”፥ #“አትቅመስ”፥ #“አትንካ”፡ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና። 23 ይህ እንደ ገዛ #ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቆን ጥበብ ያለው ይመስላል፥ ነገር ግን ሥጋ ያለ ልክ እንዳይጠግብ ለመከልከል ምንም #አይጠቅምም።

ዮሐንስ 10:27-29 27 በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ #ይከተሉኝማል፤ 28 እኔም #የዘላለም #ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ #ለዘላለምም #አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም #አይነጥቃቸውም። 29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ #ከአባቴም እጅ #ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም። ሮሜ 6:1-2 1 እንግዲህ ምን እንላለን? #ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን? 2 አይደለም። #ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? አዳም በኔ ውስጥ ሞቷል፤ ህያው ሆኖ አይኖርም። ኢየሱስ ግን በኔ ውስጥ ይኖራል፤ ህያው ሆኖ ለዘላለም ይኖራል... አዳም በኔ እንደሞተ ብቻ ሳይሆን; እኔ በአዳም ውስጥም ሞቼአለሁ፤ አዳም በኔ, እኔም በአዳም ውስጥ ህብረት የለንም… በኔ ኢየሱስ እንደሚኖር ብቻ ሳይሆን; በኢየሱስ ውስጥም እኖራለሁ፤ እኔ በኢየሱስ, ኢየሱስ በኔ ፍጹም በሆነ አንድነት እንደምንኖር፤ እንዲሁ በኔና በመጀመሪያው ሰው መካከል ፍጹም በሆነ መለየት ተለያይተናል… ከአዳም ባለመሆኔ ከሞት፣ ከኩነኔ፣  ከመጥፋት፣ ከአሮጌ ሰውነት ሁሉ ጋር ተቆራርጬአለሁ… በኢየሱስ በመሆኔ ከህይወት፣ ከጽድቅ፣ ከአለመጥፋት፣ ከአዲሱ ሰውነት  ጋር በዘላለም ቃልኪዳን  ታስሬአለሁ.... አዳማዊ ማንነቴን  በሃጢአት በመወለድ ያገኘሁትን በመስቀል ለመቸንከር አሮጌ ማንነቴን ከአዳም ጋር ሰቀልሁ፤ ስጋዊ፣ አለማዊና ዲያብሎሳዊ የጽድቅ መሳሪያዎቼን ከእርሱ ክበብ ስወጣ ሁሉንም ቀበርኋቸው…. መሲህያዊ ማንነቴን ከሰማያዊ ልደት አገኘሁ፤ ከቅቡእ አምላክ ጸጋ  በመካፈሌ የእርሱን መልክ በሙላት እስክይዝ ድረስ  በመንፈሱ ሃይል እየተጋደልሁ ርዝራዥ አዳማዊነቴን ዘወትር እሰቅላለሁ…. በመጀመሪያው አዳም  ከሆነብኝ ይልቅ በኋለኛው አዳም የሆነልኝ እጅግ ይበዛል… ከራቅሁት ርቀት ይልቅ በኋለኛው ሰው የቀረብሁት ቅሩብነት እጅግ ድንቅ ነው…  ከተቆጠረልኝ በደል ይልቅ የተቆጠረልኝ ጽድቅ….  ከገባሁበት  ጉስቁልና ይልቅ የ ወጣሁበት ከፍታ.... በተፈጥሮ ከነበርሁበት  ጭለማ ይልቅ በልእለ ተፈጥሮ የበራልኝ የብርሃን ድምቀት.... ከታወጀብኝ  ከሞት ኩነኔ ይልቅ የታወጀልኝ የጽድቅ ብዛቱ በቀላሉ እንዲህ ተብሎ የማይነገር ግሩም መለኮታዊ ችሮታ የተገለጠበት  ነው…. ✍️TTL (https://t.me/LOGOSJO1)

1 ጴጥሮስ 1:18-19,23 18-19 ከአባቶቻችሁ ከወረሳችሁት ከከንቱ ኑሮአችሁ በሚያልፍ ነገር በብር ወይም በወርቅ ሳይሆን፥ ነውርና እድፍ እንደ ሌለው እንደ በግ ደም በክቡር የክርስቶስ ደም እንደ ተዋጃችሁ ታውቃላችሁ። 23 ዳግመኛ #የተወለዳችሁት #ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ #በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል #ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ። 🚧 መቀደስ #ከልጅነት አይቀድምም ፤ ልጅነቱን ያለወቀ ሰው ልቀድስ ቢል እንኳ አይቀደስም ፤ #“ከፈረሱ ጋሪ” እንደሚል የሀገሬ ሰው ፤ #ጋሪው #ከፈረስ ከቀደመ መሰነካከል ነው እንጂ ትርፉ ፣ አንድ እርምጃ አያስኬድም ፤ ከራሳችን የሚንፈጥረው ቅድስናም የለንም ፤ በውሳጣችን ካለው ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ከተቀበልነው የቅድስና 🍓ዘር የተነሳ ነው እለት እለት የሚንቀደሰው ! 😁 ሲጃራ 🚬  pocket ላይ “ ማጨስ ሳንባን ይጎዳል” ተብሎ  ሰው ሲጃራን ያጨሳል ! ግን ይህ ሰው ወደ ክርስቶስ ስመጣ ፣ ሳንባን ይጎዳል ተብሎ ሳይሆን ሲጃራን የሚያቆመው ፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ከተቀበለው ከቅድስና ዘር ነው ! እናም የሚበልጠውን ክርስቶስ ስለያዘ ነው ! 🗯️🗯️ ለዚህም ነው ጳውሎስ የቆላስይስ ሰዎችን እንደዚህ የሚላቸው ፦ ቆላስይስ 2:20-23 20-21 ከዓለማዊ ከመጀመሪያ ትምህርት ርቃችሁ ከክርስቶስ ጋር #ከሞታችሁ፥ 22 እንደ ሰው ሥርዓትና ትምህርት፦ #“አትያዝ”፥ #“አትቅመስ”፥ #“አትንካ”፡ ለሚሉት ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ሾለ ምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በመደረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና። 23 ይህ እንደ ገዛ ፈቃድህ በማምለክና በትሕትና ሥጋንም በመጨቆን #ጥበብ ያለው ይመስላል፥ ነገር ግን ሥጋ ያለ ልክ እንዳይጠግብ ለመከልከል #ምንም አይጠቅምም። 🐬አሳ ማንነቱ መዋኘት ነው ፤ አትወኝ ብትለውም ይዋኛል 🚧 ብቻ  ከውሃ ውስጥ አይውጣ እንጂ! 🚧እኛም የክርስቶስ ዘር በውስጣችን ይኑር እንጂ ፤ እለት እለት #መቀደስ ማንነታችን ነው !  🚧ብቻ ከፀጋው እንዳንወጣ ! ሮሜ 6:6 6 ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና። #መቀደስ ከውስጥ እንጂ በውጫዊ ግፊት አይደለም ፤ #ፍቅር ያዋረደውን #ክርስቶስን እያያን #እንቀደሳለን ፤ በፀጋው ሆነን #እንቀደሳለን #በራስ ጥረት ሰው አይቀደስም ! ✍️ወንድም አሻግሬ

#ኢየሱስ_ማን ነው? ኢየሱስ ከዘላለም ዘመናት በፊት በመጀመሪያው የነበረ ጅማሬ የሌለው አለማት የተፈጠሩበት ቃል ነው!! 👉 ኢየሱስ የማይታየው እግ/ር የሚታይ አካል ነው!! 👉 ኢየሱስ በእግዚአብሔር ዘንድ የነበረ እግ/ር ነው!! 👉 ኢየሱስ የእባቡን ልሾ የቀጠቀጠ የሴቲቱ ዘር ነው!! 👉 ኢየሱስ ከሀጥያት ጥፋት የዳንበት ባለ አንድ በር የኖህ መርከብ ነው!! 👉 ኢየሱስ አሕዛብ የተባረከበት የአብርሀም ዘር ነው!! 👉 ኢየሱስ እግዚአብሔር ወደ ሰው የወረደበት ያዕቆብ በህልም ያየው መሰላል ነው!! 👍 ኢየሱስ ጅማሬ እና ፍጻሜ የሌለው እንደ መልከጸዴቅ የሆነ ንጉስ እና ካህን ነው!! 👉 ኢየሱስ ያለቦታው በተራራ የተገኘ ቀንዱ  በሀረግ የተያዘ የመስዋዕት በግ ነው!! 👉 ኢየሱስ በምድረበዳ ከሰማይ የወረደ የህይወት እንጀራ ነው!! 👉 ኢየሱስ በትንሳዔው ያፀደቀን ከይሁዳ ነገድ የሆነ አንበሳ ነው!! 👉 ኢየሱስ እኛን ማደሪያዎቹ ያደረገ የመቅደሱ ስርዓት ፍፃሜ ነው!! 👉 ኢየሱስ ነፍሱን በፈቃዱ አሳልፎ የሰጠን አጥንቱ ያልተሰበረ በግ ነው!! 👉 ኢየሱስ የህይወት ውሀ ምንጭ የሆነ የጥም ማርኪያ አለት ነው!! 👉 ኢየሱስ ስለበደላችን ስጋው ከሰፈር ውጭ መስዋዕት ሆኖ የተቃጠለ የእግዚአብሔር በግ ነው!! 👉 ኢየሱስ አባቱን ታዞ ወደ ወንድሞቹ የሄደ፣ በአባቱ የሚወደድ፣ ወንድሞቹ ያልተቀበሉት፣ በባሪያ ዋጋ በይሁዳ የተሸጠ፣ ያለ ሀጥያቱ የተከሰሰ፣ በሀሰት የተመሰከረበት፣ በመከራው ታዳጊ የሆነ፣ ወንድሞቹ የሰገዱለት ዮሴፍ ነው!! 👉 ኢየሱስ በሰይጣን ተፈትኖ ያልወደቀ ሗለኛው አዳም ነው!! 👉 ኢየሱስ በምድረበዳ ሾለ ሰዎች መዳን በእባብ ምሳሌ የተሰቀለ የናስ እባብ ነው!! 👉 ኢየሱስ እስራኤላውያንን የተስፋይቱን ምድር ያስወረሰ ከሙሴ ሼር ያደገ ኢያሱ ነው!! 👉 ኢየሱስ ከኃጥያት ባርነት የተቤዤን ቡዔዛችን ነው!! 👉 ኢየሱስ መንግሥቱ ለዘለዓለም የሆነች የዳዊት ልጅ ነው!! 👉 ኢየሱስ የኃጥያታችን ስርየት ነው!! 👉 ኢየሱስ የነውራችን እድፍ ማስወገጃ ነው!! 👉 ኢየሱስ የበደላችን መንጫ ነው!! 👉 ኢየሱስ የአመፃችን ፍርድ ጠበቃ ነው!! 👉 ኢየሱስ ለእዳችን ክስ የነፍሳችን ቤዛ ነው!! 👉 ኢየሱስ ስጋ የሆነ ቃል ነው!! 👉 ኢየሱስ ሰው የሆነ አምላክ ነው!! 👉 ኢየሱስ ህይወት ሰጪ ህይወት ነው!! 👍 ኢየሱስ የባሪያን መልክ የያዘ ጌታ ነው!! 👉 ኢየሱስ የህማም ሰው የሆነ ፈውስ ነው!! 👉 ኢየሱስ እኛን ለማክበር የተዋረደ ክቡር ነው!! 👉 ኢየሱስ እኛ የእግዚአብሔር ፅድቅ እንድንሆን ኃጥያት የሆነ ፅድቅ ነው!! ♥ ኢየሱስ እግዚአብሔር ፍቅሩን ለአለም የገለጸበት የእግዚአብሔር የፍቅር ቋንቋ ነው!! ♥ ኢየሱስ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል እግዚአብሔርና ሰው ሆኖ የገባ መካከለኛ ነው!! ♥ ኢየሱስ የእግዚአብሔርና የሰው መግባቢያ ቋንቋ ነው!! 👉 ኢየሱስ ሾለ እኛ የተጨነቀ እረፍታችን ነው!! 👉 ኢየሱስ ለእኛ እፎይታ የታወከ ሰላማችን ነው!! 👉 ኢየሱስ ውድ የህይወት ዋጋ ከፍሎ ለክብር ያጫት የቤተ ክርስቲያን ሙሽራ ነው!! . . . 👉 ኢየሱስ ተነግሮ የማይሰለች የምስራች ነው!!     
         ❤ ኢየሱስ ❤
✍️TTG መልካም ምሽት❤️❤️

በህይወት ምልልስ ውስጥ ብዙ ኃላፊነቶች፣ ፈተናዎች ሊገጥምህ ይችላል። እግዚአብሔር ግን በራስህ ብቻ እንድንተማመን አይፈልግም። ክርስቶስ ለሚገጥም ማንኛውም ነገር ሁሉ ኃይልን ይሰጥሀል። ሁሉን መቻል
በህይወት ምልልስ ውስጥ ብዙ ኃላፊነቶች፣ ፈተናዎች  ሊገጥምህ ይችላል። እግዚአብሔር ግን በራስህ ብቻ እንድንተማመን አይፈልግም። ክርስቶስ ለሚገጥም ማንኛውም ነገር  ሁሉ ኃይልን  ይሰጥሀል። ሁሉን መቻል ማለት የፈለከውን ሁሉ በራስህ ኃይል ታደርጋለህ ማለት አይደለም። ይልቁንም በክርስቶስ ኃይል ፈተናን ማለፍ፣ ታማኝ ሆኖ መኖር ማለት ነው። ዛሬ የሳምንቱን ስትጀም  በፍርሃት ወይም በጭንቀት ሳይሆን ክርስቶስ ከአንተ ጋር እንዳለ በመታመን ጀምር። ምንም ዓይነት ሸክም ወይም ፈተና ቢመጣ ብቻህን አይደለህም።
ፊልጵስዩስ 4:13 ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
✍️ #tesfa #hope

Repost from Heart of Christ
✍️መታዘዝ ማለት ለራስህ ስሜት ጨክነህ ለእግዚአብሔር ፈቃድ እሽ ማለት ነው። አብርሃም ከቤቱ እስማኤልን ስያሰናብት ልቡ አዝኖ ነበር በልጁ በእስማኤል መጨከን ከብዶት ነበር
“ይህም ነገር በአብርሃም ዘንድ ስለ ልጁ እጅግ ችግር ሆነበት።” ዘፍጥረት 21፥11
ግን አብርሃም ይስሐቅን እግዚአብሔር ሰዋልኝ ባለው ጊዜ ለምን አልተከራከረም? ለምንስ ልቡ አልጨከነም? በተስፋ ያገኘውን የእርጅና ጊዜ ምርኩዙን ይስሐቅን የብዙ ጊዜ ጸሎቱን በብዙ ጥበቃ እና ትዕግሥት ወደ ቤቱ የመጣውን ይስሐቁን ሰዋልኝ ስለው ለምን አይሆንም አላለውም? ለእስማኤል የራራው የአባትነት ልቡ በይስሐቅ ለምን ዝም አለ? ለምን መሰላችሁ....
ጉዳዩ ስለ ልጁ አይደለም ጉዳዩ ስለ ጠያቂው ታላቅነት ነው።ጠያቂው እግዚአብሔር ነዋ።
እግዚአብሔር ስጠይቅ ርህራሄ ትዕዛዝ ይሆናል። እግዚአብሔር ስጠይቅ ፍቅር መታዘዝ ይሆናል። እግዚአብሔር ስጠይቅ ድጋሚ ማሰብ ክህደት ይሆናል። የጥያቄው ክብደት የሚለካው በጠያቂው ማንነት ነው። አብርሃም ለእስማኤል አዝኖ ለይስሐቅ የጨከነው ለጠያቂው ያለው ፍቅር ለልጁ ካለው ፍቅር ሰለበለጠ ነው።
እግዚአብሔር ስጠይቅ ድጋሚ ማሰብ አለመታዘዝ ነው።
አብርሃም ይስሐቅን ይዞ ወደ ተራራው ስወጣ ልጁን ስለጠላው ሳይሆን አምላኩን ስለወደደው ነበር። ዛሬ እኛስ ውድ ነው የምንለውን ነገር ለእግዚአብሔር በመታዘዝ እንሰዋ ይሆን? ጊዜያችንን፣ልጅነታችንን፣ነገያችንን፣ውድ ነው ማንንም አላስነካም ያልነውን፣በቤታችን ውድ ነው ያልነውን ለእርሱ እንተው ይሆን? እግዚአብሔር አምጣው የሚለን ነገር ያለ እርሱ መኖር አልችልም የምንለውን ነገራችንን ነው።
እግዚአብሔር የሚጠይቀን ያጣነውን የሌለንን ነገር ሳይሆን አጥብቀን የያዝነውን አንለቅም ያልነውን ነው
እግዚአብሔር ይስሐቅን የፈለገው እንዲሞት ሳይሆን በአብርሃም ልብ ውስጥ ያለውን የራሱን ቦታ ለማየት ነው። ወዳጆቼ እግዚአብሔር አንዳች ነገር ፈልጎ ሰዋልኝ ባለን ጊዜ በሙሉ መታዘዝ መሰዋት ይሁንልን። እርሱን የምንከለክለው ነገር አይኑረን። ጌታ ሆይ ዛሬ እንደ አብርሃም እነሆኝ የምልበትን ልብ ስጠኝ። ውድ ነው ማንንም አላስነካውም ብዬ አጥብቀ የያዝኩትን በልቤ ዙፋን ያስቀመጥኩትን ይስሐቄን እንድሰዋልህ ልቤን በመታዘዝ መንፈስ ባርክልኝ። ለዓለም ጉዳይ የምሮጥበትን የራሴን ስም ለማስጠራት የምለፋበትን ጊዜዬን ወስደህ አንተን ለማገልገልና ድምፅህን ለመስማት እንድጠቀም እርዳኝ። ጌታ ሆይ እውቀቴን ለአንተ ጊዜየን ለቃልህ ነገን ደግሞ ለታማኝነትህ አሳልፌ እሰጣለሁ። መታዘዝ ከመስዋዕት እንደ ሚበልጥ በምክንያት ከምከራከር ልብ ይልቅ ለቃልህ የሚገዛ የትህትና መንፈስ በውስጠ አሳድር። የምሳሳለትን ሁሉ በአንተ እጅ ማኖር ይሁንልኝ። ለአንተ እሽታን አስተምረኝ። በአብርሃም እምነትና መታዘዝ ባርከን።🙌

1 ቆሮንቶስ 1:8-9 8 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትገኙ እርሱ እስከ መጨረሻው ድረስ ##አጽንቶ ##ይጠብቃችኋል። 9 ወደ ልጁ፣ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ
1 ቆሮንቶስ 1:8-9 8 በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትገኙ እርሱ እስከ መጨረሻው ድረስ ##አጽንቶ ##ይጠብቃችኋል። 9 ወደ ልጁ፣ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር ##የታመነ ነው። ይሁዳ 1:24-25 24 ##እንዳትወድቁ ##ሊጠብቃችሁና ያለ ነቀፋና በደስታ በክብሩ ፊት ሊያቀርባችሁ ለሚችለው፣ 25 እርሱ ብቻ አዳኛችን ለሆነው አምላክ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ከዘመናት ሁሉ በፊት፣ አሁንና እስከ ዘላለምም ድረስ ክብር፣ ግርማ፣ ኀይልና ሥልጣን ይሁን፤ አሜን። 1 ጴጥሮስ 5:10 10 በክርስቶስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ፣ ለጥቂት ጊዜ መከራ ከተቀበላችሁ በኋላ እርሱ ራሱ መልሶ ያበረታችኋል፤ ##አጽንቶም #ያቆማችኋል። 2 ጢሞቴዎስ 1:9 9 እኛ ##ስላደረግነው ##አንዳች ነገር ሳይሆን፣ ከዕቅዱና ከጸጋው የተነሣ ያዳነን፣ ወደ ቅዱስ ሕይወትም የጠራን እርሱ ነው። ##ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፤ ##በዚህ ልክ ሊጠብቀን የሚችል ታማኝ ሊቀካህናት ኢየሱስ ስላለልን ከቶ ስጋት አይገባንም ፤ ከመስቀሉ ላይም አይናችንን አናነሳም ፤ ኢየሱስ በልባችን እስክሳልም ምጥ ይይዘናል “(ገላትያ 4:19 19 የምወድዳችሁ ልጆቼ ሆይ፤ ክርስቶስ በውስጣችሁ እስኪቀረጽ ድረስ፣ ስለ እናንተ እንደ ገና ምጥ ይዞኛል፤...)” 🙏ይሄንን ለምታነቡ ሁሉ ፤ 🙏ፀሎቴ🙏 ይህ ነው ፣#ክርስቶስ በፊታችሁ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ይሳል፤ #ከምትዳሱት ፣ #ከጨበጣችሁት ነገር በላይ ፤ #ከራሳችሁ በላይ ፤ #በክርስቶስ ላይ መታመን ይሁንላችሁ 🙏 ✍️ወንድም አሻግሬ

ደባል የለኝም ህይወቴን ሚጋራ ግማሹ በአንተ ግማሹን ሌላ የሚመራ መልሼ ላልወስደው ሰጥቼሃለሁ ራሴን ለውድድር የማትቀርብ ምርጫዬ ስለሆንክ      ለእኔ ህይወት ኢየሱስ ነህ         ፊልጵስዩስ 1:21 21 ለእኔ፣ መኖር ክርስቶስ ነው፤ ሞትም ማትረፍ ነው። መኖር የማልችለው ካላንተ ብቻ ነው ... ያለ #ሀብት ያለ #ዝና ያለ #ዘመድ... መኖር እችላለሁ ግን #ያላንተ(ኢየሱስ) #እስትንፋስ የለኝም !  ለእኔ ሌላ ትምክህት የለኝም 😭             ገላትያ  6:14 14 ነገር ግን ዓለም ለእኔ ከተሰቀለበት፣ እኔም ለዓለም ከተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር፣ ሌላው ትምክሕት ከእኔ የራቀ ይሁን። አንድአንዱ “ያላአንቺ መኖር አልችልም ይላል (ፍቅረኛውን)  ፤  ያላንተ መኖር አልችልም ትላለች (ፍቅረኛዋን) ”  ግን ተመልሰው አንቺን ማየት አልፈልግም ፤ አንተን ማየት አልፈልግም ይባላሉ ! ግን #ኢየሱሴ ያንተ ፍቅር ወረት የለበትም ፤ ለዚህ ነው ያላንተ ብቻ ባዶ የሆንኩት   ❤ፍቅሬን የማፈሰው አንተ ላይ ብቻ ነው  😭 እንባዬም የሚፈሰው በአንተ ላይ ብቻ ነው ከራሴ በላይ እወድሃለሁ ፤ ነፍሴ በአንተ ፍቅር   ⛓️ ታስራለች ⛓️  ወደሌላው እንደልሄድ የፍቅርህ ⛓️ሰንሰለት ⛓️ አስሮኛል ⛓️          ወደ ገላትያ ሰዎች 6:17 --- š⁡ እኔ የኢየሱስን ማኅተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ስንኳ አያድክመኝ።              ✍️ወንድም አሻግሬ

አታንብብ 😁 ! በጣም ይጠቅምሃል 😁 🧒 አንድ ወጣት በከተማው ውስጥ ወደሚገኝ አንድ ትልቅ 🥬 የአትክልት ስፍራ ይሄዳል። በዚያም አንድ እጅግ የሚያምር፣ ቅጠሎቹ የለመለሙ፣ ግንዱ የጠነከረ እና ፍሬዎቹ ያማሩ ግዙፍ ዛፍ ይመለከታል። በዛፉ ግርማ ሞገስ እና ውበት ተደንቆ አትክልተኛውን ይጠይቀዋል። ​"ይህ ዛፍ እንዴት እንዲህ ሊያምርና ሊያፈራ ቻለ? ሌሎቹ ዛፎች በድርቅ ሲጠወልጉ ይህኛው ግን እጅግ ለምልሟል፤ ሚስጥሩ ምንድን ነው?" አለው። ​አትክልተኛውም ፈገግ ብሎ መለሰ፦ "ልጄ፣ ሚስጥሩ ከላይ በምታየው ቅርንጫፍ፣ አበባ ወይም ቅጠል ላይ አይደለም። ሚስጥሩ ከመሬት በታች፣ ከሰው እይታ ተሰውሮ በሚገኘው 'ሾሊ' ላይ ነው። የዚህ ዛፍ ስሮች እጅግ ወደ ጥልቅ መሬት ስለገቡ፣ ከየትኛውም ዛፍ በላይ ውሃን ከሩቅ መሳብ ይችላሉ። ከላይ የምታየው ውበት ሁሉ፣ ከታች ከተደበቀው ሾር የመጣ ነው።" 📚 መጽሐፍ ማንበብ ማለት ለአንድ ሰው አእምሮ ልክ እንደ ዛፍ ሾር ነው። ሰዎች ክፍልህ ውስጥ ብቻህን ሆነህ 📚መጽሐፍ ስታነብ ላያዩህ ይችላሉ፤ የምታነበው 📚መጽሐፍም ወዲያውኑ ውጫዊ ለውጥ ላያሳይህ ይችላል። ነገር ግን የምታነባቸው 📚መጽሐፍት በአእምሮህ ውስጥ ጠንካራ ሾር እየሰደዱ ይሄዳሉ። ​በመጨረሻም... አነጋገርህ፣ አስተሳሰብህ...ስብዕናህ ልክ እንደ ዛፉ ፍሬዎች አምረው እና ለምልመው ለሰዎች መታየት ይጀምራሉ። አእምሮውን በንባብ ያላጠነከረ እና የራሱ ሾር የሌለው ሰው ግን፣ በህይወት ፈተና ንፋስ ቶሎ ይወድቃል። ​ጥልቅ ማንነት ያለው ሰው ለመሆን፣ 📖 በንባብ ጠንካራ ሾር እንትከል! እኛ አማኞች ደግሞ ምርጫ ውስጥ የማናስገባው ፣ ብርሃን የሆነልን ፣ ክርሰቶስን ያገኘንበት ከሁሉ የሚበልጥ መጽሐፍ ፤ ህይወት ያለበት ብቸኛው መጽሐፍ 📖 #መጽሐፍ #ቅዱስ ብቻ ነው !  #መጽሐፍ  #ቅዱስ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ነው ! 📖2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3:15-16📖 --- š⁾ ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ #ኢየሱስን #በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን #ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል። š⁜ የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሼል ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር #መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ #ለትምህርትና #ለተግሣጽ #ልብንም ለማቅናት #በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል። ✍️ወንድም አሻግሬ ሰሞኑን የጠፋውት ለቅሶ ላይ ስለነበርኩ ነው 🙏

የማትጨልምብኝ የፅድቅ ብርሃኔ ከቶ ማልሰጋብህ የዘላለም ዋሴ ፍርዴን አስወግደህ ስራህ ተቆጠረልኝ በእኔ ምትክ ሆነህ በአብ ፊት ታየህልኝ ዮሐንስ 3:14-18 14 ሙሴ በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ፣ የሰው ልጅም እንዲሁ ሊሰቀል ይገባዋል፤ 15 ይኸውም በእርሱ የሚያምን ሁሉ #የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው ነው። 16 “በእርሱ የሚያምን ሁሉ #የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ ##እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወድዷልና። 17 እግዚአብሔር ልጁን ወደ ዓለም የላከው በዓለም ##ለመፍረድ ሳይሆን፣ ዓለምን በእርሱ ለማዳን ነው። 18 በእርሱ የሚያምን ሁሉ ##አይፈረድበትም፤ በእርሱ የማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ፣ አሁኑኑ #ተፈርዶበታል። #ቃሉ #የታመነ #ነው በክርስቶስ ስላለው ፍርድና ኩነኔ የለብኝም ! ወንድም አሻግሬ

አንድአንድ ጊዜ እኛ ክርስቲያኖች ፣ ሰው ስገፅፀን ይሁን ስመክረን በእኔ ህይወት ምን አገባህ ብለን ምላሽ እንሰጣላን … እውነቱ ግን የክርስቶስ ከሆንን በኃላ የእኔ የምንለው ህይወት የለንም ፤ #ብንበላ ፣ #ብንጠጣ፣ #ብንለብስ፣ #ብንማር ፣ #ብንሰራ ፣ #ብናገባ ፣ #ብንወልድ ፣ #ብንኖር ፣ #ብንሞት… ሁሉንም ነገር ለእርሱ ክብር ነው የምናደርጋው ! ገላትያ 2:20-21 20 ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤ ነገር ግን ክርስቶስ በውስጤ ይኖራል። አሁንም በሥጋ የምኖረው ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን አሳልፎ በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለኝ እምነት ነው። 21 የእግዚአብሔርን ጸጋ አላቃልልም፤ ጽድቅ በሕግ በኩል የሚገኝ ከሆነማ፣ ክርስቶስ እንዲያው በከንቱ ሞተ ማለት ነዋ!” የፀደቅነው በፀጋ ፤ የምንኖረው በህግ አይደለም ! ❌ የፀደቅነው በፀጋ ፤ የምንኖረውም በፀጋ ነው ✅ ወንድም አሻግሬ

🚧ማንበቡ ግዴታ አይደለም ...በጣም ያስተማረኝ ታሪክ ስለሆነ ነው ያጋረውት 🙏 #ኩባያ እና ጨው፦ 🏛️ አንድ በህይወቱ ሁሌም የሚበሳጭና አማራሪ ወጣት ነበር። በአካባቢው ያሉ ሰዎች ባህሪ፣ ንግግራቸውና ድርጊታቸው ሁሌም ሰላም ይነፍገው ነበር። በመጨረሻም መፍትሄ ፍለጋ ወደ አንድ ትልቅ አረጋዊ ዘንድ ሄደ። አረጋዊው ሰው የልጁን ችግር ካዳመጡ በኋላ፣ አንድ እፍኝ ጨውና አንድ ብርጭቆ ውሃ እንዲያመጣ አዘዙት። ወጣቱም አመጣ። አረጋዊውም "አሁን ጨዉን በውሃው ውስጥ ጨምረህ ጠጣው" አሉት። ወጣቱም እንደታዘዘው አደረገ። #"እንዴት ነው ጣዕሙ?" ሲሉ ጠየቁት። ወጣቱም ፊቱን አጨፍግጎ "በጣም ይከረፋል! ያቃጥላል!'' ሲል መለሰ። አረጋዊው ፈገግ ብለው #"አሁንም አንድ እፍኝ ጨው ይዘህ ተከተለኝ" አሉት። ወደ አቅራቢያው ወደሚገኝ አንድ ትልቅና ንጹህ ኩሬ (ሀይቅ) ይዘውት ሄዱ። "አሁን ጨዉን ኩሬው ውስጥ ጨምረውና ከኩሬው ውሃ ቅመስ" አሉት። ወጣቱም ከኩሬው ውሃ በእጁ ዘግኖ ቀመሰ። "አሁንስ ጣዕሙ እንዴት ነው?'' አሉት። ወጣቱም "በጣም ደስ የሚልና ቀዝቃዛ ነው" አለ። "የጨዉ ጣዕም ይሰማሃል?" ሲሉ ጠየቁት። "በፍጹም!' ሲል መለሰ። 🎯 #ትምህርቱ፦🎯 አረጋዊው የልጁን ትከሻ መታ አድርገው እንዲህ አሉት፦ 🎯 "ልጄ ሆይ! በህይወትህ የሚያጋጥሙህ የሰዎች ክፉ ባህሪና የሚያበሳጩ ነገሮች ልክ እንደዚህ ጨው ናቸው። መጠናቸው ተመሳሳይ ነው። ነገር ግን የሚያበሳጩህ ነገሮች ጣዕም የሚወሰነው ጨዉን በጨመርክበት ዕቃ  ❤ (በልብህ) መጠን ነው። #በሰው ስትበሳጭ #ልብህ እንደ ብርጭቆ ጠቧል ማለት ነው። #ልብህን እንደ ኩሬ ካሰፋኸው ግን፣ የሰዎች መጥፎ ባህሪ ሊያመርህ ወይም ሰላምህን ሊያናጋ አይችልም።" 🎯 #በሰዎች ድርጊት መበሳጨት የምናቆመው ሰዎቹ ሲቀየሩ ሳይሆን፣ እኛ ለነገሮች የምንሰጠው ቦታና የልባችን ስፋት ሲጨምር ነው። እኔ ከማን አንሼ ብለን ቁጣ የሚንሞላ ከሆነ ብዙ ነገር እናጣለን ! 🎯             ምሳሌ 24:29 29 “በእኔ ላይ እንደ ሠራብኝ እሠራለታለሁ፤   ሾለ አድራጎቱም የእጁን እመልስለታለሁ” አትበል።           1 ጴጥሮስ 3:9 9 ክፉን በክፉ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ፤ በዚህ ፈንታ ባርኩ፤ ምክንያቱም እናንተ የተጠራችሁት እንደነዚህ ያሉትን ነገሮች እያደረጋችሁ በረከትን ለመውረስ ነው።              ሮሜ 12:18 18 ቢቻላችሁስ በበኩላችሁ ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።

እሺ ልተው ብዬ ሳስብ እሱን እንደማወቅ ጥበብ የለም፤ እሺ ልወቅ ብዬ ስጀምር ደግሞ እርሱ ከመታወቅ በላይ ነው።
“የእግዚአብሔርን ጥልቅ ምስጢር ልትለካ ትችላለህን? ወይስ ሁሉን የሚችለውን አምላክ መርምረህ ትደርስበታለህን? ከሰማይ ይልቅ ከፍ ይላል፤ ምን ልታደርግ ትችላለህ? ከሲኦልም ይጠልቃል፤ ምን ልታውቅ ትችላለህ? መጠኑ ከምድር ይልቅ ይረዝማል፤ ከባሕርም ይልቅ ይሰፋል። እርሱ ተከታትሎ መጥቶ በግዞት ቢያስቀምጥህ፣ የፍርድ ሸንጎም ቢሰበስብ፣ ማን ሊከለክለው ይችላል?” (
ኢዮብ 11:7-10)  
የክብር አባት የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክ ይበልጥ እንድታውቁት፣ የጥበብና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ ያለ ማቋረጥ እለምናለሁ
። (ኤፌሶን 1:17) አባት አምላክ ሆይ፤ አንተ ከአእምሯችን በላይ ነህ። ነገር ግን የሰውን ሥጋ ለብሰህ ወደዚህ ዓለም መጣህ። እንደ እኔ ያሉ ኃጢአተኞችን ለማዳንና ለእኔ ኃጢአተኛው ቤዛ ለመሆን መጣህ።
“የሰው ልጅ ሊያገለግልና ሕይወቱን ለብዙዎች ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ መጣ እንጂ ሊገለገል አልመጣምና
።” (ማርቆስ 10:45) ይህንን ፍቅር እንዴት መግለጽ እችላለሁ? ከአረዳዴ በላይ ነው፤ ከምናቤም በላይ ይልቃል። እኔ ማለት የምችለው ይህንን ብቻ ነ
ው፦ “ስለዚህ ዘወትር የምስጋናን መሥዋዕት፣ ይኸውም ለስሙ የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ በኢየሱስ አማካይነት ለእግዚአብሔር እናቅር
ብ።” (ዕብራውያን 13:15) አባት ሆይ፤ አንተ ከሐሳቦቼ በላይ ከፍ ትላለህ፤ ከማስተዋሌም በላይ ትጠልቃለህ። ነገር ግን በልጅህ አማካይነት፣ ወደ እኔ ቀረብህ። ልጨብጥህ (ልይዝህ) አልችልም፤ ግን ላመልክህ እችላለሁ። ሙሉ በሙሉ ላውቅህ አልችልም፤ በጸጋህ ግን እውነትኛውን እውቀት አውቅሃለሁ። ስለዚህ አእምሮዬ ሊደርስበት ለማይችለው አምላክ ፣ ከንፈሮቼ ምስጋናን ያቅርቡልህ። አሜን። ✍️TBL https://t.me/btlfld https://t.me/LOGOSJO1

የቴሌግራም አካውንት እየተጠለፈ ነው !!! ሙሉ መረጃውን እዚህ ጋር ያንብቡ

ኤፌሶን 2:10 … ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን።
ኤፌሶን 2:10 … ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ የተፈጠርን የእግዚአብሔር እጅ ሥራዎች ነን።